ሉዓላዊነት እና አብሮነትን የሚፈታተኑ ሚዲያዎች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን አስታወቀ። የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አንዷለም እንዳሉት አንዳንድ ዓለም አቀፍ የሚዲያ ተቋማት በትግራይ ክልል ላይ የሰሯቸው ዘገባዎች በአጠቃላይ የጋዜጠኝነት ሙያ አስተምህሮ እና ሙያዊ ስነ ምግባር ጥያቄዎችን የሚያስነሱ ናቸው። ሥራዎቻቸው በጣም የሚያስተዛዝቡ እና የሚያበሳጩ ጭምር መሆናቸውን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል። ዓለም አቀፍ ሚዲያውን እና ዘገባው የሰራውን ባለሙያ ለይቶ ማየት ያስፈልጋል ሲሉ አቶ ወንድወሰን ተናግረዋል። አንድ የሚዲያ ተቋም የላከው ጋዜጠኛ ስህተት ሰራ ማለት ሚዲያው ሙሉ በሙሉ ከእውነት፣ ከፍትህ እና ከሀቅ የተፋታ ነው የሚል ድምዳሜ ላይ ለመድረስ እንደማያስችልም አንስተዋል። የተዛቡ ዘገባዎችን … [Read more...] about በዓለምአቀፍ ሚዲያ ዘጋቢዎች ላይ እርምጃ ሊወሰድ ነው
Archives for March 2021
በሲዳማ/ሀዋሳ 128 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥ፤ 2 መትረየስ ከ8,129 ጥይት ጋር ተያዘ
በሲዳማ ክልላዊ መንግስት በግለሰብ ቤት ተከማችቶ የነበረ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር መዋሉን ፌዴራል ፖሊስ ገልጿል፡፡ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ኢንተለጀንስ ዳይሬክቶሬት ከህብረተሰቡ የደረሰውን መረጃ መሰረት በማድረግ ለረጅም ጊዜ ሲከታተል ቆይቶ መጋቢት 5 ቀን 2013 ዓ.ም በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በጭኮ ከተማ አስተዳደር እና በሀዋሳ ከተማ ታቦር ክፍለ ከተማ በርካታ የጦር መሳሪያ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ኢንተለጀንስ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጎሳዬ ለገሰ ገልፀዋል፡፡ በጭኮ ከተማ ላይ በተደረገው ክትትል 30 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥ እና ሁለት መትረየስ የተያዘ ሲሆን፣ በተመሳሳይ ሀዋሳ ከተማ ታቦር ክፍለ ከተማ ፋራ ቀበሌ ልዩ ቦታው ወልደ አማኑኤል ተብሎ በሚታወቅ አካባቢ በሚገኝ የግለሰብ መኖሪያ ቤት ውስጥ የፌደራል ፓሊስ እና የክልሉ ልዩ … [Read more...] about በሲዳማ/ሀዋሳ 128 ቱርክ ሰራሽ ሽጉጥ፤ 2 መትረየስ ከ8,129 ጥይት ጋር ተያዘ
የአክሱም ጅምላ ጭፍጨፋ ተብሎ የተሰራጨው ፎቶ የሐሰት ሆነ
ሰሞኑን በትህነግ የማህበራዊ ሚዲያ ጀሌዎች (ዲጂታል ወያኔ) በአክሱም የተደረገ የጅምላ ጭፈጨፋ ማስረጃ ነው ተብሎ የተሰራጨው ፎቶ የሐሰት ሆኖ መገኘቱ ተገለጸ። በትግራይ አክሱም የተነሳ ነው ተብሎ ሰሞኑን የተሰራጨው ምስል ሐሰተኛ መሆኑን ያረጋገጠው የኢትዮጵያ የአስቸኳይ ጊዜ መረጃ ማጣሪያ ነው። በትግራይ አክሱም የተጨፈጨፉ ሰለባዎች ተብሎ ሃሰተኛ መረጃ ሲሰራጭ የቆየ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ለዚህም ማስረጃ እንዲሆን ከሰሞኑ ከማህበራዊ እስከ ዓለምአቀፍ ሚዲያ በምስል የተደገፈ መረጃ በስፋት ሲሰራጭ መቆየቱ ይታወሳል። ሆኖም በማስረጃ በተደገፈ የተሰራጨው ምስል ሐሰተኛ መሆኑን የኢትዮጵያ የአስቸኳይ ጊዜ መረጃ ማጣሪያ አስታውቋል፡፡ ተቋሙ ባደረገው ማጣራት ፎቶው በኖቬምበር 2020 በናይጀሪያ የተነሳ መሆኑን ማረጋገጡን የኢትዮጵያ የአስቸኳይ ጊዜ መረጃ ማጣሪያ ጨምሮ … [Read more...] about የአክሱም ጅምላ ጭፍጨፋ ተብሎ የተሰራጨው ፎቶ የሐሰት ሆነ
በትግራይ ትምህርት ቤቶች በቅርቡ ሥራ ይጀምራሉ
75% ሆስፒታሎች ሥራ ጀምረዋል የአስቸኳይ ጊዜ አስተባባሪ ማዕከል ዘርፈ ብዙ ምላሽ ሰጪ ብሔራዊ ኮሚቴ ሳምንታዊ ስብሰባውን አካሂዷል፡፡ኮሚቴው በስብሰባው በትግራይ ክልል የአባል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶችን የአስቸኳይ ሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት እንዲሁም የመልሶ ማቋቋም ስራዎች አፈፃፀምን ገምግሟል፡፡በክልሉ ትምህርት ቤቶችን ለመክፈት ዝግጅት መጠናቀቁ እና ትምህርት ቤቶቹን ስራ ለማስጀመርም ከመምህራን እና ወላጆች ጋር ውይይት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል፡፡ትምህርት ቤቶቹ በቅርቡ ስራ እንዲጀምሩ የተወሰነ መሆኑ እና ይህን ለማድረግ አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁስ መሰራጨታቸውም ተመልክቷል፡፡በክልሉ ከሚገኙ ሆስፒታሎች መካከል 75 በመቶ የሚሆኑት ሙሉ በሙሉ እንዲሁም 10 በመቶ የሚሆኑት በከፊል ስራ መጀመራቸው ተጠቅሷል፡፡ለአብነትም ባለፉት 2 ሳምንታት 1,583 እናቶች በነዚሁ ተቋማት አገልግሎት … [Read more...] about በትግራይ ትምህርት ቤቶች በቅርቡ ሥራ ይጀምራሉ
በማይካድራ የጅምላ መቃብር ተገኘ፤ በህወሓት የተገደሉት ቁጥር ከ1300 እንደሚበልጥ ተነገረ
የማይካድራ ከተማ ከንቲባን አቶ ቸሩ ሀጎስ የቀበሌ 01 ሊቀመንበር አብሪሁ ፋንታሁን እና የከተማዋን ነዋሪዎች ጠቅሶ ጌቲ ኢሜጅስ በምስል አስደግፎ ባሰራጨው መረጃ ላይ እንደተገለጸው፤ እአአ ማርች 5/2020 በአቡነ አረጋዊ ቤተክርስቲያን የጅምላ ቃብ ውስጥ ከ1300 በላይ የአማራ ብሄር ተወላጅ የሆኑ ሰዎች አስከሬን ተገኝቷል። የአማራ ብሄር ተወላጅ የሆኑት እነዚሁ ሟቾች ህወሓት ሳምሪ በሚል ባደራጃቸው ወጣቶች፣ ሚሊሻዎች እና በፖሊሶቹ አማካኝነት የተገደሉ መሆኑን ታዋቂው ዓለምአቀፍ ሚዲያ ጌቲ ኢሜጅስ በዘገባው ጠቅሷል። ሟቾቹ በአከባቢው ላሉ ባለሀብቶች በጉልበት ስራ ተቀጥረው የሚሰሩ ንጹሀን መሆናቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ ገዳዮቹ ቤት ለቤት እየሄዱ የአማራ ብሄር ተወላጆችን እየመረጡ ጭፍጨፋውን መፈጸማቸውን ገልጿል። አብዛኛዎቹ ሟቾች በስለታማ መሳሪያዎች ተጨፍጭፈው … [Read more...] about በማይካድራ የጅምላ መቃብር ተገኘ፤ በህወሓት የተገደሉት ቁጥር ከ1300 እንደሚበልጥ ተነገረ
የጃዋር ቅዠትና የበቀለ የተላላኪነት ፖለቲካ – የለማ ሃዲድ መሳት
አቶ በቀለ ገርባ ከእስር ተፈተው አሜሪካ እስከገቡ፣ ከአሜሪካም ሜኖሶታ ከጃዋር ጋር ጫጉል ቆይተው እስኪወጡ የሚናገሩትንና የሚያደርጉትን የሚያውቁ፣ የሚያመልኩትን አምላክ ተግሳጽ መስማት የሚችሉ፣ በዙሪያቸውም ሆነ በሩቅ ባሉ ክብር ያላቸው ፖለቲከኛ እንደነበሩ ስምምነት አለ። ይህ ስምምነት ነበር አቶ በቀለን በኢትዮጵያ ለውጥ ቢፈጠር ሁሉንም አቻችለው ወደ በጎ መንገድ እንዲመሩ ከሚታሰቡት መካከል ቀዳሚው አድርጓቸው የነበረው። የዲሲ ነዋሪው ገመቹ በቀለ ከሜኖሶታ "ተሃድሶ" ይለዋል ተመርቀው ሲወጡ "የአንጎል ቀዶ ጥገና ተድርጎላቸዋል" ባይ ነው። የዘወትር የጎልጉል አስተያየት ሰጪ ገመቹ እንዳብራራው አቶ በቀለ ጃዋር በዝግ ቤት ከሰው ለይቶ ቀዶ ጥገና ካደረጋቸው በኋላ ሙሉ በሙሉ ሌላ የማይታወቁ ሰው ሆኑ። "በቀለ ይፈታ" እያሉ ሲጮሁ የነበሩ ወገኖችን ከነ ባንዲራቸው … [Read more...] about የጃዋር ቅዠትና የበቀለ የተላላኪነት ፖለቲካ – የለማ ሃዲድ መሳት
የኬሪያና የጃዋር ድብቁ ግንኙነትና አዲሱ የቤት ውስጥ እስር
የቀድሞ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የነበሩት ወ/ሮ ኬሪያ በዋስ መፈታታቸው ተሰምቷል። ፖሊስ ለችሎት እንዳስረዳው ወይዘሮዋ የተፈቱት ቀዳሚ ምርመራ እስኪሰማ ድረስ በወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ አንቀጽ 28 መሰረት ነው። ፋና ችሎቱን ጠቅሶ እንደዘገበው ወይዘሮ ኬሪያ ቀዳሚ ምርመራ እስከሚሰማ ድረስ የሚቆዩት በሰርቪስ ማረፊያ ነው። የህግ ማስከበሩ ሲጀመር ሌሎች ሲሸሹ መቀሌ ሆነው እጃቸውን የሰጡት የቀድሞ አፈ ጉባኤ፤ እጃቸውን ከሰጡ በኋላ ክስ ሳይመሰረትባቸው መቆየቱ ይታወሳል። ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም እንዴት ወደ መቀሌ ሄዱ? አፈጉባዔዋ ወደ መቀሌ የሄዱት ከአዲስ አበባ ተገፍተው መሆኑንን ጉዳይን በወጉ ሲከታተሉ የነበሩ ይናገራሉ። ኬሪያ ሃላፊነታቸውን በገዛ ፈቃዳቸው መልቀቃቸውን ከማስታወቃቸው በፊት ከአቶ ጃዋር ጋር ጥብቅ ግንኙነት እንዲመሠርቱ … [Read more...] about የኬሪያና የጃዋር ድብቁ ግንኙነትና አዲሱ የቤት ውስጥ እስር
UNDP Memo Echoes Ethiopian Talking Points on Tigray
The United Nations’ top development agency said in a memo to U.N. Secretary-General António Guterres that leadership in Ethiopia’s Tigray region deserves much of the blame for provoking the federal government’s bloody offensive against the Tigrayans, appearing to suggest that a military crackdown that has driven half a million people from their homes and fueled allegations of mass atrocities may have been justified. The confidential memo—signed by Achim Steiner, the administrator of the U.N. … [Read more...] about UNDP Memo Echoes Ethiopian Talking Points on Tigray
የልደቱ፤ የትህነግ እና የነጃዋር መጨረሻ
ትህነግ ወደ ከርሰ መቃብር፤ ጃዋር ወደ ከርሱ፤ ልደቱ ወደ ዕረፍቱ በስተመጨረሻ “መንግስት የለም” የሚለውን ትግል ተቀላቅለው የነበሩትና፣ ትህነግ ባስቀመጠው የትግል ስልት የማስተባበር ስራ ሲሰሩ እንደነበር በመግለጽ ክስና ወቀሳ ሲሰነዘርባቸው የነበሩት አቶ ልደቱ አያሌው በድንገት ከፖለቲካ በበቃኝ መገለላቸው ተሰማ። ውሳኔያቸው ከትህነግ ህልውና መክሰማና ከነ ጃዋር ምግብ መብላት መጀመር ጋር መያያዙ ውሳኔያቸውን የተስፋ መቁረጥ አስመስሎባቸዋል። ልደቱ አያሌው በቅርቡ ተከሰው በነበሩበት ወቅት የተገኘባቸውን ሽጉጥ ከደህንነት መስሪያ ቤት የተሰጣቸው መሆኑንን መግለጻቸው፣ በደህንነት መስሪያ ቤት ውስጥ በሂሳብ መዝገብ ወጪ እየተደረገ ደሞወዝ ይከፈላቸው እንደነበር ይፋ መሆኑ “ቀድሞም ትህነግ ነበሩ” የሚለውን ወቀሳ አጠናክሮባቸው ነበር። ቀደም ሲል ህግ ተጥሶም ቢሆን ምርጫ … [Read more...] about የልደቱ፤ የትህነግ እና የነጃዋር መጨረሻ