• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች

February 17, 2020 09:13 pm by Editor 1 Comment

በቡራዩ የተከሰተውን ረብሻ አስመልክቶ ቢቢሲና የመንግሥት ሚዲያዎች የተሟላ መረጃ አለማቅረባቸውን የቡራዩ ነዋሪዎች ለጎልጉል ገለጹ። እነሱ እንዳሉት በአንድ መጠነኛ ሆቴል ምረቃ ላይ ለተነሳው ጸብ መነሻው በሽብር ተግባሩ የሚታወቀውና ጃል ማሮ (ኩምሣ ድርባ) የሚባለው የኦነግ ሸኔ ሽፍታ መሪ ፎቶ በጨረታ እንዲሸጥ መቀረቡን ተከትሎ ነው።

ነዋሪዎቹ ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ሲያስረዱ በምረቃው ላይ ጃል ማሮን የሚያወድሱ ሙዚቃዎች በዝተው ነበር። የውዳሴው ሙዚቃ መብዛቱ ከቡራዩና አካባቢው ወይም በተለምዶ የ“ሸዋ” የሚባሉትን ኦሮሞዎች አላስደሰተም። ሙዚቃው ቅይጥ እንዲሆን ቢጠየቅም ሰሚ አልነበረም።

“በዚህ ስሜት ውስጥ እያሉ ነው ጃል መሮ የሚባለው የኦነግ ሸኔ ሽፍታ መሪ ምስል ለጨረታ የቀረበው” ሲሉ በስፍራው የነበሩ ምስክሮች ያረጋግጣሉ። አክለውም “የዚህን ጊዜ ንትርክ ተነሳ። በንትርኩም “ይህ አገር ሻጭ፣ ከሃጂ፣ አሸባሪ፣ ሽፍታ ማን ስለሆነ ነው ፎቶው ለጨረታ የሚቀርበው? የት እናውቀዋለን? ለናንተም አልጠቀመም” በማለት ተቃውሞ ያላቸው ተቆጡ።

“ምክንያቱ በውል ለማይታወቅ ጉዳይ ጫካ ሆኖ ከወያኔ ጋር በማበር አገር የሚወጋ ከሃዲ ፎቶ ለጨረታ መቅረብ የለበትም በሚል አካባቢ ጠቅሰው መሟገት ጀመሩ። ጉዳዩ ከረረና እገሌ ከገሌ ሳይባል እርስ በእርስ መፈናከት ተጀመረ። የዚህን ጊዜ ፖሊስ ጣልቃ ገባ” በወቅቱ በቦታው የነበሩ ለጎልጉል የሰጡት ቃል ነበር።

እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ፣ አስቀድመው የተፈናከቱት እርስ በርስ መሆኑ እየታወቀ፣ የጸቡ መነሻ የጃል መሮ ፎቶ ጨረታ መቅረብና ከልክ በላይ በዘፋኞቹ መሞገስ መሆኑ እየታወቀ በተጠቀሱት ሚዲያዎች አለመጠቆሙ የቡራዩ ነዋሪዎችን አሳዝኗል።

አዲስ ስታንዳርድና ቢቢሲ አማርኛ ነዋሪነቷ ኖርዌይ የሆነች ሴት ላይ የደረሰውን ፍንከታ አጉልተው ዘገቡ እንጂ በጠርሙስ ጉዳት የደረሰባቸው በርካታ እንደሆኑ የቡራዩ ነዋሪዎች አስረድተዋል። 

ሃዊ ኤች ቀነኒ የምትባለው ይህቺው የኖርዌይ ነዋሪ “በወቅቱ ዘፍነን እየወጣን ነበር። የተጠራው ሰው እየተበተነ ባለበት ወቅት ፖሊሶች ወደ ሆቴሉ መጥተው ኦነግን አሞካሽታችኋል በሚል ነው ድብደባውን የጀመሩት” ስትል ለቢቢሲና ለአዲስ ስታንዳርድ የተናገረችው ሰባራና ያልተሟላ፣ ሃቁን የሸሸገ መሆኑንን በስፍራው የነበሩ ይናገራሉ። አንዳቸውም ሚዲያ ስለ ጃል መሮ ፎቶ ጨረታ ጉዳይ አላነሱም።

ነዋሪዎች የቡራዩ ፖሊስ ጥንቃቄ መርጦ መሸፋፈኑ ሌሎች ሚዲያዎችም ዋናውን ጉዳይ እንዲደብቁት ድጋፍ ማድረጉን በትችት ገልጸዋል። መጠነኛም ቢሆን ሆቴሉ ከወለጋ መጣ የተባለ ሰው እንደሆነም አክለው ተናግረዋል።

የጸቡን መነሻ ያስተዋሉና የተከታተሉት እንደሚሉት ጃል መሮ የሚባለው አሸባሪና ሽፍታ ላይ በኦሮሞ ተወላጆች ዘንድ የተለያየ አቋም መኖሩን ሲሆን፣ ጉዳዩ የመጪውን ምርጫ ውጤት አመላካች እንደሆነም ጠቁመዋል።

ጃል መሮ መንግሥትና ሕዝብ ላይ ጦርነት ያወጀ፣ የውጪ አገር ዜግነት ያላቸው ገንዘብ በማሰብሰብ የሚመሩት የኦነግ ሸኔ አንድ ጉራጅ መሆኑ ይታወቃል። ዜግነታቸውን መመለስ ስለማይፈልጉ ወደ ውጭ መውጣት የመረጡ ክፍሎች የሚረዱትና የሚመሩት፤ ጦርነት የመረጠ ቡድን በርካታ ንጹሃንን ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ መግደሉ በተደጋጋሚ ሲገለጽ ቆይቷል። 

በኖርዌይ የበርገን ነዋሪዎች እንዳሉት ከዚሁ ከጃል መሮ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ ኦሮሞዎች አካባቢና ጎራ በመለየት መነጋገር ካቆሙና የጎሪጥ መተያየት ከጀመሩ ሰንብተዋል። 

በአገር ውስጥ ደግሞ በ“ዲቃላ” የፖለቲካ ጦስ እየታመሰ በሚገኘው ኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ጎራ እየለዩ መከታከት እየተለመደ መጥቷል። በኦሮሞነት ከተመዘገበው ህዝብ ቁጥር ውስጥ እጅግ በርካታ የሆነው የተዳቀለ በመሆኑ በሰሞኑ የ“ዲቃላ” ፖለቲካ ዲስኩር ዙሪያ ይፋ ሆኖ ባይወጣም፤ ትንሽ የማይባል ቁጥር ያለው ሕዝብ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መንገድ ቁጣውን እየገለጠ ይገኛል።

ከወራት በፊት የኦሮሞ ድርጅቶች እና ታዋቂ ሰዎች በተገኙበት ሁሉም ተሰብሳቢዎች በሙሉ ድምጽ በወለጋ በአሸባሪነት እየተንቀሳቀሰ በሚገኘው ቡድን ላይ የማያዳግም እርምጃ እንዲወሰድ በፊርማ ማረጋገጣቸው ይታወሳል።

ጃል መሮ የተባለው ወንበዴ የመንግሥት ጥቃት በወለጋ በሚደርስበት ወቅት ትግራይ ስለመታየቱ የዓይን ምስክር ነን ያሉ በወቅቱ መናገራቸውን በተለይ በፌስቡክ የተሰራጨ ጉዳይ ነበር።

በውጭ አገር የሚኖሩ ኃይሎች ጃል መሮን የሚደግፉት በዚህችው ሃዊ ቀነኒ በኩል እንደሆነ በስፋት እየታወቀ ሳለ የጃል መሮ ፎቶ ለጨረታ በመቅረቡ ግጭቱ ስለመቀስቀሱ አንድኛውም ሚዲያ ያለመዘገቡ የቡራዩ ነዋሪዎችን ያሳዘነ ብቻ ሳይሆን ጥያቄ የፈጠረም ጉዳይ ሆኗል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: Full Width Top, jawar massacre, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Liberty says

    February 19, 2020 10:42 am at 10:42 am

    This law is another version of the same anti-terrorism law which is to be implemented in a different approach but with the same final objective.Its final objective is to suppress honest voices like the above websites who expose the covertly operating global network of satanic conspiracy.Any way after reading the above link you get the answer by your self.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule