• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል

February 25, 2020 11:26 pm by Editor Leave a Comment

ኦነግ አወዛጋቢ ማንነቱና ያልረጋ የፖለቲካ ሩጫው ዛሬም መነጋገሪያ ሆኗል። ቀደም ሲል ለኦሮሞ ትግል እንደ አንድ ብቸኛና ልዩ ምልክት ተደርጎ የተወሰደው ኦነግ በአራት ጎራ ተከፍሎ ቢቆይም አገር ቤት ከገባ በኋላ አንድ መሆን አልቻለም።

በኤርትራ በረሃ እያለ እርስበርስ ጎራ ለይቶ በጥይት የተጫረሰው ኦነግ፣ በአውሮፓና በአሜሪካ ባሉ የተለያዩ አመራሮቹ የስልጣን ሽኩቻ አንድ መሆን አቅቶት ሁለት ዐሥርተ ዓመታት አስቆጥሮ አሁን አገሪቱ ውስጥ በተፈጠረው የፖለቲካ ለውጥ ሁሉም አካላት ወደ አገር ቤት ቢገቡም ልዩነታቸውን ማስወገድ አልቻሉም።

ዳውድ ኢብሣ (ፍሬው ማሾ)፣ አባ ነጋ፣ ገላሳ ዲልቦና ጄኔራል ከማል ገልቹ የተቀራመቱት ኦነግ አራት መልክ ይዞ ወደ አገር ቤት ሲገባ ሕዝብ ጥያቄ ያነሳው “ለምን አንድ አትሆኑም? አንድ ሁኑና ኑ” የሚል ነበር። እነዚህ አራት ክንፎች እንኳን አንድ ሊሆኑ ይባስ ብሎ አቶ ዳውድ ኢብሣ የሚመሩት ኦነግ ሸኔ በሚል ሁለት መልክ ይዞ መጣ።

የፕሮፌሰር መረራ ፓርቲ ኦፌኮ ከአቶ ዳውዱ ኦነግ ሸኔና ከጄኔራል ከማል ገልቹ ሽራፊ ኦነግ ጋር ግንባር ለመፍጠር መስማማታቸው ይፋ ቢሆንም፣ አቶ ዳውድ መቀሌ የመሸገው ህወሓት ካደራጀው የፌደራሊስቶች ኃይል ጋር ፍቅር መጀመሩ በርካቶችን ጉድ ያሰኘና ህወሓት ክፉኛ በደል ሲፈጽምባቸው በነበሩ የኦሮሞ ልጆችና ቤተሰቦች እንዲሁም ባጠቃላይ የኦሮሞ ማኅበረሰብ ዘንድ “አይ ዳውድና ድርጅቱ!?” በሚል ሙሾና ሽሙጥ እየተሰነዘረበት ነው።

ኦነግ ሸኔ – መንታ ትግል

ዳውድ ኢብሣ የሚመሩት ኦነግ ሸኔ አንድም ቁራሽ መሬት በቁጥጥሩ ሳያውል ከኤርትራ የበረሃ ኑሮ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ ወታደሮቹ ደግሞ በትግራይ በኩል ሲገቡ እነ ስብሃት ነጋ በቀይ ወጥ ግብዣ አድርገውላቸው ነበር። ኦነግ ሸኔ ወደ ትግራይ በረሃ ያሽቀነጠራቸውን ኃይል ለእንኳን ደህና መጣህና ለቀይ ወጥ ግብዣ ሲመርጡ ነበር ወዲያውኑ “የማይረጥቡ አሣዎች” የሚል ስያሜ የተሰጣቸው። “አይቼሽ ነው ባይኔ ወይስ በቴሌቪዥን” ሲሉ የዘፈኑላቸውም ጥቂት አልነበሩም።

ሥጋቱ ብዙም ሳይቆይ አቶ ዳውድ “ይቅርታ ሰጪም፣ ይቅርታ ተቀባይም የለም” ሲሉ የፍየል ከመድረሷ ቅጠል መቅንጠሷ ፖለቲካቸውን ጀመሩ። ቄሮ ትግሉን ባፋፋመበት ወቅት “የቄሮ አደረጃጀት ባለቤት ማንም ሳይሆን እኛ ነን” ሲሉ ከኤርትራ የጫጉላ ሰፈራቸው በወረዛ የቪዲዮ መልዕክት ያስተላለፉት አቶ ዳውድ በወቅቱ ጃዋርን “አትንተክተክ” ሲሉትም ተደምጠው ነበር።

በኦነግ ምስኪን ወታደሮች ላይ የተፈጸመው የእርስ በእርስ መገዳደልና በአመራር ውሳኔ ህይወታቸውን ያጡ፣ የተሰቃዩ፣ በእስር ማቅቀው ያለፉት ጉዳይ ራሱን የቻለ አጣሪ እንደሚያስፈልገው የዳውድ ኢብሣ ኮቴ አዲስ አበባ ሲረግጥ መወትወት የጀመሩ ቢኖሩም አዋራው የፈጠረው ጩኸት ሰሚ እንዲያገኙ አላስቻላቸውም። በተመረዘ ምግብ በአንድ አዳር ዳውድ ሲተርፉ የተቀሩት እምሽክ ያሉበት ግፍና የኦነግ ሠራዊት ኤርትራ በረሃ የደረሰበት አስነዋሪ ግፍ ፋይል ግን አልተዘጋም። ቀኑን ጠብቆ ይከፈታል የሚል እምነት በበርካቶች ዘንድ አለ።

ሁሉም ቀርቶ ኦነግ ሸኔ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ ቅድሚያ ሥራው የነበረው በወለጋ የተለያዩ ዞኖችና በቤኒሻንጉል ጫካዎችና ትምህርት ቤቶች ውስጥ ህጻናትን ለውትድርና መልምሎ በማሰልጠንና በማስታጠቅ ነበር የጀመረው። የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ የቤኒሻንጉል አንድ ከፍተኛ አመራርን አነጋግሮ እንደተረዳው ኦነግ ሸኔ በርካታ ቁጥር ያላቸውን ህጻናት ሲያሰለጥንና ሲመለምል ያልታደሰው የኦዲፒ ኃይል፣ መከላከያውና ደኅንነት/ጸጥታ ውስጥ ያለው መዋቅር ያውቅ ነበር። ከማወቅም በላይ ተባባሪ የነበሩ፣ መሣሪያ በማጓጓዝና በማስዘረፍ የሚተባበሩ ነበሩ።

በዚህ መልክ አጋጣሚን ተገን አድርጎ በአኩራፊ ጡንቸኛ ኃይላት ድጋፍ የደረጀው ኦነግ ሸኔ የሰላማዊ ትግል እያጣቀሰ ራሱን ለትጥቅ ትግል ሲያዘጋጅ ዋና መሪው መቀመጫውን ኡጋንዳ ያደረገው ዱጋሣ ባካኮ የሚባለው የቀድሞ ኦነግ የሠራዊት መሪ ነው። ዱጋሣ ኦነግ ሸኔ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ አብሮ የመጣ ሲሆን ይህንኑ ሚሽን ተቀብሎ ወዲያው አገር ጥሎ እንደወጣ ይታወቃል።

እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ጃል መሮ የሚመራው ሽፍታ የሚባለው ድራማ የሸኔዎች ማምታቻና የተገዙ ሚዲያዎች ስብከት ነው። በአባ ነጋ የሚመራው ኦነግ አባል እንደሚለው ዳውድ ኢብሣና ዱጋሣ ባካኮ አንድና ሊለያዩ የማይችሉ ናቸው። ይህ ታማኝ የሠራዊት መሪ ይህ ኃላፊነት እንዲሰጠው የተደረገውም በዚሁ ትሥሥር እንጂ በሌላ አይደለም። ሰኞ በተላለፈው ዘገባ ለቪኦኤ መግለጫ የሰጡት የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽነር አራርሣ መርዳሣም ያረጋገጡት ይህንኑ ነው።

ዱጋሣ ባካኮ

እሳቸው እንዳሉት ኦነግ ሸኔ በሁለት እግሩ እየተጫወተ ነው። አዲስ አበባ ያለውና ጫካ የከተመው ኦነግ ሸኔ በሚገባ አንድ ናቸው። የኮሚሽነሩን መግለጫ “የት ከርመሽ” ሲሉ የተቹት የአባ ነጋ ኦነግ አባል “ይህ ጉዳይ በግልጽ ከድሮ ጀምሮ የሚታወቅ፣ የአደባባይ ሚስጢር ነው። ዛሬም አልረፈደም። ሕዝብ መርሮታል። ለሁለት መንግሥት መገበር ሰልቸኝ እያለ እያለቀሰ ነው። ሰላማዊ ሰልፍ አድርጎ አረጋግጧል” ይላሉ።

ኦነግ ሸኔ – ቃርሚያ ሲጀመር ለምን ይጮሃል?

ምክትል ኤታማዦር ሹም ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ አዲስ አበባ ያለው ኦነግ ሸኔና በረሃ ያለው ሽፍታው ኦነግ ሸኔ አንድ መሆናቸውን ለቢቢሲ በቅርቡ በይፋ ተናግረዋል። ይህንኑ ኃይል ለመደምሰስ መንግሥት በይፋ ዘመቻ መክፈቱንም አረጋግጠዋል። የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽንም ይህ ኦነግ ሸኔ በወጉ መመታቱን አስታውቀዋል። እንደ መንግሥት ገለጻ ከሆነ አሁን ተበትኖ ወደ ትውልድ ቀዬው መሸሽ የቻለውን ኃይል እየቃረሙ ነው።

ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ

እንግዲህ ሰሞኑን “አባላቶቼ ታሰሩብኝ፣ አባላቶቼ ተገረፉ፣ ተሳደዱ…” በሚል የአዲስ አበባው ኦነግ ሸኔ በአቶ ዳውድ ፊርማ ሰሞኑንን ተከታታይ መግለጫ እያወጣ ነው። የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽነር አራርሣ መርዳሣ የጸጥታ አስከባሪዎቻችን፣ የሲቪል መሥሪያ ቤት ሠራተኞች፣ ሰላማዊ ነዋሪዎች፣ ሚሊሻዎች በኦነግ ሸኔ ታታቂ ሽፍቶች ሲገደሉ አዲስ አበባ ያለው ቢሮ ያለው ነገር ያለም። ለምን? በማለት ይጠይቃሉ።  

እርሳቸውን እንዲያስተባበሉ የቪኦኤው ሙክታር ጀማል ያናገራቸው የአዲስ አበባው ኦነግ ሸኔ ሥራ አሥፈጻሚ ሚካኤል በረን “አንድ አይደለንም” ሲሉ ጫካ ሆኖ ንጹሃንን ስለሚገድለው ኦነግ ሸኔ ይናገራሉ። አያይዘውም መንግሥትን ጨምሮ ሁሉም ኃይሎች የሚሳተፉበት መፍትሔ ካልተፈለገ አንድን ኃይል ወይም ቡድን በማጠልሸት ወደሚፈለገው ሰላም አያመጣም” ሲሉ ሁሉ አቀፍ የመፍትሔ እርምጃ እንዲወሰድ ይወተውታሉ።

ዛሬ መንግሥት ቃርሚያ ላይ መሆኑንን፣ በተለያዩ የኦሮሚያ ክልሎች መንግሥትን የሚደግፉ ሰላማዊ ሰልፎች ወለጋን ጨምሮ መደረጉ በኦሮሚያ የሚንቀሳቀሱ ኃይሎችን አስደንግጧል። ይህ ሽፍታ ቡድን በርካታ ለጋ ምልምሎቹ የተማረኩና የተደመሰሱ መሆናቸው፣ ሕዝቡም ለእነሱ ቀለብ መስፈር መሰላቸቱ፣ ሥራውን መሥራትና ምርቱን ወደ ገበያ ማውጣት አለመቻሉ ስላስመረረው የሸኔ ጉዞ የጨለመ መስሏል። እናም ጩኸቱ “ጩኸቴን ቀሙኝ” ከመሆን አያልፍም።

የዘወትር የጎልጉል መረጃ አቀባይ የኦፌኮ የመካከለኛ ደረጃ አመራር እንደሚለው ኦፌኮም የሸኔ ሰለባ እንዳይሆን ሥጋት አለ። አቶ በቀለ ገርባ ፕሮፌሰር መረራን ቆርጠው ኦፌኮን ከኦነግ ሸኔ ጋር አብረው ሊገምዱት ጫፍ ደርሰው እንደነበር ያስታወቀው ይኸው መረጃ አቀባይ የተጀመረው አብሮ የመሥራት ስምምነት ወደ ውኅደት ያላደገው ከውስጥ ባለ ጫና ነው ” ይላል።

ኦነግ ሸኔና – ዕድገት ወደ ቅጥር ነፍሰ ገዳይነት

በወለጋ የቴሌኮሙኒኬሽን ኃላፊን ከቤቱ አስጠርቶ ቤተሰቡ ፊት የገደለው የኦነግ ሸኔ ክንፍ በርካታ ንጹሃንን ገሏል። በቤኒሻንጉል መንገድ ላይ እየጠበቀ ባለሥልጣንን ገድሏል። በአምቦና በኢጀሬ መካከል ሚሊሻዎችን ገሏል። የመንግሥት ተቋማትን ዘርፏል። የኦሮሚያ ፖሊስ ይፋ እንዳደረገው በቡራዩ ኮማንደር ሰለሞን ታደሰን ገሏል፣ አንድ አርቲስትና ሁለት ተጨማሪ ዜጎችን አቁስሏል። ኮማንደር ሰለሞንና ሁለቱ የቆሰሉት ወገኖች የሰላሌ ተወላጆች መሆናቸው ጉዳዩን “እየመረጡና እየለዩ መግደል” የሚል ስም እንዲሰጠው አድርጎታል።

ይህ ሳያንስ በአምቦ ለብልጽግና ፓርቲ ድጋፍ ለመስጠት አደባባይ በወጡ ሰልፈኞች ላይ ቦምብ ተወርውሮ ሃያ ዘጠኝ ሰዎች ላይ የመቁሰል አደጋ ደርሷል። ይህም አደጋ በቀጥታ የኦነግ ሸኔ ኃይሎች የፈጸሙት መሆኑ ተገልጿል።

ኮማንደር ሰለሞን ከመገደላቸው በፊት በቡራዩ የሆቴል ምረቃ ላይ ጃል መሮ የሚባለውን የዚህ ክፋት አቀናባሪ ምስል ጨረታ ለማቅረብ ሲሞከር ጸብ መነሳቱ ይታወሳል። በጸቡ “ይህን ከሃዲ የወያኔ ተላላኪ ፎቶ ለጨረታ ማቅረብ አይቻልም። የት እናውቀዋለን” ባሉ የቡራዩ አካባቢ ነዋሪዎች ላይ ጥቃት ለማድረስ ተሞክሮ በተነሳ ጸብ ከኖርዌይ የሄደችው የጨረታ አስተባባሪ ጨምሮ ጉዳት ደርሷል። ፖሊስ ይህንን ጉዳይ በቁጥጥር ሥር ባዋለ በቀናት ውስጥ የኮማንደሩ መገደል ጉዳዩን ከኦነግ ሸኔ ሽፍታ ጋር በቀጥታ እንደሚያገናኘው የበርካቶች እምነት ነው።

ከሽፍታነት ወደ ቅጥር ነፍሰ ገዳይነት ዕድገት ያሳየው የኦነግ ሸኔ የትግል ያሳሰባቸው፤ በፊት ሲጠየፉት ወደ ነበረው የሽግግር መንግሥት ጥያቄ፣ የብሔራዊ መግባባት ጥሪ፣ የመተባበር አዋጅ ተዛውረዋል። መንግሥት ደግሞ በር ዘግቶና ዙሪያውን ከቦ የደቆሰውን ኃይል እስከ መጨረሻ የማጥፋት ሥራ ላይ ተጠምዷል። ቃርሚያውንም ቢሆን በአካባቢ ሚሊሻና የሸኔ ተግባር ባማረራቸው ዜጎች ድጋፍ ሊቋጨው፣ እንዲሁም የህዝብ የሰላም ይከበር ጥያቄ የተበራከተ በመሆኑ በሁለት እግር የሚጫወቱትን እግራቸውን ለማሳጠር እርምጃ መውሰድ የመረጠ መሆኑንን የፖሊስ ኮሚሽነሩ ቃል ያረጋግጣል። ከወንጀሎቹ ጋር በተያያዘ የተያዙት ላይ ምርመራው ሲጠናቀቅ ይኸው ተግባር እንደሚፈጸም ይጠበቃል።

የኦነግ ሸኔ – ሦስተኛው እግር

የኦነግ ሸነኔ ሦስተኛው እግር ለውጡን ተከትሎ አቶ ዳውድን አጅቦ አዲስ አበባ ገብቶ ተመልሶ ከአገር የወጣው ኃይል ነው። ይህ ኃይል በውጪ አገር ሆኖ ገንዘብ እያሰባሰበ ጫካ ያለውን ኦነግ ሸኔ የሚቀልብ፣ ትጥቅ የሚገዛ፣ አዲስ አበባ ላለው “የሰላማዊ ትግል ቡድን” ሽፋን የሚሰጥ እንደሆነ እንቅስቃሴውን በቅርብ የሚያውቁ ይናገራሉ።

ይህ ሦስተኛው የኦነግ ሸኔ እግር መንግሥት የጣምራ ዜግነትን እንዲፈቅድ የሚወተውትና በዚሁ ጣምራ ዜግነት በመውሰድ አገር ቤት የፖለቲካ ስልጣን ማግኘት የሚሻ ቡድን ነው። ይህ ቡድን ጫካ ያለውን ኃይል የማገዝ አጀንዳ ተረክቦ ኡጋንዳ ከሚገኘው ዱጋሣ ባካኮ ጋር በመሆን የሚሠራ ነው። የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽንም ሆነ መከላከያ ሚኒስቴር ይህንኑ በወጉ ስለሚያውቁት አስፈላጊውን ስራ እየሰሩ መሆኑ ተሰምቷል።

አሁን ከዚሁ የኦነግ ሸኔ ሦስተኛው እግር የሚሰማው አዲስ ጉዳይ ቢኖር ዘመቻውን በውጪ አገር ማጠናከር ነው። ዜጎች ታፈኑ፣ ታሰሩ፣ ተገረፉ፣ ተሳደዱ በሚል መንግሥት የወሰደውን እርምጃና ወደፊትም የሚወስደውን እርምጃ እንዲያቆም ማሳጣት ላይ እንዲጠመዱ ነው አቅጣጫ የተቀመጠለት። የጎልጉል የአሜሪካ ሪፖርተር እንዳጣራው በውጪ ያለው የኦነግ ሸኔ በዚህ ተግባር ሲሰማራ፣ የአዲስ አበባው ኦነግ ሸኔ ደግሞ ስለ ብሔራዊ መግባባትና የአገራዊ እርቅ ጥሪ ላይ አብዝቶ ይጮሃል።

እንደ ቀድሞ መንገድ ዝጉ፣ አገልግሎት አቋርጡ የሚለው የክተት ጥሪ ስለማይሠራ ዘመቻው “ብሔራዊ እርቅ” ወደሚለው አዋጅ መዘዋወሩን የሰሞኑን መግለጫዎች የሚከታተሉ የሚሰጡት አስተያየት ነው። ፕሮፌሰር መረራ “አሁን ባለው ሁኔታ በገዢው ፓርቲ ውስጥም ሆነ በተቃዋሚ የፖለቲካ ኃይሎች መካከል የሚታየው ፍጥጫና መጠላለፉ አገሪቱን ወደማትወጣው የፖለቲካ ቅርቃር ውስጥ እየከተታት ይገኛል” ብለዋል፤ አክለውም “ይህም ዳግም በ1960ዎቹ ወደነበረው የመጠፋፋት ፖለቲካ አንዳይመልስን ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል” ሲሉ ለጀርመን ድምጽ ተናግረዋል።

በአሁኑ ውቅት በአገሪቱ በሚገኙ የፖለቲካ ኃይሎች መካከል እየሰፋ የመጣውን የፖለቲካ ፈጥጫ ወይም በእሳቸው አባባል political polarization ለማለዘብ የጋራ ብሔራዊ መግባባትን መፍጠር እንደሚገባ የተናገሩት በሃዋሳ በተደረገ የምክክር መድረክ ላይ ነው። “ሰጋሁ” ያሉት መረራ በዚሁ መድረክ የኢጄቶ ነፍሰገዳዮችና ደም አፍሳሾች ከእሥር እንዲፈቱ ግፊት እንደሚደረግ ሲጠየቅ ሲያጨበጭቡ ነበር።

የጃዋርን ድጋፍ እቀራመታለሁ በሚል ራሱን ኦነግ ሸኔ ውስጥ የቀረቀረው ኦፌኮ የቆመበት መንገድ የትኛው እንደሆነ አስረግጦ መናገር ባይቻልም፣ አሁን እየሆነ ባለው የኦነግ ሸኔ አካሄድ ግን አደጋ ውስጥ መግባቱን አባላቱ በቅሬታ እየገለጹ ነው። በተለይም በጃዋር የፖለቲካ መተጣጠፍ የተሰላቹ “ጃዋርን የሚጠሉ ኦፌኮንም ሳይፈልጉ ይለዩታል። በተለይም የዲቃላ ፖለቲካ ሰለባ እንዲሆኑ የተፈረደባቸው ኦሮሞዎች ጃዋር ካለበት ፖለቲካ እየሸሹ ነው” የሚል አስተያየት እየሰጡ ነው።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: daud ibssa, dhugassa bakako, Full Width Top, Middle Column, olf, olf shine

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule