• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ

March 15, 2023 01:43 am by Editor Leave a Comment

ከፍጥነት ወሰን በላይ በመንዳት የሚደርሰውን የትራፊክ ጉዳት ለመቀነስ በተሽከርካሪዎች ላይ የፍጥነት መገደቢያ መሣሪያ እንዲገጠም መወሰኑን ተከትሎ፣ በፌደራል መንግሥት ፈቃድና የብቃት ማረጋገጫ የተሰጣቸው አቅራቢዎች ለኦሮሚያ ክልል እንዳያቀርቡ የገበያ ገደብ እንደተጣለባቸው ለአዲስ ማለዳ ተናገሩ።

በዚሁ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች የመሰረቱት “ኢትዮ መላ የተሸከርካሪዎች ፍጥነት መገደቢያ መሳሪያ አስመጥቶ መግጠም ዘርፍ ማኅበር” ለአዲስ ማለዳ እንደገለጸው፣ በኦሮሚያ ክልል 17 ሺሕ ተሽከርካሪዎች የፍጥነት መገደቢያ እንዲገጠምላቸው ተወስኖ ከሕግ አግባብ ውጪ ለአንድ ግለብ ተስጥቶ ሌሎቹ በነጻ ገበያ እንዳይሳተፉ ተከልክለዋል ብሏል።

የክልሉ ትራንስፖርት ቢሮ በክልሉ የሚገኙ የተሽከርካሪ ባለንብረት ማኅበራት፣ የፍጥነት መገደቢያ መሳሪያ ከአንድ ግለሰብ ጋር ውል ገብተው እንዲያስገጥሙ ትዕዛዝ በመስጠት ውል እንዲገቡ አድርጓል ተብሏል። ቢሮው ማኅበራቱ ከአንድ ግለሰብ ጋር ውል እንዲገቡ የተደረጉት ዋጋውን ጭምር በመወሰን በማስፈራራት መሆኑን ማኅበሩ ገልጿል።

ከማስፈራሪያዎች መካከል ከተባለው ግለሰብ የፍጥነት መገደቢያ የማታስገጠሙ ከሆነ ወይም ከሌላ አቅራቢ የምታስገጡሙ ከሆኑ የነዳጅ ድጎማ ተጠቃሚ አትሆኑም የሚል እንደሚገኝበትም ማኅበሩ ጠቁሟል።

የቢሮው ውሳኔ በዘርፉ የተሰማሩ የማኅበሩ አባላት በሕግ የሰጣቸውን በነጻ ገበያ ለተጠቃሚዎች የማቅረብ መብት፣ እንዲሁም የተሽከርካሪ ባለንብረቶቹ በነጻ ገበያ በጥራትና ዋጋ አወዳደረው የመግዛት ዕድላቸውን የነፈገ መሆኑን ማኅበሩ ገልጿል።

ማኅበሩ ግለሰቡ ያሰረው ውል እንዲቋረጥና አባላቱ በነጻ ገበያ የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፣ ለኦሮሚያ ክልል ፕሬዝደንት ጽ/ቤት፣ ለትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፣ ለፍትሕ ሚኒስቴር፣ ለፌደራልና ኦሮሚያ ክልል ጸረ ሙስና ኮሚሽን እና ለኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ቅሬታ ለማስገባት ደብዳቤ አዘጋጅቻለሁ ብሏል።

የቴክኖሎጂ አቅራቢዎቹ በኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት የተረጋገጠ ጂፒኤስ የተገጠመለት የፍጥነት መገደቢያ ቴክኖሎጂ፣ መንግሥት በፈቀደላቸው የቀረጥ ነጻ ዕድል በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ አስገብተው የገበያ ዕድሉ በመታገዱ እየከሰሩ መሆኑም ተነግሯል። (አዲስ ማለዳ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: corruption, Ethiopia corruption

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule