ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ይታሰባል ተብሎ ባልተገመተ ሁኔታ የዓድዋ በዓል በኢትዮጵያዊነት መንፈስ በትግራይ የዓድዋ ከተማ ሶሎዳ ተራራ ሥር መከበሩን ኢፕድ ዘግቧል። በበዓሉ ላይ ህፃናት ስለ ዓድዋ ድል የሚተርክ ህብረ ዝማሬ አቅርበዋል። የከተማው ነዋሪዎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በዓሉን ለመታደም ማልደው በሥፍራው ተገኝተዋል። ከዚህ በተጨማሪም የኢትዮጵያን ሠንደቅ ዓላማ የሚያውለበልቡና በአማርኛ የተጻፉ አስደማሚ መፈክሮች በበዓሉ ሰልፍ ላይ ታይተዋል። ትህነግ በግፍ በሚገዛት ትግራይ ይህ ዓይነት አከባበር መከሰቱ ለክልሉ ሕዝብ የነጻነት ተስፋ የፈነጠቀ ነው ሲሉ አስተያየት ሰጪዎች ተናግረዋል። ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ
Adwa 127
በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ?
የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን "በዓሉ በአዲስ አበባ ሶስቱም ቦታ በሰላም ተከብሯል፣ በዓሉን እንዳያከብር የተከለከለ ሰውም የለም" ብሏል 127ኛው የአድዋ ድል በዓል በአዲስ አበባ ሚኒሊክ አደባባይ፣ አድዋ ድልድይ እና መስቀል አደባባይ በተለያዩ ስነስርአቶች ተከብሯል። የድል በዓሉን በሚኒሊክ አደባባይ ለማክበር የወጡ የመዲናዋ ነዋሪዎች ግን” በዓሉን እንዳናከብር ተከልክለን ነበር፤ አስለቃሽ ጭስም ተተኩሶብናል” ብለዋል ከአል አይን አማርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ። እታገኘሁ በየዓመቱ የካቲት 23 የአድዋ ድል በዓልን ሚኒሊክ አደባባይና አድዋ ድልድይ ታከብራለች። ዘንድሮም በዓሉን ሁሌም እንደምታደርገው ጠዋት 3:00 መንገድ አቆራርጣ ሰሜን ሆቴል ከባለቤቷና ልጇ ጋር ደረሰች። ሆኖም ህዝባዊ በዓሉን ማክበር ከጀመረች ወዲህ ያልገጠማት ሁነት እንደተፈጠረ ገልጻለች። እታገኘሁ … [Read more...] about በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ?