ኦነግ አወዛጋቢ ማንነቱና ያልረጋ የፖለቲካ ሩጫው ዛሬም መነጋገሪያ ሆኗል። ቀደም ሲል ለኦሮሞ ትግል እንደ አንድ ብቸኛና ልዩ ምልክት ተደርጎ የተወሰደው ኦነግ በአራት ጎራ ተከፍሎ ቢቆይም አገር ቤት ከገባ በኋላ አንድ መሆን አልቻለም። በኤርትራ በረሃ እያለ እርስበርስ ጎራ ለይቶ በጥይት የተጫረሰው ኦነግ፣ በአውሮፓና በአሜሪካ ባሉ የተለያዩ አመራሮቹ የስልጣን ሽኩቻ አንድ መሆን አቅቶት ሁለት ዐሥርተ ዓመታት አስቆጥሮ አሁን አገሪቱ ውስጥ በተፈጠረው የፖለቲካ ለውጥ ሁሉም አካላት ወደ አገር ቤት ቢገቡም ልዩነታቸውን ማስወገድ አልቻሉም። ዳውድ ኢብሣ (ፍሬው ማሾ)፣ አባ ነጋ፣ ገላሳ ዲልቦና ጄኔራል ከማል ገልቹ የተቀራመቱት ኦነግ አራት መልክ ይዞ ወደ አገር ቤት ሲገባ ሕዝብ ጥያቄ ያነሳው “ለምን አንድ አትሆኑም? አንድ ሁኑና ኑ” የሚል ነበር። እነዚህ አራት ክንፎች እንኳን … [Read more...] about የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል
Archives for February 2020
በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች
በቡራዩ የተከሰተውን ረብሻ አስመልክቶ ቢቢሲና የመንግሥት ሚዲያዎች የተሟላ መረጃ አለማቅረባቸውን የቡራዩ ነዋሪዎች ለጎልጉል ገለጹ። እነሱ እንዳሉት በአንድ መጠነኛ ሆቴል ምረቃ ላይ ለተነሳው ጸብ መነሻው በሽብር ተግባሩ የሚታወቀውና ጃል ማሮ (ኩምሣ ድርባ) የሚባለው የኦነግ ሸኔ ሽፍታ መሪ ፎቶ በጨረታ እንዲሸጥ መቀረቡን ተከትሎ ነው። ነዋሪዎቹ ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ሲያስረዱ በምረቃው ላይ ጃል ማሮን የሚያወድሱ ሙዚቃዎች በዝተው ነበር። የውዳሴው ሙዚቃ መብዛቱ ከቡራዩና አካባቢው ወይም በተለምዶ የ“ሸዋ” የሚባሉትን ኦሮሞዎች አላስደሰተም። ሙዚቃው ቅይጥ እንዲሆን ቢጠየቅም ሰሚ አልነበረም። “በዚህ ስሜት ውስጥ እያሉ ነው ጃል መሮ የሚባለው የኦነግ ሸኔ ሽፍታ መሪ ምስል ለጨረታ የቀረበው” ሲሉ በስፍራው የነበሩ ምስክሮች ያረጋግጣሉ። አክለውም “የዚህን ጊዜ ንትርክ ተነሳ። … [Read more...] about በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች
“ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው
በኦሮሚያ ክልል አዲስ የተነሳው የፍረጃ ፖለቲካ የኃይል አሰላለፉን እንደቀየረና በርካታ የክልሉን ተወላጆች እያሳሰበ መሆኑ ተገለጸ። አካሄዱ ወደ ዘር ማጽዳት ለሚደረገው ድብቅ ጉዞ አመላክች ተደርጎ ሊወሰድ እንደሚችል አስተያየት እየተሰጠ ነው። ሲጀመር “ዲቃላ” የሚለው ፍረጃ በድንገት የተሰነዘረው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን ስም በማንሳት ነው ቢባልም አቶ በቀለ ገርባ ቀደም ብለው ለዚህ አካሄድ ፍንጭ መስጠታቸውን ስጋት የገባቸው ለጎልጉል እንደመነሻ ያነሱታል። “ከሌሎች ብሔረሰቦች ጋር አትጋቡ፣ አትነግዱ” ሲሉ ዲስኩር ያደረጉት አቶ በቀለ ገርባ ይህ ንግግራቸው በወቀቱ ከፍተኛ ተቃውሞ አስነስቶባቸው እንደነበር ያወሱት እነዚህ ክፍሎች፣ ይህንኑ መርዘኛ ቅስቀሳ ለማስተባበል ጃዋር መሐመድ የሚመራቸው ሚዲያዎች በዘመቻ መልክ መትጋታቸውን ያክላሉ። በወቅቱ በፕሮፓጋንዳ ብዛት ነገሩ … [Read more...] about “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው
“ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ
“በየቦታው የሚፈጠሩ የወንጀል ድርጊቶች ዋነኛ ችግር የፖለቲካ አመራሮች እጅ” አለበት ጠቅላይ አቃቤ ሕግ በኢትዮጵያ የሕግ የበላይነትን ለማስከበር የተወሰዱ እና ሊወሰዱ ይገባቸዋል ስላላቸው እርምጃዎች የካቲት 5፣ 2012 መግለጫ አውጥቷል። በየቦታው የሚፈጠሩ የወንጀል ድርጊቶች ዋነኛ ችግር የፖለቲካ አመራሮች እጅ እንዳለበት የገለጸው መግለጫ ለሀገሪቱ ደህንነትና ለህዝቡ ህልውና ሲባል ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን እንደማይታገስ አቋም መያዙን ይፋ አድርጓል። የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦ ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተሰጠ መግለጫ የሕግ የበላይነትን ማስከበር ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም የኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የፍትህ ስርዓቱን የማጠናከርና የህግ የበላይነትን የማክበርና የማስከበር ተግባሩን … [Read more...] about “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ
“እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ
በዚህ ሳምንት መጀመሪያ አካባቢ ከጅማ ዞንና ከከተማዋ የተውጣጡ የተለያዩ የማህበረሰብ አካላት የተሳተፉበትና በህዝቦች አብሮነት እሴት ላይ ትኩረቱን አድርጎ በተዘጋጀው መድረክ ላይ ተሳታፊዎች ምን አሉ? የህዝቡን አብሮ የመኖር እሴት የሚሸረሽሩ ተግባራት ተነቅፈዋል። የኦሮሞ ህዝብ በሰላም የመኖር እሴትና አኩሪ ባህል እንዳለው ተብራርቷል። በመሰዳደብ፣ ጥላቻና ነቀፋ ላይ ያተኮሩ ተግባራትን ሊወገዙ እንደሚገባቸው ሀሳብ ተሰጥቷል። ህዝቡን እንወክላለን የሚሉ አካላት እየተፈፀሙ ያሉ የህዝቡን አብሮነት እሴት የሚሸረሽሩ ተግባራት ተወግዘዋል። የተወሰኑ የውይይት ተሳታፊዎች ሀሳብ፦ "ከየትኛውም ብሄርም ይሁን ሃይማኖትም ይሁን ክልል ተንኮል የሚያስብ ሰው የትም አይደርስም። በመሳደብ የሚመጣ ለውጥ የለም።" "አዋቂና ለኦሮሞ ተስፋ ናቸው ከምንላቸው ሰዎች … [Read more...] about “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ
“ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች
የሙያው ባለቤቶችና ተመራማሪዎች ታጋቾችን ማስለቀቅ ራሱን የቻለ ታላቅ ጥበብና ስልት ይጠይቃል ይላሉ። የአጋቾችን ስነልቡና ለመስረቅ፣ ለማለስለስ፣ ወዘተ አደራዳሪዎች ፈጽሞ ሊታሰቡ የማይችሉ የሚባሉ ዘዴዎችን ሲጠቀሙ ይስተዋላሉ። የአጋቾቹን ፍቅረኛ ወይም እናት ወይም ሌላ ተወዳጅ የቤተሰብ አባል ወደ ዕገታው ቦታ በማምጣት በድምጽ ማጉያ የተማጽንዖ ቃል እንዲናገሩ ይደረጋሉ። የሃይማኖት መሪዎች፣ ሽማግሌዎች፣ ሌሎች ተጽዕኖና አመኔታ ሊጣልባቸው የሚችሉ ሰዎች በዚህ እንዲሳተፉ ይደረጋል። ይህንና ሌሎች መሰል ተግባራትን በመጠቀም የታገቱት ያለ አንዳች ችግር በነጻ እንዲወጡ ሙከራ ይደረጋል። በዚህም ምክንያት ረጅም ጊዜ የሚወስድ ዕገታ በሰላም የመጠናቀቅ ዕድሉ በጣም ከፍተኛ ነው ይባላል። ማፈን፣ ማገት፣ ሰዎችን ያለፈቃዳቸው በቁጥጥር ሥር ማዋል፣ ወዘተ ያልተለመደ ተግባር … [Read more...] about “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች
“ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል”
የዚህች ሃገር ችግር የሴራ ፓለቲካ ነው። ጀዋር ሞሃመድ ዛሬ (ሰኞ) ለማየት የሚሰቀጥጥ አንድ ቪዲዮ ለጠፈ። በጣም አንጀት የሚበላ ጥቁርም ሆነ ነጭ ኦሮሞም ሆነ አማራ፤ የሰውን ልጅ እንደዛ በጭካኔ ማሰቃየት ከባድ የሰብዓዊነት ጥሰት ነው። የህግ ተጠያቂነት ደግሞ ግድ ነው፤ ግን ደግሞ ማነው ይህን ወንጀል የፈጸመው? ዋናው ነገር ይህንን ወንጀል የፈጸመውን እና ያስፈጸመውን ለይቶ ለህግ ማቅረብ ነው። ቪዲዮው ልጁ ግፍ ሲፈጸምበት እንጂ ግፍ የፈጸሙትን አያሳይም ለምን ወንጀለኞችን መደበቅ አስፈለገ? ታስቦበት ስለተፈጸመ ነው። በሴራ ከመዘፈቅ ይልቅ ወንጀሉን የፈጸሙትን በማጋለጥ ለህግ የበላይነት መተባበር ነበር። ግን ያንን ትተው ግፍ የተፈጸመበትን በማሳየት ህዝብን ማበሳጨት ነበር የተፈለገ። ወንጀሉን የፈጸመውን በመደበቅ አማራ ኦሮሞን አሰቃየ ማለት የፖለቲካ ሴራ ነው። ነገሩ … [Read more...] about “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል”
ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ!
“ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል” ታዬ “ዲቃላ” በጃዋር ስሌት ዋስትና የሌላቸው ኦሮሞዎች “በዐቢይ ላይ ቁርዓን ይዤ ጅማ እዘምታለሁ” ጃዋር ጃዋር በሁለት ጠርዝ ወደ መጨረሻው ምዕራፍ እየበረረ መሆኑንን የሚያሳዩ ምልክቶች እየታዩ ናቸው። በገሃድ እንደታየው ቤተመንግሥት ለመግባት የተጫኑለትን ስሞች በሙሉ አራግፎ ፖለቲከኛ ሆኗል። ወደ ሥልጣን በሚያደርገው ጉዞ ዋንኛው ዓላማ የተደረገው አማራን ማበጣበጥ ነው። ለዚህም ምኞቱ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በጅማና በመላው ኦሮሚያ እንዲጠሉ ቁርዓን ይዞ ዘመቻ እንደሚያደርግ ይፋ አድርጓል። በተመሳሳይ ደግሞ በጃዋር ጉዳይ መለሳለስ አሳይቷል እየተባለ የሚተቸው መንግሥት የተከማቸውን ፋይል ሊገልጥ ጫፍ መዳረሱን የሚያሳዩ ፍንጮችም ገሃድ እየወጡ ነው። በሌላ በኩል “ዲቃላ” በሚል ጃዋር የሚጠራቸው ኦሮሞዎች ዋስትናቸውን … [Read more...] about ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ!
“ህወሓት ስለ ብልፅግና ፓርቲ ህጋዊነት አይመለከተውም!” ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ
https://www.youtube.com/watch?v=NIvQXi8NwPo&feature=youtu.be&fbclid=IwAR13D7r_vtAWnyoTUm8e_yaHBwF_-QBrSVp7wJhB0-ezVQNHVrUZFPXecR8 … [Read more...] about “ህወሓት ስለ ብልፅግና ፓርቲ ህጋዊነት አይመለከተውም!” ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ
ለዋዜማ ሬዲዮ – የህዳሴውን ግድብ ዜናችሁን ላስተካክልላችሁ
የውሃ ሃብት ባለሙያ ነኝ፤ የግድቡ ጉዳይ ቀጥታ ከሙያዬ ጋር ባይገናኝም እንደዜጋ ሁኔታውን በቅርብ እከታተላለሁ፤ ፖለቲካንም እንዲሁ። የዋዜማን ሰዎች ዋዜማ ሳትሆኑ ነው የማውቃችሁ፤ ካገር ከመውጣታችሁ በፊት ማለቴ ነው። የማውቃችሁም በግል ሳይሆን እንደማንኛውም የሚዲያ ተጠቃሚ ነው፤ ስለዚህ እናንተ አታውቁኝም። አሁንም ዋዜማን እከታተላለሁ። ከዳያስፖራ ከሚመነጩት የዜና ዘገባዎችና መረጃዎች የእናንተ በተሻለ መጠን ተዓማኒነትና ሥርዓት የያዘ ነው ብዬ ስለማምን አነባችኋለሁ። “ኢትዮጵያን ቋሚ ባለዕዳ የሚያደርገው የህዳሴ ግድብ ስምምነት ላይ መንግስት የመፈረም ፍላጎት እያሳየ ነው” በሚል ርዕስ ያወጣችሁትን ዘገባ አንብቤዋለሁ። ዘገባው እንደሚለው ለረጅም ጊዜ የተጠበቀውን ሰነድ ስምምነት እንድትፈርም ኢትዮጵያ ግፊት እየተደረገባት እንደሆነ፤ ይህም “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ … [Read more...] about ለዋዜማ ሬዲዮ – የህዳሴውን ግድብ ዜናችሁን ላስተካክልላችሁ