• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ

February 13, 2020 05:07 pm by Editor Leave a Comment

“በየቦታው የሚፈጠሩ የወንጀል ድርጊቶች ዋነኛ ችግር የፖለቲካ አመራሮች እጅ” አለበት

ጠቅላይ አቃቤ ሕግ በኢትዮጵያ የሕግ የበላይነትን ለማስከበር የተወሰዱ እና ሊወሰዱ ይገባቸዋል ስላላቸው እርምጃዎች የካቲት 5፣ 2012 መግለጫ አውጥቷል። በየቦታው የሚፈጠሩ የወንጀል ድርጊቶች ዋነኛ ችግር የፖለቲካ አመራሮች እጅ እንዳለበት የገለጸው መግለጫ ለሀገሪቱ ደህንነትና ለህዝቡ ህልውና ሲባል ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን እንደማይታገስ አቋም መያዙን ይፋ አድርጓል።

የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦

ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተሰጠ መግለጫ

የሕግ የበላይነትን ማስከበር ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም

የኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የፍትህ ስርዓቱን የማጠናከርና የህግ የበላይነትን የማክበርና የማስከበር ተግባሩን አጠናክሮ ለማስቀጠል ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ይታወሳል። በተለይም መንግሥት የሕግና የፍትሕ ሥርዓቱን ለማሻሻልና በዘርፉ አሳታፊነትን ለማጎለበት በሰጠው ትኩረት መሠረት ከመንግሥት መዋቅር ውጭ ከፍተኛ ልምድና ብቃት ያላቸውን የሕግ ባለሙያዎች ያካተተ የሕግና ፍትህ ጉዳዮች አማካሪ ጉባዔ በማቋቋም የሰብዓዊና የዴሞክራሲ ምህዳሩን ሊያሰፉ የሚችሉ ህጎች ላይ ማሻሻያ አድርጓል።

አንዳንዶቹ ከ20 ዓመት በላይ ለማሻሻል ተብሎ ከፍተኛ የሀብት ብክነት ሲፈፀምባቸው የነበረው በአማካሪ ጉባኤ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲሻሻል የተደረጉት ተጠቃሽ ናቸው።

የሕግ የበላይነትን በማረጋገጥ የዴሞክራሲ ምህዳሩን ለማስፋትና ህዝባችን በፍትሕ ሥርዓቱ ያለውን አመኔታ ለማሻሻል በተወሰደው የማሻሻያ እርምጃ ለህዝባችን ተስፋን ያሰነቁ ተግባራት ተፈፅመዋል።

በሌላ በኩል የህግ ተጠያቂነትን ከማረጋገጥ ጋር በተያያዘ በከባድ ሰብዓዊ መብት ጥሰት፣ በጅምላ ጭፍጨፋ እና ከባድ የሙስና ወንጀል ፈፅመዋል ተብለው የተጠረጠሩ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም የዚህ ድርጊት ተሳታፊ የሆኑ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እንዲታይ ተደርጓል።

ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እየተበራከቱ የመጡ የወንጀል ተግባራት በተለይም በብሔር ወይም በክልሎች መካካል በግለሰቦችና ቡድኖች በሚፈጠር ግጭት መነሻነት ወንጀል የተፈጸመባቸው አካባቢዎች ዋና ዋና ተጠርጣሪዎችን በሕግ ቁጥጥር ሥር እንዲውሉ በማድረግ የተደራጀ የምርመራና ክስ የመመሥረት ሂደት ላይ እንገኛለን።

በዚህ መሰረት፣ በኦሮሚያ ክልል ምእራብ ጉጂ ዞን እና በደቡብ ክልል ጌደኦ ዞን አንዳንድ አካባቢዎች፣ በሶማሌ ብሔራዊ ክልል በጅግጅጋና ሌሎች ዞኖች፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ብሔራዊ ክልል ካማሽ ዞን፣ መተከል ዞን፣ በደቡብ ክልል በሀዋሳ፣ በቴፒና ሸካ ዞን፣ በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ፣ ምስራቅ ሸዋ፣ አርሲ፣ ምስራቅ ሐረርጌ፣ ባሌ ዞን፣ ምዕራብ አርሲ፣ ምዕራብ ሸዋ እና አዲስ አበባ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን፣ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞንና በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር፣ በአዊ ብሄረሰብ ዞን በጃዊ ወረዳ፣ በጎንደር፣ በአዲስ አበባ በሃይማኖት ተቋማት እንዲሁም በአንዳንድ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተፈጸመውን ወንጀል ድርጊቶችን መነሻ በማድረግ ተጠሪጣሪዎችን ቁጥጥር ሥር የማዋል ሥራ ተጀምሯል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የካቲት 5 ቀን 2012 ዓ.ም በክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር የሚመራ የፌደራል የፍትህና የጸጥታ መዋቅር አመራሮች እንዲሁም የክልሎች ርዕሰ መስተዳድሮችና የፍትህና የጸጥታ መዋቅር አመራሮች ባካሄዱት አስቸኳይ ግምገማ ለውጡን ተከትሎ በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ማንነትን መሠረት ያደረጉ፣ በሃይማኖት ተቋማት ላይ እና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ የተፈጸሙ ወንጀሎች እንዲሁም በከባድ የሙስና ወንጀል ተጠርጥሮ ያልተያዙ ተጠርጣሪዎችን ለፍርድ ለማቅረብ ከመቼውም ጊዜ በላይ በቁርጠኝነት ህዝቡን ይዞ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።

መንግሥት በለውጡ ማግስት የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋት በህግና ፍትህ ስርዓቱ ላይ እመርታዊ ለዉጥ ለማምጣት በርካታ ተግባራትን ሲያከናውን እንደነበረ እሙን ነው።  የፍርድ ወሳኔ ያገኙና ጉዳያቸው በምርመራ ላይ ያሉ ተጥርጣሪዎችን በምህረት አዋጅ ክሳቸው እንዲቋረጥ ተደርጓል። በርካቶቹ በይቅርታ ከእሥር እንዲፈቱ ተደርገዋል። ይህ የመንግሥት ሆደ ሰፊነትን ያልተረዱ አንዳንድ አካላት ኢ-መደበኛ በሆነ ቡድናዊ አደረጃጀት በርካታ ወንጀሎችን ሲፈጽሙ ተሰተውሏል። በዚህም ክቡር የሰው ልጅ ህይወት ጠፍቷል፣ የሕዝብና የመንግሥት ሀብትና ንብረት ተዘርፏል፣ ወድሟል። ስለሆነም ከእንግዲህ ወዲህ ለሀገራችን ደህንነትና ለህዝባችን ህልውና ሲባል ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን እንደማይታገስ ጽኑ አቋም ተይዟል።

ከፍተኛ አመራሩ ባደረገው ግምገማ በየቦታው የሚፈጠሩ የወንጀል ድርጊቶች ዋነኛ ችግር የፖለቲካ አመራሮች እጅ ያለበት መሆኑን በሚገባ የተረዳ ሲሆን፥ ይህን የማይገባ ተግባር ሲያስፈጽም እና ሲፈፅም በዝምታ ሲያልፍ የነበረው አመራር ከዚህ እንዲታረም በዚህ አጋጣሚ ማሳሰብ ይፈልጋል።

በሀገሪቱ በሚፈለገው መጠን የህግ የበላይነትን በማስከበር ዘንድ የነበረውን ፈተና ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ የምንሻገረው እንደሚሆን እሙን ነው። ስለሆነም ይህን ህገ ወጥ ተግባራትን የምንሸከምበት ጫንቃ እና በወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦችን ለፍርድ የማናቀርብበት ምንም ምክንያት የማይኖረን መሆኑን እንገልጻለን።

ስለሆነም በዛሬው መድረካችን በተፈጸሙ ወንጀሎች ላይ የተሳተፉ አካላትን በህግ ፊት ለማቅረብ፣ የዜጎች ሰብዓዊ መብት ጥሰት ለመከላከል የተጀመረው ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል እንዲሁም ተጠርጣሪዎች በሕግ ፊት እንዲቀርቡ በሚደረገዉ ጥረት ላይ የሚያደናቅፉ አካላት ላይ ያለምንም ምህረት በማያዳግም ሁኔታ ተጠያቂ የሚያደረግ መሆኑን መግለጽ ይፈልጋል።

በሌላ በኩል ከወንጀል ድርጊቶች ጋር በተያያዘ የተጀመረው የተጠረጠሩትን ግለሰቦች ለፍርድ የማቅረብ ሂደቱ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፤ በዚህም የህግ የበላይነትን የማስከበር እንቅስቃሴ ለድርድር አይቀርብም። ኅብረተሰቡም ጥፋት ፈፃሚዎችን ለህግ ለማቅረብ በሚደረገው ርብርብ እንደ ወትሮው ሁሉ አሁንም የተለመደ ትብብሩን እንዲቀጥል በዚህ አጋጣሚ እንጠይቃለን።

ኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ
የካቲት 5 ቀን 2012 ዓ.ም
አዲስ አበባ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: AG, Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule