• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ?

March 2, 2023 09:43 am by Editor Leave a Comment

የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን “በዓሉ በአዲስ አበባ ሶስቱም ቦታ በሰላም ተከብሯል፣ በዓሉን እንዳያከብር የተከለከለ ሰውም የለም” ብሏል

127ኛው የአድዋ ድል በዓል በአዲስ አበባ ሚኒሊክ አደባባይ፣ አድዋ ድልድይ እና መስቀል አደባባይ በተለያዩ ስነስርአቶች ተከብሯል።

የድል በዓሉን በሚኒሊክ አደባባይ ለማክበር የወጡ የመዲናዋ ነዋሪዎች ግን” በዓሉን እንዳናከብር ተከልክለን ነበር፤ አስለቃሽ ጭስም ተተኩሶብናል” ብለዋል ከአል አይን አማርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ።

እታገኘሁ በየዓመቱ የካቲት 23 የአድዋ ድል በዓልን ሚኒሊክ አደባባይና አድዋ ድልድይ ታከብራለች።

ዘንድሮም በዓሉን ሁሌም እንደምታደርገው ጠዋት 3:00 መንገድ አቆራርጣ ሰሜን ሆቴል ከባለቤቷና ልጇ ጋር ደረሰች። ሆኖም ህዝባዊ በዓሉን ማክበር ከጀመረች ወዲህ ያልገጠማት ሁነት እንደተፈጠረ ገልጻለች።

እታገኘሁ የጸጥታ ኃይሎች መንገድ ዘግተው “ማለፍ አትችሉም” በማለት ግርግር መፈጠራቸውን ለአል ዐይን ተናግራለች።

“ከኋላችን አድማ በታኞች (ሄልሜትና መከላከያ የለበሱ) መጥተው አስለቃሽ ጭስ ሲተኩሱ ሁላችንም እግሬ አውጭኝ አልን” የምትለው እታገኘሁ፥ በዚህም ህዝቡ ራሱን ከአደጋ ለመጠበቅ መበተኑን ትገልጻለች።

በዓሉን ለማክበር ወደ ሚኒሊክ አደባባይ እየተጓዙ የነበሩ ሰዎች ማዋከብም እንደደረሰባቸውም ነው የአይን እማኟ የተናገረችው።

ሌላኛው ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የመዲናዋ ነዋሪም ከጓደኞቹ ጋር ከፈረንሳይና ስድስት ኪሎ ተሰባስበው ወደ ሚኒሊክ አደባባይ በዓሉን ለማክበር ቢጓዝም “አትገቡም” እንደተባሉ ይናገራል።

“አትገቡም ብለው አስቆሙን፣ ሰው እየበዛ ሲመጣ ግን አስገቡን፤ የጸጥታ ሃይሎች ሃይል ከሰበሰቡ በኋላ ግን አስለቃሽ ጭስ ለቀዉብን፣ ትርምስ ሆነ፣ ህጻናትና ነፍሰጡሮች ጭምር ራሳቸውን ስተውነበር፣ በጭሱ ምክንያት የሚያስመልሳቸውን ሰዎችም አይቻለሁ” ይላል የአይን እማኙ።

በተፈጠረው ግፊያና ትርምስ በርካታ ሰው ተረጋግጦ መጎዳቱንም ነው ለአል አይን የተናገረው።

“ከዚህ በፊት እንዲህ አይነት ነገር ገጥሞን አያውቀም፤ የጸጥታ ሃይሎች ሁለት ሶስት ሆነው የአጼ ሚኒሊክ እና ጣይቱን ቲሸርት እንዲሁም ባንዲራ (አረንጓዴ ቢጫ ቀይ) የበለሱ ሰዎችን እየመረጡ ሲመልሱ ነበር” ሲልም አክሏል።

ስሟ እንዳይጠቀስ የፈለገች እና በዓሉን ለማክበር ወደ ጊዮርጊስ ለመምጣት የሞከረች ሌላኛዋ በዓል አክባሪም “ጣልያን ሀገራችንን በቅኝ ግዛት በወረረ ጊዜ እናቶቻችን ከሌሎች ማህበረሰብ ጋር ሆነው የከፈሉትን መስዋዕትነት ለማሰብ በየዓመቱ በምኒልክ አደባባይ እየተገኘሁ አከብራለሁል፤ ዘንድሮ ግን ወደ ሚኒሊክ ሀውልት እንዳልቀርብ በጸጥታ ሀይል ተከልክያለሁ” ብላለች።

የመንግስት ኮሙንኬሽን ሚንስትር ዴኤታ አቶ አቶ ከበደ ደሲሳ በበኩላቸው የዘንድሮው 127ኛው የአድዋ ድል በዓል በሀገር አቀፍ ደረጃ መከበሩን ተናግረዋል።

አቶ ከበደ አክለውም በአዲስ አበባም በመስቀል አደባባይ፣ በአድዋ ድልድይ እና በሚኒሊክ አደባባይ በሰላም መከበሩን ጠቅሰዋል።

በምኒልክ አደባባይ በነበረው የበዓሉ አከባበር ወቅት ዜጎች ወደ በዓሉ ማክበሪያ ስፍራ እንዳይገቡ በጸጥታ ሀይሎች መከልከላቸው ተነግሯል፤ ይህ ለምን ሆነ? በሚል ለአቶ ከበደ ላቀረብንላቸው ጥያቄ “በዓሉ በአዲስ አበባ ሶስቱም ቦታ በሰላም ተከብሯል፤ በዓሉን እንዳያከብር የተከለከለ ሰውም የለም” ሲሉ ለአል ዓይን ተናግረዋል።

ወደ ኋላ ላይ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ባወጣው መግለጫ የሚከተለውን ብሏል፤

“127ኛው የአድዋ ድል በዓል ከወትሮው በላቀና ድሉን በሚመጥን መልኩ እንዲከበር የመከላከያ ሠራዊትና ሌሎችም ባለ ድርሻ አካላት በቂ ዝግጅት አድርገዋል። የጸጥታ ተቋማትም የበዓሉን ድባብ የሚያውክ ነገር እንዳይፈጠር የቅድሚያ መረጃዎችን መሠረት አድርገው በበቂ ሁኔታ ተዘጋጅተዋል። 

“በበዓል አዘጋጆችና በጸጥታ አካላት ጥምረት በዓሉ በብሔራዊ ደረጃና በመላ ሀገሪቱ በታቀደለት ልክና ዓላማ ተከብሯል። 

“ይሁን እንጂ ይሄንን መሰል ሀገራዊ ክንውኖች እንዳይሳኩ የሚፈልጉ አካላት መኖራቸውን የጸጥታ አካላት አስቀድሞ መረጃ ነበራቸው። በመረጃው መሠረትም ተገቢውን ጥንቃቄ እና ጥበቃ አከናውነዋል። በተለይም በምኒልክ አደባባይ የሚደረገውን በዓል ለመረበሽ የፈለጉ አካላት ሁከት ለመቀስቀስ ሞክረው ነበር። እነዚህ አካላት የአደባባዩን በዓል መረበሽ ሲያቅታቸው በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሚደረገውን ሃይማኖታዊ በዓል ለመረበሽ ሞክረዋል። 

“የጸጥታ አካላት ሑከት ፈጣሪዎችን ለማስታገሥ በሚያደርጉት ጥረት በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ የነበረው ሃይማኖታዊ በዓል ሊስተጓጎልና ለሃይማኖታዊ በዓል የመጡ  ምእመናን መጠነኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል። ሆኖም የጸጥታ አካላት ባደረጉት ርብርብ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ የተሸረበዉን ሤራ ከሽፏል። መንግሥት ይሄንን መሰል ተግባር  መፈጸም እንደሌለበት ያምናል።  ሁኔታውንም አጣርቶ በችግር ፈጣሪዎች ላይ ተገቢውን ርምጃ ይወስዳል።

“በአጠቃላይ በዓሉ በታሰበው ደረጃና ልክ እንዲከበር ኃላፊነት ወስደው የሠሩትን ሁሉ መንግሥት ያመሰግናል። ከዘንድሮው አከባበር በተወሰዱ ትምህርቶችም ለወደፊቱ የተሻለ የበዓል አከባበር እንዲኖር መንግሥት ጥረት ያደርጋል።”

በዚህ መልኩ ነጻነት በሚከበርበት ቀን በሕዝብ ላይ የደረሰን እንግልት ምላሽ ሊሰጠውና አጥፊዎችም ተገቢው ቅጣት ሊቀበሉ ይገባል ሲሉ በርካታ አስተያየት ሰጪዎች ተናግረዋል።

ከዚህ ሌላ በዓሉ በትግራይ ዓድዋ ከተማ ተከብሯል። በዕለቱ በአማርኛ ተጽፈው የታዩት መፈክሮች ት ህነግ በሚገዛት ትግራይ የማይታሰቡ እንደሆኑ የበዓሉን ዝግጅቶች የተከታተሉ ይናገራሉ።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: Adwa 127, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule