• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል”

February 11, 2020 06:59 pm by Editor 4 Comments

የዚህች ሃገር ችግር የሴራ ፓለቲካ ነው። ጀዋር ሞሃመድ ዛሬ (ሰኞ) ለማየት የሚሰቀጥጥ አንድ ቪዲዮ ለጠፈ። በጣም አንጀት የሚበላ ጥቁርም ሆነ ነጭ ኦሮሞም ሆነ አማራ፤ የሰውን ልጅ እንደዛ በጭካኔ ማሰቃየት ከባድ የሰብዓዊነት ጥሰት ነው። የህግ ተጠያቂነት ደግሞ ግድ ነው፤ ግን ደግሞ ማነው ይህን ወንጀል የፈጸመው?

ዋናው ነገር ይህንን ወንጀል የፈጸመውን እና ያስፈጸመውን ለይቶ ለህግ ማቅረብ ነው። ቪዲዮው ልጁ ግፍ ሲፈጸምበት እንጂ ግፍ የፈጸሙትን አያሳይም ለምን ወንጀለኞችን መደበቅ አስፈለገ? ታስቦበት ስለተፈጸመ ነው።

በሴራ ከመዘፈቅ ይልቅ ወንጀሉን የፈጸሙትን በማጋለጥ ለህግ የበላይነት መተባበር ነበር። ግን ያንን ትተው ግፍ የተፈጸመበትን በማሳየት ህዝብን ማበሳጨት ነበር የተፈለገ።

ወንጀሉን የፈጸመውን በመደበቅ አማራ ኦሮሞን አሰቃየ ማለት የፖለቲካ ሴራ ነው። ነገሩ ድራማ መሆኑ በግልጽ ያሳያል። በሰው ጭንቅ እና ሰቆቃ ፖለቲካ ይሰራል።

የድራማው ባለቤት ደግሞ “Jawar” እራሱ ነው፤ የዚህ ጉዳይ አላማ ግልጽ ነው፤

1ኛው፤ አጀንዳ ማስቀየር ነው። የፖለቲካ ምረጡኝ “ጉማ እና ዲቃላ” ከሽፏል። “ጂርቱ እና ጂራ” የሚለው መፈክርም ተበላሽቷል። የጠባቂዎቼ መነሳት ፖለቲካም ውሃ አላነሳም። ስለዚህ አዲስ ኦሮሞን ስሜት የሚያነሳሳ አጀንዳ ማምጣት ያስፈለገው።

2ኛው፤ ኢትዮጵያ ወደ ዴሞክራሲ የምታደርገውን ጉዞ ማቆሸሽ ነው። ብዙ የአለም ሃገር መሪዎች አዲስአበባ ናቸው። ሁሉም ኢትዮጵያ ያለችበትን የሽግግር ጊዜ ትልቅ ቦታ ሰጥተውታል፤ ይህ የኢትዮጵያን ተቀባይነት ያሳድጋል። ይህንንም ለማቆሸሽ ነው ይህን ዘግናኝ ነገር ማምጣት ያስፈለገው።

3ኛው፤ ኢትዮጵያን ማፍረስ ነው። ማሳያውም በቅርቡ የአማራ ክልል ተማሪዎች በደንቢዶሎ መታገት ተነገረ። ኦሮሞ አማራን አገተ ሲባል ነበር። ዛሬ ደግሞ የአማራ ፖሊሶች ድሬዳዋ ላይ ኦሮሞን እያሰቃዩ ነው ብሎ ለጠፈ። ይህ ኦሮሞ እና አማራን የማባላት ከዩኒቨርስቲ ተማሪዎች እርስበርስ ማገዳደል የቀጠለ አጀንዳ መሆኑ ነው። ኢትዮጵያ ለማፍረስ ነው ይህ ሁሉ።

ወያኔ የሃውዜንን ህዝብ በእቅድ አስጨርሶ የትግራይን እና የአለምን ድጋፍ አገኘ። ዛሬ ውጪ የሚኖሩ ኦሮሞችን ደጋፍ ለመሸመት የወያኔን ተሞክሮ ወሰደ። ይህ መንገድ ዛሬ አያዋጣም።

ጃዋር በቀደም ተከበብኩ በማለት የ97 ንጹሃንን ህይወት አጥፍቷል። ይህ የኖቤሉን ድል በደም ለመቀባት የተደረገ ነበር። ዛሬ ደግሞ አጀንዳ ለማስቀየር እና ህዝብን ለማባላት ቪዲዮ በማዘጋጀት ለቀቀ። መንግስት በጣም ነው የታገሰው።

ከዚህ በላይ በህዝብ ደም እና ስቃይ መነገድ መቆም አለበት። ተጠያቂነትም ይመጣል። እንደ ትናንቱ በንጹሃን ደም እና ስቃይ በመጫወት GoFunDMe መክፈት የለም። ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል። ምርመራም ተጀምሯል።

ሰብዓዊ መብት የህግ የበላይነት!

ታዬ ደንደአ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Left Column, Opinions Tagged With: jawar massacre, Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. gi haile says

    February 12, 2020 07:14 am at 7:14 am

    ቀደሙኑ የሰብዐዊ መብት በማስከበሩ ረገድ የፍርድ ተቋማት ትክክለኛ ስራ ሰርተው ቢሆን ኖሮ የነጭ ሸሚዝ ከላይ የውስጥ ካናቴራ የሸተተ ሌቦች አገራችንን በሌብነት ሙያቸው በላዋረዷት ነበር አሸዋ ማሽላ ብሎ ሲሸጥ የነበረ ሌባ አገር ሲሰጠው ይምራል ወይ ቢባል ሊሞቱ የደረሱ ሌቦች አሁን ለፍርድ ቀረቡ ኣልቀረቡ ትርጉም የለውም የዘረፉት ግን ወደ መንግስት ካዝና ይግባ። የተሰረቀ ሐብት በውጭ በውሽሞችና በልጆቻቸው በየአገሩ ተበትኖ ይገኛልና ሌባ በአደባባየሰ ከማዋረድ በቀር ሌላ ፍርድ ኣያስፈልገውም። ሌቦቹን በአደባባይ ከሰረቁት ነገረሰ ጋር በአደባባይ ማጋለጠሰ እራሱ የሞራል ውድቀትና ኪሳራ ነው። ኂሊናወሰ የደነዘዘን ሌባ በፍርድ ቤት ለመቅጣት መነሳት የአገር ሐብትን ለፍርድ ቤት መባከን ነው። መጀመሪያ ሐብታቸውን መውረስ ይቀድማል ከዚያ በመረጃ ሐብታቸው ምንጭ ከየት እንደሆነ ይጣራ።

    Reply
  2. Aman Kidane says

    February 12, 2020 03:44 pm at 3:44 pm

    “ወያኔ የሓውዘን ሕዝብ በዕቅድ ኣስጨርሶ የትግራይንና የዓለም ድጋፍ ኣገኝ” የምትለዋን በኢትይጵያ በተለይ ደግሞ በኣማራ ፖለቲከኞች በተደጋጊሚ ስትትረክ እንሰማለን።
    በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የታሪክ ክህደትና ሌብነት የተለመደ ነው።
    ኣንድ ከፍተኛ ባለስልጣን እንደዚህ ዓይነት የሕዝብን ቁስል የሚጭር ነውረኝ መግለጫ ሲሰጥ፡ ለትግራይ ሕዝብ ስድብ ብቻ ሳይሆን መራር ሓዘን ነው። ትናንት በኛ ዘመን የተፈጸው የህዝብ እልቂት፡ ሓሰት ነው ኣልተፈጸመም፡ ወይም ሴራ ነው ብሎ ማለት፡ በሽዎች ደም መቀለድ ነው። የትግራይ ሕዝብ የከፈለው መስዋእት ማንቃሸሽ ነው።ኢትዮጵያ እንደ ሓገር የት እንደሚያደርሳት እናያለን። ኣገረቱ በታሪክ ሌቦች እየተመራች ነው ልበል!
    በጣም ያሳዝናል፡ እል

    Reply
    • ሞሽ says

      February 15, 2020 02:27 am at 2:27 am

      በጊዜው ለገበያ በተሰበሰበ ህዝብ መሀል የታጠቀ የወያኔ ሰራዊት እንዲገባ ተደርጓል፡፡ በመቀጠልም ወያኔዎች ደርግ ውስጥ በሚገኙ ሰዎች አማካኝነት ከደርግ የደህንነት ክንፍ መረጃ እንደመጣ በማስመሰል ለአየር ሀይል አዛዦች ይሄ መረጃ እንዲደርስ አድርገዋል፡፡ ደርግም ጠላቴን ገበያ ላይ አገኘሁት ብሎ ጀት ሲልክ፡ ወያኔ ደግሞ ካሜራ ይዛ እየጠበቀች ነበር፡፡ ይሄ ከሆነ አንተን ያሳዘነህ፡ ፓለቲካ አልገባህም ወይም አልበሰልክም ማለት ነው፡፡

      Reply
    • Tsega Zeab says

      February 16, 2020 05:51 am at 5:51 am

      የሃውዜንን ሚስጥር ያወጣው ማንም አይደለም: ከትግራይ ተወላጁ የህወሃት ነባር ታጋይ ገብረመድህን ኣርኣያ እንጅ:: ታዲያ አማራ ላይ ማላክክ ምን አመጣው? ከሃውዜን የቀጠለው እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል የሚለው የህወሃት የሴራ ፖለቲካ ተከታታዩ ድራማ ካልሆነ በስተቀር:: የቂልነት ገደብ ከሌለው በስተቀር: የኢትዮጵያ ህዝብ ስለህወሃት ያለው ግንዛቤ ከሩብ ክፍለዘመን በላይ ያስቆጠረ ስለሆነ ወድቆ መንፈራገጥ አጉል መላላጥ ነው:: የትግራይ ህዝብም አሁን አንተ የምታላዝነውን ጥቁር ውሸት በግርድፋ የሚያኝክ አይመስለኝም:: ከሆነ ግን ራሱን መልሶ ግብር የሚያስከፍለው መሆኑን ለማወቅ ነቢይነትን አይጠይቅም:: ገብረመድህን ኣርአያ አልሞተም አልታመመም በተንቀሳቃሽ ምስልም ተቀርፆ አለም ያየውና ለወደፊቱም የሚያየው የህወሃት አንዱ ጥቁር ታሪክ ነው:: የሙታን ቤተሰቦችም አንድ ቀን ህወሃትን ለፍርድ የሚያቀርቡበት መረጃ ስለሆነ እንዲሁ በቀላሉ ወደ አማራ በማላከክ የሚዘጋ ፋይል አይመስለኝም::

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule