• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የልደቱ፤ የትህነግ እና የነጃዋር መጨረሻ

March 10, 2021 10:09 am by Editor 7 Comments

ትህነግ ወደ ከርሰ መቃብር፤ ጃዋር ወደ ከርሱ፤ ልደቱ ወደ ዕረፍቱ

በስተመጨረሻ “መንግስት የለም” የሚለውን ትግል ተቀላቅለው የነበሩትና፣ ትህነግ ባስቀመጠው የትግል ስልት የማስተባበር ስራ ሲሰሩ እንደነበር በመግለጽ ክስና ወቀሳ ሲሰነዘርባቸው የነበሩት አቶ ልደቱ አያሌው በድንገት ከፖለቲካ በበቃኝ መገለላቸው ተሰማ። ውሳኔያቸው ከትህነግ ህልውና መክሰማና ከነ ጃዋር ምግብ መብላት መጀመር ጋር መያያዙ ውሳኔያቸውን የተስፋ መቁረጥ አስመስሎባቸዋል።

ልደቱ አያሌው በቅርቡ ተከሰው በነበሩበት ወቅት የተገኘባቸውን ሽጉጥ ከደህንነት መስሪያ ቤት የተሰጣቸው መሆኑንን መግለጻቸው፣ በደህንነት መስሪያ ቤት ውስጥ በሂሳብ መዝገብ ወጪ እየተደረገ ደሞወዝ ይከፈላቸው እንደነበር ይፋ መሆኑ “ቀድሞም ትህነግ ነበሩ” የሚለውን ወቀሳ አጠናክሮባቸው ነበር።

ቀደም ሲል ህግ ተጥሶም ቢሆን ምርጫ መደረግ እንደሌለበት ሲሞግቱ የነበሩት አቶ ልደቱ፤ ትህነግ መቀሌ ሆኖ “ከመስከረም 30 በኋላ ቅቡል መንግስት የለም” የሚል አዋጅ ካሰማ በኋላ “ የሽግግር መንግስት ይቋቋም” በሚል የመሃል ፖለቲካውን ለመምራት ከነ ጃዋር መሐመድ ጋር ግንባር ገጥመው እንደነበር ይታወሳል። በወራት እድሜ ውስጥ ለተቀያየረው አቋማቸው በወጉ ተጠይቀው ምክንያታቸውን ሲያስረዱ ያልተሰሙት አቶ ልደቱ፣ ባሰራጩት ሰፊ ጽሁፍ ራሳቸውን ከፖለቲካ ማሰናበታቸውን አስታውቀዋል።

“በመጨረሻም ከአቅም በላይ በሆነ የጤና ምክንያት ቢሆንም ሀገራችን ከመቼውም ጊዜ በላይ ዋጋ የሚከፍልላት ዜጋ በሚያስፈልጋት በአሁኑ ወቅት ለጊዜውም ቢሆን ከትግል ተሳትፎዬ ለመታቀብ በመገደዴ፥ የትግል አጋሮቼንና የዐላማ ደጋፊዎቼን ሁሉ ከልብ ይቅርታ እጠይቃለሁ” ያሉት አቶ ልደቱ፣ ስንብቱን የመረጡት በጤና እክል የተነሳ ነው ብለዋል።

ሆኖም በእስር በነበሩ ጊዜ የልብ በሽታ እንዳልባቸውና ውድ አሜሪካ ለመሄድ እያሉ መታሰራቸው አገባብ አይደለም በማለት የፓርቲ ሰዎቻቸው መንግሥትን ሲሞገቱ ነበር። በእስር እያሉ የጤና ዕክል ቢገጥማቸው መንግሥትን ተጠያቂ እንደሚያደርጉ ሲናገሩ ነበር። ሆኖም አቶ ልደቱ ከእስር ከተለቀቁ ወራት የተቆጠሩ ቢሆንም ለልብ ሕክምና ወደ ውጭ እስካሁን እንዳልሄዱ ይታወቃል። ከዚያ ይልቅ የሚለውን መጽሃፋቸውን በማሳተም ተጠምደው እንደ ነበር ይታወቃል።

“… ከእኔ ብዙ እንደምትጠብቁና ለእኔ ለራሴ እንደሆነብኝ ሁሉ ለእናንተም ይህ ክስተት ድንገተኛ መርዶ እንደሚሆንባችሁ ስለምገነዘብ ነው። ወደፊት የጤና ሁኔታዬ ተሻሽሎ እስከመጨረሻው በፖለቲካ ሒደቱ ለመቀጠል ለራሴ የገባሁትን ቃል ለመፈጸም ፈጣሪ ዕድል እንደሚሰጠኝ ተስፋ እያደረግኹ ሀገራችን ኢትዮጵያ መልካሙ ሁሉ እንዲገጥማት ያለኝን ልባዊ ምኞት በዚህ አጋጣሚ እገልጻለሁ” ሲሉ ደብዳቤያቸውን የቋጩት አቶ ልደቱ፣ እሳቸው በሚሉት ደረጃ ለኢትዮጵያ ወሳኝና ለዘመኑ ቀውስ መድሃኒት የሆኑ ዜጋ ስለመሆናቸው የሚያሳይ ታሪካቸው ለማሳያነት አልጠቀሱም።

በጽሁፋቸው ኢትዮጵያ በኤርትራና በሱዳን መወረሯን አንስተው “ይህ የመበታተን ምልክት ነው” ብለዋል። የኢትዮጵያ ጦር ላይ ክህደት ተፈጽሞ በተኛበት መጨፍጨፉን አጉልተው ሲነቅፉ ያልተሰሙት አቶ ልደቱ ዛሬም ኤርትራን ወራሪ አድረገው መሳላቸው አግራሞትን ፈጥሯል።

“ከሞት የተረፈው የኢትዮጵያ ጦር እርቃኑንን በርሃብና በውሃ ጥም ተሰቃይቶ ኤርትራ ሲገባ ነብስ እንዲዘራና ሃፍረተ ሰውነቱን እንዲሸፍን ያደረጉት የኤርትራ ሰራዊትና መንግስት ናቸው” በሚል የአገር መከላከያ ሰራዊት አባላት የደረሰባቸውን ግፍ በተናገሩት መጠንና ህዝብ ቁጣውን በገለጸበት ልክም ባይሆን አቶ ልደቱ ለትህነግ ወግነው መቆማቸው ደጋፊ አልባ አድርጓቸዋል እየተባለ ነው። በተለይ ከእስር ሲፈቱ ከእስርቤት ደጅ ጀምሮ ይሆናል ብለው የጠበቁትን የሕዝብ ድጋፍ ባለማግኘታቸው ፖለቲካቸው ድጋፍ እያጣ ለመሆኑ የማነቂያ ደወል እንደሰጣቸው በቅርብ ያሉ ሰዎች ይናገራሉ።

ተወለድኩበት የሚሉት አካባቢ ሳይቀር በዚሁ ከትህነግ ጋር ያላቸው ትሥሥር ያስከተለባቸው ጥላቻ ድጋፍ እየነሳቸው መሆኑንን በመረዳታቸው ከጤና ችግራቸው ጋር አዳምረው ከፖለቲካው ዓለም ለመሰናበት መወሰናቸውን ከጽሁፋቸው ግርጌ አስተያየት የሰጡ አስታውቀዋል። “ሲሻለኝ እንደምመለስ ተስፋ አደርጋለሁ” ያሉትን አስመክልቶ “አቶ ልደቱ አሁን የደበዘዘውና የሰከነው የውስጡ ፖለቲካ ሲጋጋል እንደሚሻላቸው አመላካች ነው” የሚል ሽሙጥ ቢጤ አስተያየት ተሰጥቶበታል። በመረጋጋት ላይ ያለው ፖለቲካ ባንድ ጊዜ መጦዝ ቢጀምርና ትርምስ ቢከሰት ልደቱ በፊትአውራሪነት ብቅ እንደሚሉ በርግጠኝነት አስተያየት የሰጡም አሉ።

አቶ ልደቱ “የትግራይ ህዝብና ትህነግ አንድ ናቸው” በሚል ድምዳሜያቸው ይታወቃሉ። በዛሬ የመለያያ ጽሁፋቸው መንግስትን ለአንዴና ለመጨረሻ በሚመስል መልኩ ደብድበዋል። ህገ መንግስቱ እንዲቀየር ጥሪ አቅርበዋል። የህገመንግስት ረቂቅና አፈጻጸም መጽሃፍ እያዘጋጁ ስለሆነ ተቃዋሚዎች እንደ ሰነድ ተጠቅመውበት የመታገያ አጀንዳቸው እንዲያደርጉት ታቦት ሳይጠሩ ተማጽነዋል። በተዘዋዋሪ ቀጣዩ መጽሃፌን ግዙ ብለዋል።

የትህነግ መክሰም በኢትዮጵያ በርካታ ችግሮችን አብሮ እንደሚያከስም በፖለቲካው ዙሪያ ያሉ አስተያየት ሰጥተዋል። በርካታ ደጋፊዎቻቸውም ተስፋ እንደሚቆርጡ አመልክተዋል።

ሌላው የተነሳው ጉዳይ አቶ ልደቱ ከፖለቲካ መሰናበታቸውና የእነ ጃዋር መሐመድ ምግብ መጀመር ግጥምጥሞሽ ነው። አቶ ልደቱ “ከመስከረም ሰላሳ በኋላ መንግስት የለም” የሚለውን ዘመቻ ሲቀላቀሉ ከነ ጃዋር ጋር ገጥመው የነበረ መሆኑንን፣ በኦሮሞ ሚዲያዎች ላይ ከጃዋር ጎን በመሆን በህብረት ዘመቻውን ማራመዳቸውን ያታወሱ፣ ሁሉም ነገር ማክተሙና እነ ጃዋርም ምግብ ለመብላት መወሰናቸው አቶ ልደቱን አዲስ የሚጠበቅ ተስፋ አሳጥቷቸዋል። በዚህም የተነሳ ስንበቱን ለጊዜውም ቢሆን መርጠዋል የሚሉ አስተያየቶች ተሰምተዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ጃዋር “የአንድነት ሃይሎች ከዱኝ” መናገሩን አስመልክቶ ከዚህ በፊት የዘገበው እዚህ ላይ ይገኛል። (ethio12.com)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics

Reader Interactions

Comments

  1. ነፃ ሕዝብ says

    March 10, 2021 01:48 pm at 1:48 pm

    ሠላም ጎልጎሎች ፦ ዝንጀሮ የቂጧ መላጣ አይታያትም ይባላል ፥ እናንተም የፋሽስታዊና አፓርታይዳዊ ኦሮሙማው አገዛዝ ቁንጮ ከሆነው ግራኝ አህመድ አሊ ጀምሮ የነፍሰ_ገዳዩ ህወሃት ሎሌዎችና ተላላኪዎች እንዳልነበራችሁ ልደቱን እንደ ሰይጣን አድርጋችሁ ትቆጥሩታላችሁ ፥ ለፋሽስቱና ነፍሰ_ገዳዩ ህወሃት ከልደቱ በበለጠ እናንተ አልነበራችሁም እንዴ የምትቀርቡትና አገልጋይ የነበራችሁት ? ጎልጉሎች ኢትዮጵያ ውስጥ መንግሥት አለ ብላችሁ ተቃዋሚውን ስታብጠለጥሉ በእጅጉ ትገርማላችሁ ፥ በአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የፋሽስቱና አፓርታይዳዊ አገዛዝ ብሎም ነፍሰ_ገዳዩ ኦሮሙማ መሆኑን የዓለም ሕዝብ የሚያውቀው ሃቅ ነው ፥ ጎልጎሎች በምሥራቅ ወለጋ በየቀኑ የሚገደለውን አማራ ይታያችሁዋልን ? እናንተ የነፍሰ_ገዳዩና ዘረኛው የአብይ አህመድ አሊ አለቅላቂዎች ናችሁ ፥ ባለፈው ጊዜ ለአብይ ወግናችሁ እውቁ የፖለቲካ ተንታኝ የሆነውን ኤርምያስ ለገሰን ስታብጠለጥሉት ነበር ፥ በፍጹም ሃፍረት የማይሰማችሁ ጉደኞች ናችሁ ፥ በኢትዮጵያ ውስጥ ማንም ፖለቲከኛ ነኝ የሚል ሁሉ ቢጨፈለቁ አንድ ልደቱ አያሌውን የሚያህል አይኖርም ፥ ልደቱ ያነበበ እና ወቅቱን ያገናዘበ እውቅ ፖለቲካኛ ነው ፥ ለህክምና ወደ አሜሪካ እንዳይሄድ የከለከለው የእናንተው ነፍሰ_ገዳዩ አብይ መሆኑን እያወቃችሁ በመጽሐፍ ሽያጭ ላይ ተጠምዶዋል ትሉታላችሁ ፥ መጽሐፍ የሚፅፍ ጭንቅላት ያለውና እውቀት ያለው እንጂ እንደ እናንተ ያለው ዲጂታል የኦሮሙማው ተቀላቢ አይደለም ፡፡

    Reply
    • Sule says

      March 10, 2021 05:51 pm at 5:51 pm

      ትክክል!!

      Reply
  2. አሌክስ says

    March 10, 2021 07:48 pm at 7:48 pm

    ልደቱ ከሞተ ሰንብቶል. ዛሪ ሰለሞተ ግለሰብ መፃፍ ወይም ግዜ ማባከን ተገቢ አይደለም. አሁን ሐገራችንን ለመከፋፈል የሚፈልጉ ጠላቶቻ ችንን በመዋጋት ግዜአችንን እንጠቀም.

    Reply
  3. We ana Anaa says

    March 12, 2021 09:11 am at 9:11 am

    Selabi bet buda geba!! Lidetu ( aselchi achberbary polotikegna)
    Please lidetu don’t try to go to dedebit it should be enough to you here!

    Reply
  4. Shewa rega says

    March 12, 2021 02:39 pm at 2:39 pm

    ትክክል ብልሀል አሌክስ እንዴት የሞተ ሬሳ ለማንቀሳቀስ ይሄ ሁሉ ሽርጉድ ??!!!

    Reply
  5. Tesfa says

    March 13, 2021 08:56 pm at 8:56 pm

    የሃበሻው ፓለቲካ ሸፋፋና ገዳዳ ነው፡፡ አንድም ቀን ሞልቶለት አያውቅም፡፡ ወፌ ቆመች ሲባል ተመልሶ በአፍ ጢሙ የሚደፋ፤ የቀደመው ያቆመውን የቀኑ አለቃ የሚንድበት በዙር የመገዳደል ፓለቲካ ነው፡፡ አቶ ልደቱ ወያኔና የትግራይ ህዝብ አንድ ናቸው ማለቱ ወደውም ሆነ ተገደው የትግራይ ህዝብ 45 ኣመት ሙሉ ወያኔን ተሸክሞት ኖሯል፡፡ አሁንም የወያኔን ሞት ቀድመው ያወጅ ሁሉ ቢላሾች እንደሆኑነ ቀን ያሳየናል፡፡ ወያኔ በተንኮልና በማፍረስ ሥራ የተካነ ድርጅት ነው፡፡ ያው ዛሬም ጠበንጃ ይዞ ዘጥ ዘጥ ማለቱ አይቀሬ ነው፡፡ በመሰረቱ ወያኔ ማለት ከጀርመኑ ናዚ፤ ከጣሊያኑ ሞሶሎኒና ግራዚያኒ የሚስተካከል የጨካኞች ስብስብ ነው፡፡ ይህ ደግሞ የሰሩትና የሚሰሩት መሰሪ ሥራ የሚመሰክረው በዘራቸውና በቋንቋቸው የሰከሩ ታላቋን ትግራይ ለመመስረት ታስቦ ለ 27 ኣመታት በሰፋ ዳቦ ተታለው ምድሪቱን ሲመዘብሩ ኑሮው መቀሌ ከተሰባሰቡ በህዋላ ለውጊያ ሲዘጋጅ እንደ ነበር በሰሜን እዝ ላይ ያደረሱት “መብረቃዊ ጥቃት” ዛሬ ላለንበት ቀን አድርሶናል፡፡
    አሁን በሱዳን በገዳሪፍ ግዛት ከሱዳንና ከግብጽ ሃይሎች ጎን ተሰልፈው እንደገና ለመፋለም ወደ 80 ሺህ ጦር እንዳዘጋጅ ይነገራል። የኢትዮጵያን አንድ መሆን ከሚጠሉ ነጮችና የአረብ ሃገሮች ጋር ዳግመኛ በመቆራኘት የሌለ ነገር ሆነ እያሉ ከፍለው በማሳመንና አልፎ ተርፎም የዘር ማጥፋት ተፈጸመብን በማለት መጮሃቸው ምን ያህል የዲፕሎማሲ ስራቸው ሥር የሰደደ መሆኑን ያሳያል። እነ ስዬ አብርሃ በእርጅና ሱዳን ጠረፍ የወሰዳቸው ያ በፊትም ከከተማ ወደ ጫካ የወሰዳቸው የዘር ፓለቲካ እንጂ ለሰው ልጆች ሰላምና ልዕልና ወያኔዎች አንድም ቀን አስበው አያውቁም። ያልገባቸው ነገር ግን መለስ ብሎ የሃበሻውን ፓለቲካ ላየ በዙር መገዳደል እንጂ የብሄር ነጻነት ፈላጊዎች ባርነትን እንጂ ነጻነትን አመንጭተው አያውቁም። ዛሬም ውጊያ፤ ነገም ተነሱ፤ ሞትና ለቅሶ ለጥቂቶች ተድላና ደስታ እልፎች የሚሞቱባት ሃገር ኢትዮጵያ ብቻ ናት። ጃዋር፤ ልደቱ እና ወያኔ በሃሳብ ተስማሙ ከተባልን ለማፍረስ እንጂ ሃገር ለማቆም እንዳልሆነ የታወቀ ነገር ነው። ዛሬ በኦሮሚያ ክልልና በሌሎችም የሃገሪቱ ምድር ሰው የሚሸራከተው በክልል ዙሪያ በሚነሳ የብሄር ግጭት ምንጩ አዲስ አበባ ላይ ቁጭ ብለው ሰው እንዲገዳደል አይዞአችሁ የሚሉ ሁሉ ናቸው። ገዳዪ ተከፋይ፤ ከሞት የተረፈው ተፈናቃይ ከሆነ ዘመን አልፎ እያለ አውሮፓና አሜሪካ በትግራይ የአዞ እንባ ሲያፈሱ ማየት ለጤና እንዳልሆነ የሰነበተ ያየዋል። የአለም ፓለቲካ ከቀዝቃዛው ጦርነት ወዲህ በሃያላን መንግስታትና በተለጣፊ ሃገሮች መካከል ያለው ግብግብ በረድ ያለ ቢመስልም የሚናቆሩበት ጉዳይ አጥተው አያውቁም። ሊቢያ፤ የመን፤ ኢራቅ፤ ሶሪያና ሌሎችም ሃገሮች በእነዚህ ሃይሎች ተፈረካክሰው በመንገዳገድ ላይ ይገኛሉ። አሜሪካ ማለት ሳውዲ አረቢያ ውስጥ ያለውን የሰው ልጆች ጭቆናና ግፍ በነዳጅ ዶላር ሸፍኖ የመን ከምድርና ከሰማይ እንድትደበደብ ስንቅና ትጥቅ የሚያቀብል መንግሥት ነው። ዞሮ ተመልሶ ደግሞ ለተራበ ስንዴ ያቀብላል። ይህን እንዴት ቆሞ የሚሄድ ሰው መረዳት ይሳነዋል? ለኢትዪጵያም የታለመላት ማፈራረስ ነው። ጣሊያን በመርዝ ጋዝ ህዝባችን ሲያጠቃው ቆመው ያዪ ሃገራት ናቸው ዛሬም ከወያኔ ጎን ቆመው ኡኡታ የሚያሰሙት። ይህ ግን ለትግራይ ህዝብ አዝነው ሳይሆን የቆመው ሁሉ ዶጋ አመድ ሆኖ እነርሱ ነፍስ አትራፊ ሆነው ለመታየት ነው።
    የዶ/ር አብይ መንግስትና አረማመድም ከቀን ወደ ቀን እየተወላገደ ሄዷል። ወንጀል የሰሩ ሰዎችን እየለቀቁ ያለ ምንም መረጃ ሌሎችን ጨለማ ውስጥ ማጎሩ ወያኔያዊ ነው። ለነገሩ ጠ/ሚሩ ቢሆን ከወያኔ የክፋት ጆኒያ አፈትልኮ የወጣ አይደል። ሰው ደንዝዟል። ሰው ሞተ ሲባል ተዳረ የሚሉት ይመስለዋል። ለነገሩ ዘሩ ተጠይቆ ለቅሶ በሚደረስበት ምድር የሰው ሰውነቱ ከሞተ ቆይቶ የለ። ብቻ የዓረብና የነጭ ተላላኪዎች፤ ወገናችን ተጸያፊዎች ሆነን የት ነው የምንደርሰው? አሁን ማን ይሙት ኢትዮጵያ ያለ ትግራይ ኖሯ ታውቃለች? ትግራይ ያለ ኢትዮጵያስ የሚተርፋት ምንድን ነው? የጅል ፓለቲካ ያዘው ጥለፈው ነው። ሁሌ መኮነን፤ ሁሌ ያልተረጋገጠ ነገር መለጣጠፍ በሰው ደምና ህይወት መነገድ የቀኑን በይ ሌላ በላተኛ ሲበላው ያ ኡደቱ ይቀጥላል። ማነህ ባለሳምንት? ተነሳና ቁም! ቆይተን እንይ። በቃኝ!

    Reply
  6. ነፃ ሕዝብ says

    March 15, 2021 12:05 pm at 12:05 pm

    አንዳንድ ጊዜ ሆድ ሲሞላ ህሊና ይታወራል ይባላል ፥ የብልፅግና ካድሬዎች የፋሽስቱ ህወሃት ግልባጭ የሆነው አፓርታይዳዊ አገዛዝ ኦሮሙማው ሲነካባቸው የማይዘላብዱት መዓት የለም ፥ ምክንያቱም መሬት ሻጭ ካድሬ ሳይሰራ ምላሱን እየቆላ በገፍ የሕዝብ ገንዘብ ስለሚከፈለው ለሥርዓቱ ዐይንና ጆሮ ሆኖ ያገለግላል ፥ ካድሬ የሕዝብን ቆዳ ገፎ የሚያስቀር ከሃዲ ነው ፥ ካድሬ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሲቃይና የመጀመሪያ ተጠያቂ መሆኑ ይታወቃል ፥ በየሥርዓቱ ካድሬ የሚሆኑ እውቀት የሌላቸውና ፍጹም ሆዳሞች ሲሆኑ የሕዝብ እልቂትና እንግልት የማይሰማቸው ከርሳሞችና ውሸታሞች ናቸው ፥ ትናንት የገዳዩና ፋሽስቱ ህወሃት ካድሬዎች የነበሩ ዛሬ ተገልብጠው ለተረኛው ዘረኛና ነፍሰ_ገዳይ ብሎም ፋሽስት ኦሮሙማው አፓርታይዳዊ አገዛዝ ህሊናቸውን ሸጠው ይህንንም ገዳይና አስገዳይ ሥርዓት ለማስቀጠል ፋሽስቱ ኦሮሙማው የሚጠላውን ሁሉ እየተከተሉ ሲያብጠለጥሉና ሲያራክሱ ይታያሉ ፥ ያም ሆነ ይህ የአብይ ሥርዓት በአፍጢሙ ሲደፋ እናንተም አብራችሁ ትደፏታላችሁ @

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule