• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ?

March 2, 2023 09:43 am by Editor Leave a Comment

የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን “በዓሉ በአዲስ አበባ ሶስቱም ቦታ በሰላም ተከብሯል፣ በዓሉን እንዳያከብር የተከለከለ ሰውም የለም” ብሏል

127ኛው የአድዋ ድል በዓል በአዲስ አበባ ሚኒሊክ አደባባይ፣ አድዋ ድልድይ እና መስቀል አደባባይ በተለያዩ ስነስርአቶች ተከብሯል።

የድል በዓሉን በሚኒሊክ አደባባይ ለማክበር የወጡ የመዲናዋ ነዋሪዎች ግን” በዓሉን እንዳናከብር ተከልክለን ነበር፤ አስለቃሽ ጭስም ተተኩሶብናል” ብለዋል ከአል አይን አማርኛ ጋር ባደረጉት ቆይታ።

እታገኘሁ በየዓመቱ የካቲት 23 የአድዋ ድል በዓልን ሚኒሊክ አደባባይና አድዋ ድልድይ ታከብራለች።

ዘንድሮም በዓሉን ሁሌም እንደምታደርገው ጠዋት 3:00 መንገድ አቆራርጣ ሰሜን ሆቴል ከባለቤቷና ልጇ ጋር ደረሰች። ሆኖም ህዝባዊ በዓሉን ማክበር ከጀመረች ወዲህ ያልገጠማት ሁነት እንደተፈጠረ ገልጻለች።

እታገኘሁ የጸጥታ ኃይሎች መንገድ ዘግተው “ማለፍ አትችሉም” በማለት ግርግር መፈጠራቸውን ለአል ዐይን ተናግራለች።

“ከኋላችን አድማ በታኞች (ሄልሜትና መከላከያ የለበሱ) መጥተው አስለቃሽ ጭስ ሲተኩሱ ሁላችንም እግሬ አውጭኝ አልን” የምትለው እታገኘሁ፥ በዚህም ህዝቡ ራሱን ከአደጋ ለመጠበቅ መበተኑን ትገልጻለች።

በዓሉን ለማክበር ወደ ሚኒሊክ አደባባይ እየተጓዙ የነበሩ ሰዎች ማዋከብም እንደደረሰባቸውም ነው የአይን እማኟ የተናገረችው።

ሌላኛው ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የመዲናዋ ነዋሪም ከጓደኞቹ ጋር ከፈረንሳይና ስድስት ኪሎ ተሰባስበው ወደ ሚኒሊክ አደባባይ በዓሉን ለማክበር ቢጓዝም “አትገቡም” እንደተባሉ ይናገራል።

“አትገቡም ብለው አስቆሙን፣ ሰው እየበዛ ሲመጣ ግን አስገቡን፤ የጸጥታ ሃይሎች ሃይል ከሰበሰቡ በኋላ ግን አስለቃሽ ጭስ ለቀዉብን፣ ትርምስ ሆነ፣ ህጻናትና ነፍሰጡሮች ጭምር ራሳቸውን ስተውነበር፣ በጭሱ ምክንያት የሚያስመልሳቸውን ሰዎችም አይቻለሁ” ይላል የአይን እማኙ።

በተፈጠረው ግፊያና ትርምስ በርካታ ሰው ተረጋግጦ መጎዳቱንም ነው ለአል አይን የተናገረው።

“ከዚህ በፊት እንዲህ አይነት ነገር ገጥሞን አያውቀም፤ የጸጥታ ሃይሎች ሁለት ሶስት ሆነው የአጼ ሚኒሊክ እና ጣይቱን ቲሸርት እንዲሁም ባንዲራ (አረንጓዴ ቢጫ ቀይ) የበለሱ ሰዎችን እየመረጡ ሲመልሱ ነበር” ሲልም አክሏል።

ስሟ እንዳይጠቀስ የፈለገች እና በዓሉን ለማክበር ወደ ጊዮርጊስ ለመምጣት የሞከረች ሌላኛዋ በዓል አክባሪም “ጣልያን ሀገራችንን በቅኝ ግዛት በወረረ ጊዜ እናቶቻችን ከሌሎች ማህበረሰብ ጋር ሆነው የከፈሉትን መስዋዕትነት ለማሰብ በየዓመቱ በምኒልክ አደባባይ እየተገኘሁ አከብራለሁል፤ ዘንድሮ ግን ወደ ሚኒሊክ ሀውልት እንዳልቀርብ በጸጥታ ሀይል ተከልክያለሁ” ብላለች።

የመንግስት ኮሙንኬሽን ሚንስትር ዴኤታ አቶ አቶ ከበደ ደሲሳ በበኩላቸው የዘንድሮው 127ኛው የአድዋ ድል በዓል በሀገር አቀፍ ደረጃ መከበሩን ተናግረዋል።

አቶ ከበደ አክለውም በአዲስ አበባም በመስቀል አደባባይ፣ በአድዋ ድልድይ እና በሚኒሊክ አደባባይ በሰላም መከበሩን ጠቅሰዋል።

በምኒልክ አደባባይ በነበረው የበዓሉ አከባበር ወቅት ዜጎች ወደ በዓሉ ማክበሪያ ስፍራ እንዳይገቡ በጸጥታ ሀይሎች መከልከላቸው ተነግሯል፤ ይህ ለምን ሆነ? በሚል ለአቶ ከበደ ላቀረብንላቸው ጥያቄ “በዓሉ በአዲስ አበባ ሶስቱም ቦታ በሰላም ተከብሯል፤ በዓሉን እንዳያከብር የተከለከለ ሰውም የለም” ሲሉ ለአል ዓይን ተናግረዋል።

ወደ ኋላ ላይ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ባወጣው መግለጫ የሚከተለውን ብሏል፤

“127ኛው የአድዋ ድል በዓል ከወትሮው በላቀና ድሉን በሚመጥን መልኩ እንዲከበር የመከላከያ ሠራዊትና ሌሎችም ባለ ድርሻ አካላት በቂ ዝግጅት አድርገዋል። የጸጥታ ተቋማትም የበዓሉን ድባብ የሚያውክ ነገር እንዳይፈጠር የቅድሚያ መረጃዎችን መሠረት አድርገው በበቂ ሁኔታ ተዘጋጅተዋል። 

“በበዓል አዘጋጆችና በጸጥታ አካላት ጥምረት በዓሉ በብሔራዊ ደረጃና በመላ ሀገሪቱ በታቀደለት ልክና ዓላማ ተከብሯል። 

“ይሁን እንጂ ይሄንን መሰል ሀገራዊ ክንውኖች እንዳይሳኩ የሚፈልጉ አካላት መኖራቸውን የጸጥታ አካላት አስቀድሞ መረጃ ነበራቸው። በመረጃው መሠረትም ተገቢውን ጥንቃቄ እና ጥበቃ አከናውነዋል። በተለይም በምኒልክ አደባባይ የሚደረገውን በዓል ለመረበሽ የፈለጉ አካላት ሁከት ለመቀስቀስ ሞክረው ነበር። እነዚህ አካላት የአደባባዩን በዓል መረበሽ ሲያቅታቸው በቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሚደረገውን ሃይማኖታዊ በዓል ለመረበሽ ሞክረዋል። 

“የጸጥታ አካላት ሑከት ፈጣሪዎችን ለማስታገሥ በሚያደርጉት ጥረት በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ የነበረው ሃይማኖታዊ በዓል ሊስተጓጎልና ለሃይማኖታዊ በዓል የመጡ  ምእመናን መጠነኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል። ሆኖም የጸጥታ አካላት ባደረጉት ርብርብ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ የተሸረበዉን ሤራ ከሽፏል። መንግሥት ይሄንን መሰል ተግባር  መፈጸም እንደሌለበት ያምናል።  ሁኔታውንም አጣርቶ በችግር ፈጣሪዎች ላይ ተገቢውን ርምጃ ይወስዳል።

“በአጠቃላይ በዓሉ በታሰበው ደረጃና ልክ እንዲከበር ኃላፊነት ወስደው የሠሩትን ሁሉ መንግሥት ያመሰግናል። ከዘንድሮው አከባበር በተወሰዱ ትምህርቶችም ለወደፊቱ የተሻለ የበዓል አከባበር እንዲኖር መንግሥት ጥረት ያደርጋል።”

በዚህ መልኩ ነጻነት በሚከበርበት ቀን በሕዝብ ላይ የደረሰን እንግልት ምላሽ ሊሰጠውና አጥፊዎችም ተገቢው ቅጣት ሊቀበሉ ይገባል ሲሉ በርካታ አስተያየት ሰጪዎች ተናግረዋል።

ከዚህ ሌላ በዓሉ በትግራይ ዓድዋ ከተማ ተከብሯል። በዕለቱ በአማርኛ ተጽፈው የታዩት መፈክሮች ት ህነግ በሚገዛት ትግራይ የማይታሰቡ እንደሆኑ የበዓሉን ዝግጅቶች የተከታተሉ ይናገራሉ።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: Adwa 127, operation dismantle tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule