• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች

February 17, 2020 09:13 pm by Editor 1 Comment

በቡራዩ የተከሰተውን ረብሻ አስመልክቶ ቢቢሲና የመንግሥት ሚዲያዎች የተሟላ መረጃ አለማቅረባቸውን የቡራዩ ነዋሪዎች ለጎልጉል ገለጹ። እነሱ እንዳሉት በአንድ መጠነኛ ሆቴል ምረቃ ላይ ለተነሳው ጸብ መነሻው በሽብር ተግባሩ የሚታወቀውና ጃል ማሮ (ኩምሣ ድርባ) የሚባለው የኦነግ ሸኔ ሽፍታ መሪ ፎቶ በጨረታ እንዲሸጥ መቀረቡን ተከትሎ ነው።

ነዋሪዎቹ ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ሲያስረዱ በምረቃው ላይ ጃል ማሮን የሚያወድሱ ሙዚቃዎች በዝተው ነበር። የውዳሴው ሙዚቃ መብዛቱ ከቡራዩና አካባቢው ወይም በተለምዶ የ“ሸዋ” የሚባሉትን ኦሮሞዎች አላስደሰተም። ሙዚቃው ቅይጥ እንዲሆን ቢጠየቅም ሰሚ አልነበረም።

“በዚህ ስሜት ውስጥ እያሉ ነው ጃል መሮ የሚባለው የኦነግ ሸኔ ሽፍታ መሪ ምስል ለጨረታ የቀረበው” ሲሉ በስፍራው የነበሩ ምስክሮች ያረጋግጣሉ። አክለውም “የዚህን ጊዜ ንትርክ ተነሳ። በንትርኩም “ይህ አገር ሻጭ፣ ከሃጂ፣ አሸባሪ፣ ሽፍታ ማን ስለሆነ ነው ፎቶው ለጨረታ የሚቀርበው? የት እናውቀዋለን? ለናንተም አልጠቀመም” በማለት ተቃውሞ ያላቸው ተቆጡ።

“ምክንያቱ በውል ለማይታወቅ ጉዳይ ጫካ ሆኖ ከወያኔ ጋር በማበር አገር የሚወጋ ከሃዲ ፎቶ ለጨረታ መቅረብ የለበትም በሚል አካባቢ ጠቅሰው መሟገት ጀመሩ። ጉዳዩ ከረረና እገሌ ከገሌ ሳይባል እርስ በእርስ መፈናከት ተጀመረ። የዚህን ጊዜ ፖሊስ ጣልቃ ገባ” በወቅቱ በቦታው የነበሩ ለጎልጉል የሰጡት ቃል ነበር።

እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ፣ አስቀድመው የተፈናከቱት እርስ በርስ መሆኑ እየታወቀ፣ የጸቡ መነሻ የጃል መሮ ፎቶ ጨረታ መቅረብና ከልክ በላይ በዘፋኞቹ መሞገስ መሆኑ እየታወቀ በተጠቀሱት ሚዲያዎች አለመጠቆሙ የቡራዩ ነዋሪዎችን አሳዝኗል።

አዲስ ስታንዳርድና ቢቢሲ አማርኛ ነዋሪነቷ ኖርዌይ የሆነች ሴት ላይ የደረሰውን ፍንከታ አጉልተው ዘገቡ እንጂ በጠርሙስ ጉዳት የደረሰባቸው በርካታ እንደሆኑ የቡራዩ ነዋሪዎች አስረድተዋል። 

ሃዊ ኤች ቀነኒ የምትባለው ይህቺው የኖርዌይ ነዋሪ “በወቅቱ ዘፍነን እየወጣን ነበር። የተጠራው ሰው እየተበተነ ባለበት ወቅት ፖሊሶች ወደ ሆቴሉ መጥተው ኦነግን አሞካሽታችኋል በሚል ነው ድብደባውን የጀመሩት” ስትል ለቢቢሲና ለአዲስ ስታንዳርድ የተናገረችው ሰባራና ያልተሟላ፣ ሃቁን የሸሸገ መሆኑንን በስፍራው የነበሩ ይናገራሉ። አንዳቸውም ሚዲያ ስለ ጃል መሮ ፎቶ ጨረታ ጉዳይ አላነሱም።

ነዋሪዎች የቡራዩ ፖሊስ ጥንቃቄ መርጦ መሸፋፈኑ ሌሎች ሚዲያዎችም ዋናውን ጉዳይ እንዲደብቁት ድጋፍ ማድረጉን በትችት ገልጸዋል። መጠነኛም ቢሆን ሆቴሉ ከወለጋ መጣ የተባለ ሰው እንደሆነም አክለው ተናግረዋል።

የጸቡን መነሻ ያስተዋሉና የተከታተሉት እንደሚሉት ጃል መሮ የሚባለው አሸባሪና ሽፍታ ላይ በኦሮሞ ተወላጆች ዘንድ የተለያየ አቋም መኖሩን ሲሆን፣ ጉዳዩ የመጪውን ምርጫ ውጤት አመላካች እንደሆነም ጠቁመዋል።

ጃል መሮ መንግሥትና ሕዝብ ላይ ጦርነት ያወጀ፣ የውጪ አገር ዜግነት ያላቸው ገንዘብ በማሰብሰብ የሚመሩት የኦነግ ሸኔ አንድ ጉራጅ መሆኑ ይታወቃል። ዜግነታቸውን መመለስ ስለማይፈልጉ ወደ ውጭ መውጣት የመረጡ ክፍሎች የሚረዱትና የሚመሩት፤ ጦርነት የመረጠ ቡድን በርካታ ንጹሃንን ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ መግደሉ በተደጋጋሚ ሲገለጽ ቆይቷል። 

በኖርዌይ የበርገን ነዋሪዎች እንዳሉት ከዚሁ ከጃል መሮ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ ኦሮሞዎች አካባቢና ጎራ በመለየት መነጋገር ካቆሙና የጎሪጥ መተያየት ከጀመሩ ሰንብተዋል። 

በአገር ውስጥ ደግሞ በ“ዲቃላ” የፖለቲካ ጦስ እየታመሰ በሚገኘው ኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ጎራ እየለዩ መከታከት እየተለመደ መጥቷል። በኦሮሞነት ከተመዘገበው ህዝብ ቁጥር ውስጥ እጅግ በርካታ የሆነው የተዳቀለ በመሆኑ በሰሞኑ የ“ዲቃላ” ፖለቲካ ዲስኩር ዙሪያ ይፋ ሆኖ ባይወጣም፤ ትንሽ የማይባል ቁጥር ያለው ሕዝብ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መንገድ ቁጣውን እየገለጠ ይገኛል።

ከወራት በፊት የኦሮሞ ድርጅቶች እና ታዋቂ ሰዎች በተገኙበት ሁሉም ተሰብሳቢዎች በሙሉ ድምጽ በወለጋ በአሸባሪነት እየተንቀሳቀሰ በሚገኘው ቡድን ላይ የማያዳግም እርምጃ እንዲወሰድ በፊርማ ማረጋገጣቸው ይታወሳል።

ጃል መሮ የተባለው ወንበዴ የመንግሥት ጥቃት በወለጋ በሚደርስበት ወቅት ትግራይ ስለመታየቱ የዓይን ምስክር ነን ያሉ በወቅቱ መናገራቸውን በተለይ በፌስቡክ የተሰራጨ ጉዳይ ነበር።

በውጭ አገር የሚኖሩ ኃይሎች ጃል መሮን የሚደግፉት በዚህችው ሃዊ ቀነኒ በኩል እንደሆነ በስፋት እየታወቀ ሳለ የጃል መሮ ፎቶ ለጨረታ በመቅረቡ ግጭቱ ስለመቀስቀሱ አንድኛውም ሚዲያ ያለመዘገቡ የቡራዩ ነዋሪዎችን ያሳዘነ ብቻ ሳይሆን ጥያቄ የፈጠረም ጉዳይ ሆኗል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: Full Width Top, jawar massacre, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Liberty says

    February 19, 2020 10:42 am at 10:42 am

    This law is another version of the same anti-terrorism law which is to be implemented in a different approach but with the same final objective.Its final objective is to suppress honest voices like the above websites who expose the covertly operating global network of satanic conspiracy.Any way after reading the above link you get the answer by your self.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule