• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ

February 13, 2020 05:07 pm by Editor Leave a Comment

“በየቦታው የሚፈጠሩ የወንጀል ድርጊቶች ዋነኛ ችግር የፖለቲካ አመራሮች እጅ” አለበት

ጠቅላይ አቃቤ ሕግ በኢትዮጵያ የሕግ የበላይነትን ለማስከበር የተወሰዱ እና ሊወሰዱ ይገባቸዋል ስላላቸው እርምጃዎች የካቲት 5፣ 2012 መግለጫ አውጥቷል። በየቦታው የሚፈጠሩ የወንጀል ድርጊቶች ዋነኛ ችግር የፖለቲካ አመራሮች እጅ እንዳለበት የገለጸው መግለጫ ለሀገሪቱ ደህንነትና ለህዝቡ ህልውና ሲባል ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን እንደማይታገስ አቋም መያዙን ይፋ አድርጓል።

የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦

ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተሰጠ መግለጫ

የሕግ የበላይነትን ማስከበር ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የፍትህ ስርዓቱን የማጠናከርና የህግ የበላይነትን የማክበርና የማስከበር ተግባሩን አጠናክሮ ለማስቀጠል ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ይታወሳል። በተለይም መንግሥት የሕግና የፍትሕ ሥርዓቱን ለማሻሻልና በዘርፉ አሳታፊነትን ለማጎለበት በሰጠው ትኩረት መሠረት ከመንግሥት መዋቅር ውጭ ከፍተኛ ልምድና ብቃት ያላቸውን የሕግ ባለሙያዎች ያካተተ የሕግና ፍትህ ጉዳዮች አማካሪ ጉባዔ በማቋቋም የሰብዓዊና የዴሞክራሲ ምህዳሩን ሊያሰፉ የሚችሉ ህጎች ላይ ማሻሻያ አድርጓል።

አንዳንዶቹ ከ20 ዓመት በላይ ለማሻሻል ተብሎ ከፍተኛ የሀብት ብክነት ሲፈፀምባቸው የነበረው በአማካሪ ጉባኤ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲሻሻል የተደረጉት ተጠቃሽ ናቸው።

የሕግ የበላይነትን በማረጋገጥ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋትና ህዝባችን በፍትሕ ሥርዓቱ ያለውን አመኔታ ለማሻሻል በተወሰደው የማሻሻያ እርምጃ ለህዝባችን ተስፋን ያሰነቁ ተግባራት ተፈፅመዋል።

በሌላ በኩል የህግ ተጠያቂነትን ከማረጋገጥ ጋር በተያያዘ በከባድ ሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ በጅምላ ጭፍጨፋ እና ከባድ የሙስና ወንጀል ፈፅመዋል ተብለው የተጠረጠሩ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የዚህ ድርጊት ተሳታፊ የሆኑ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እንዲታይ ተደርጓል።

ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እየተበራከቱ የመጡ የወንጀል ተግባራት በተለይም በብሔር ወይም በክልሎች መካካል በግለሰቦችና ቡድኖች በሚፈጠር ግጭት መነሻነት ወንጀል የተፈጸመባቸው አካባቢዎች ዋና ዋና ተጠርጣሪዎችን በሕግ ቁጥጥር ሥር እንዲውሉ በማድረግ የተደራጀ የምርመራና ክስ የመመሥረት ሂደት ላይ እንገኛለን።

በዚህ መሰረት፣ በኦሮሚያ ክልል ምእራብ ጉጂ ዞን እና በደቡብ ክልል ጌደኦ ዞን አንዳንድ አካባቢዎች፣ በሶማሌ ብሔራዊ ክልል በጅግጅጋና ሌሎች ዞኖች፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ብሔራዊ ክልል ካማሽ ዞን፣ መተከል ዞን፣ በደቡብ ክልል በሀዋሳ፣ በቴፒና ሸካ ዞን፣ በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ፣ ምስራቅ ሸዋ፣ አርሲ፣ ምስራቅ ሐረርጌ፣ ባሌ ዞን፣ ምዕራብ አርሲ፣ ምዕራብ ሸዋ እና አዲስ አበባ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን፣ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞንና በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር፣ በአዊ ብሄረሰብ ዞን በጃዊ ወረዳ፣ በጎንደር፣ በአዲስ አበባ በሃይማኖት ተቋማት እንዲሁም በአንዳንድ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተፈጸመውን ወንጀል ድርጊቶችን መነሻ በማድረግ ተጠሪጣሪዎችን ቁጥጥር ሥር የማዋል ሥራ ተጀምሯል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የካቲት 5 ቀን 2012 ዓ.ም በክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር የሚመራ የፌደራል የፍትህና የጸጥታ መዋቅር አመራሮች እንዲሁም የክልሎች ርዕሰ መስተዳድሮችና የፍትህና የጸጥታ መዋቅር አመራሮች ባካሄዱት አስቸኳይ ግምገማ ለውጡን ተከትሎ በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ማንነትን መሠረት ያደረጉ፣ በሃይማኖት ተቋማት ላይ እና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎች እንዲሁም በከባድ የሙስና ወንጀል ተጠርጥሮ ያልተያዙ ተጠርጣሪዎችን ለፍርድ ለማቅረብ ከመቼውም ጊዜ በላይ በቁርጠኝነት ህዝቡን ይዞ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።

መንግሥት በለውጡ ማግስት የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት በህግና ፍትህ ስርዓቱ ላይ እመርታዊ ለዉጥ ለማምጣት በርካታ ተግባራትን ሲያከናውን እንደነበረ እሙን ነው።  የፍርድ ወሳኔ ያገኙና ጉዳያቸው በምርመራ ላይ ያሉ ተጥርጣሪዎችን በምህረት አዋጅ ክሳቸው እንዲቋረጥ ተደርጓል። በርካቶቹ በይቅርታ ከእሥር እንዲፈቱ ተደርገዋል። ይህ የመንግሥት ሆደ ሰፊነትን ያልተረዱ አንዳንድ አካላት ኢ-መደበኛ በሆነ ቡድናዊ አደረጃጀት በርካታ ወንጀሎችን ሲፈጽሙ ተሰተውሏል። በዚህም ክቡር የሰው ልጅ ህይወት ጠፍቷል፣ የሕዝብና የመንግሥት ሀብትና ንብረት ተዘርፏል፣ ወድሟል። ስለሆነም ከእንግዲህ ወዲህ ለሀገራችን ደህንነትና ለህዝባችን ህልውና ሲባል ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን እንደማይታገስ ጽኑ አቋም ተይዟል።

ከፍተኛ አመራሩ ባደረገው ግምገማ በየቦታው የሚፈጠሩ የወንጀል ድርጊቶች ዋነኛ ችግር የፖለቲካ አመራሮች እጅ ያለበት መሆኑን በሚገባ የተረዳ ሲሆን፥ ይህን የማይገባ ተግባር ሲያስፈጽም እና ሲፈፅም በዝምታ ሲያልፍ የነበረው አመራር ከዚህ እንዲታረም በዚህ አጋጣሚ ማሳሰብ ይፈልጋል።

በሀገሪቱ በሚፈለገው መጠን የህግ የበላይነትን በማስከበር ዘንድ የነበረውን ፈተና ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ የምንሻገረው እንደሚሆን እሙን ነው። ስለሆነም ይህን ህገ ወጥ ተግባራትን የምንሸከምበት ጫንቃ እና በወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦችን ለፍርድ የማናቀርብበት ምንም ምክንያት የማይኖረን መሆኑን እንገልጻለን።

ስለሆነም በዛሬው መድረካችን በተፈጸሙ ወንጀሎች ላይ የተሳተፉ አካላትን በህግ ፊት ለማቅረብ፣ የዜጎች ሰብዓዊ መብት ጥሰት ለመከላከል የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንዲሁም ተጠርጣሪዎች በሕግ ፊት እንዲቀርቡ በሚደረገዉ ጥረት ላይ የሚያደናቅፉ አካላት ላይ ያለምንም ምህረት በማያዳግም ሁኔታ ተጠያቂ የሚያደረግ መሆኑን መግለጽ ይፈልጋል።

በሌላ በኩል ከወንጀል ድርጊቶች ጋር በተያያዘ የተጀመረው የተጠረጠሩትን ግለሰቦች ለፍርድ የማቅረብ ሂደቱ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፤ በዚህም የህግ የበላይነትን የማስከበር እንቅስቃሴ ለድርድር አይቀርብም። ኅብረተሰቡም ጥፋት ፈፃሚዎችን ለህግ ለማቅረብ በሚደረገው ርብርብ እንደ ወትሮው ሁሉ አሁንም የተለመደ ትብብሩን እንዲቀጥል በዚህ አጋጣሚ እንጠይቃለን።

ኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ
የካቲት 5 ቀን 2012 ዓ.ም
አዲስ አበባ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: AG, Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule