• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ?

March 2, 2023 09:43 am by Editor Leave a Comment

የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን “በዓሉ በአዲስ አበባ ሶስቱም ቦታ በሰላም ተከብሯል፣ በዓሉን እንዳያከብር የተከለከለ ሰውም የለም” ብሏል

127ኛው የአድዋ ድል በዓል በአዲስ አበባ ሚኒሊክ አደባባይ፣ አድዋ ድልድይ እና መስቀል አደባባይ በተለያዩ ስነስርአቶች ተከብሯል።

የድል በዓሉን በሚኒሊክ አደባባይ ለማክበር የወጡ የመዲናዋ ነዋሪዎች ግን” በዓሉን እንዳናከብር ተከልክለን ነበር፤ አስለቃሽ ጭስም ተተኩሶብናል” ብለዋል ከአል አይን አማርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ።

እታገኘሁ በየዓመቱ የካቲት 23 የአድዋ ድል በዓልን ሚኒሊክ አደባባይና አድዋ ድልድይ ታከብራለች።

ዘንድሮም በዓሉን ሁሌም እንደምታደርገው ጠዋት 3:00 መንገድ አቆራርጣ ሰሜን ሆቴል ከባለቤቷና ልጇ ጋር ደረሰች። ሆኖም ህዝባዊ በዓሉን ማክበር ከጀመረች ወዲህ ያልገጠማት ሁነት እንደተፈጠረ ገልጻለች።

እታገኘሁ የጸጥታ ኃይሎች መንገድ ዘግተው “ማለፍ አትችሉም” በማለት ግርግር መፈጠራቸውን ለአል ዐይን ተናግራለች።

“ከኋላችን አድማ በታኞች (ሄልሜትና መከላከያ የለበሱ) መጥተው አስለቃሽ ጭስ ሲተኩሱ ሁላችንም እግሬ አውጭኝ አልን” የምትለው እታገኘሁ፥ በዚህም ህዝቡ ራሱን ከአደጋ ለመጠበቅ መበተኑን ትገልጻለች።

በዓሉን ለማክበር ወደ ሚኒሊክ አደባባይ እየተጓዙ የነበሩ ሰዎች ማዋከብም እንደደረሰባቸውም ነው የአይን እማኟ የተናገረችው።

ሌላኛው ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የመዲናዋ ነዋሪም ከጓደኞቹ ጋር ከፈረንሳይና ስድስት ኪሎ ተሰባስበው ወደ ሚኒሊክ አደባባይ በዓሉን ለማክበር ቢጓዝም “አትገቡም” እንደተባሉ ይናገራል።

“አትገቡም ብለው አስቆሙን፣ ሰው እየበዛ ሲመጣ ግን አስገቡን፤ የጸጥታ ሃይሎች ሃይል ከሰበሰቡ በኋላ ግን አስለቃሽ ጭስ ለቀዉብን፣ ትርምስ ሆነ፣ ህጻናትና ነፍሰጡሮች ጭምር ራሳቸውን ስተውነበር፣ በጭሱ ምክንያት የሚያስመልሳቸውን ሰዎችም አይቻለሁ” ይላል የአይን እማኙ።

በተፈጠረው ግፊያና ትርምስ በርካታ ሰው ተረጋግጦ መጎዳቱንም ነው ለአል አይን የተናገረው።

“ከዚህ በፊት እንዲህ አይነት ነገር ገጥሞን አያውቀም፤ የጸጥታ ሃይሎች ሁለት ሶስት ሆነው የአጼ ሚኒሊክ እና ጣይቱን ቲሸርት እንዲሁም ባንዲራ (አረንጓዴ ቢጫ ቀይ) የበለሱ ሰዎችን እየመረጡ ሲመልሱ ነበር” ሲልም አክሏል።

ስሟ እንዳይጠቀስ የፈለገች እና በዓሉን ለማክበር ወደ ጊዮርጊስ ለመምጣት የሞከረች ሌላኛዋ በዓል አክባሪም “ጣልያን ሀገራችንን በቅኝ ግዛት በወረረ ጊዜ እናቶቻችን ከሌሎች ማህበረሰብ ጋር ሆነው የከፈሉትን መስዋዕትነት ለማሰብ በየዓመቱ በምኒልክ አደባባይ እየተገኘሁ አከብራለሁል፤ ዘንድሮ ግን ወደ ሚኒሊክ ሀውልት እንዳልቀርብ በጸጥታ ሀይል ተከልክያለሁ” ብላለች።

የመንግስት ኮሙንኬሽን ሚንስትር ዴኤታ አቶ አቶ ከበደ ደሲሳ በበኩላቸው የዘንድሮው 127ኛው የአድዋ ድል በዓል በሀገር አቀፍ ደረጃ መከበሩን ተናግረዋል።

አቶ ከበደ አክለውም በአዲስ አበባም በመስቀል አደባባይ፣ በአድዋ ድልድይ እና በሚኒሊክ አደባባይ በሰላም መከበሩን ጠቅሰዋል።

በምኒልክ አደባባይ በነበረው የበዓሉ አከባበር ወቅት ዜጎች ወደ በዓሉ ማክበሪያ ስፍራ እንዳይገቡ በጸጥታ ሀይሎች መከልከላቸው ተነግሯል፤ ይህ ለምን ሆነ? በሚል ለአቶ ከበደ ላቀረብንላቸው ጥያቄ “በዓሉ በአዲስ አበባ ሶስቱም ቦታ በሰላም ተከብሯል፤ በዓሉን እንዳያከብር የተከለከለ ሰውም የለም” ሲሉ ለአል ዓይን ተናግረዋል።

ወደ ኋላ ላይ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ባወጣው መግለጫ የሚከተለውን ብሏል፤

“127ኛው የአድዋ ድል በዓል ከወትሮው በላቀና ድሉን በሚመጥን መልኩ እንዲከበር የመከላከያ ሠራዊትና ሌሎችም ባለ ድርሻ አካላት በቂ ዝግጅት አድርገዋል። የጸጥታ ተቋማትም የበዓሉን ድባብ የሚያውክ ነገር እንዳይፈጠር የቅድሚያ መረጃዎችን መሠረት አድርገው በበቂ ሁኔታ ተዘጋጅተዋል። 

“በበዓል አዘጋጆችና በጸጥታ አካላት ጥምረት በዓሉ በብሔራዊ ደረጃና በመላ ሀገሪቱ በታቀደለት ልክና ዓላማ ተከብሯል። 

“ይሁን እንጂ ይሄንን መሰል ሀገራዊ ክንውኖች እንዳይሳኩ የሚፈልጉ አካላት መኖራቸውን የጸጥታ አካላት አስቀድሞ መረጃ ነበራቸው። በመረጃው መሠረትም ተገቢውን ጥንቃቄ እና ጥበቃ አከናውነዋል። በተለይም በምኒልክ አደባባይ የሚደረገውን በዓል ለመረበሽ የፈለጉ አካላት ሁከት ለመቀስቀስ ሞክረው ነበር። እነዚህ አካላት የአደባባዩን በዓል መረበሽ ሲያቅታቸው በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሚደረገውን ሃይማኖታዊ በዓል ለመረበሽ ሞክረዋል። 

“የጸጥታ አካላት ሑከት ፈጣሪዎችን ለማስታገሥ በሚያደርጉት ጥረት በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ የነበረው ሃይማኖታዊ በዓል ሊስተጓጎልና ለሃይማኖታዊ በዓል የመጡ  ምእመናን መጠነኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል። ሆኖም የጸጥታ አካላት ባደረጉት ርብርብ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ የተሸረበዉን ሤራ ከሽፏል። መንግሥት ይሄንን መሰል ተግባር  መፈጸም እንደሌለበት ያምናል።  ሁኔታውንም አጣርቶ በችግር ፈጣሪዎች ላይ ተገቢውን ርምጃ ይወስዳል።

“በአጠቃላይ በዓሉ በታሰበው ደረጃና ልክ እንዲከበር ኃላፊነት ወስደው የሠሩትን ሁሉ መንግሥት ያመሰግናል። ከዘንድሮው አከባበር በተወሰዱ ትምህርቶችም ለወደፊቱ የተሻለ የበዓል አከባበር እንዲኖር መንግሥት ጥረት ያደርጋል።”

በዚህ መልኩ ነጻነት በሚከበርበት ቀን በሕዝብ ላይ የደረሰን እንግልት ምላሽ ሊሰጠውና አጥፊዎችም ተገቢው ቅጣት ሊቀበሉ ይገባል ሲሉ በርካታ አስተያየት ሰጪዎች ተናግረዋል።

ከዚህ ሌላ በዓሉ በትግራይ ዓድዋ ከተማ ተከብሯል። በዕለቱ በአማርኛ ተጽፈው የታዩት መፈክሮች ት ህነግ በሚገዛት ትግራይ የማይታሰቡ እንደሆኑ የበዓሉን ዝግጅቶች የተከታተሉ ይናገራሉ።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: Adwa 127, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule