• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ

February 13, 2020 09:28 am by Editor Leave a Comment

በዚህ ሳምንት መጀመሪያ አካባቢ ከጅማ ዞንና ከከተማዋ የተውጣጡ የተለያዩ የማህበረሰብ አካላት የተሳተፉበትና በህዝቦች አብሮነት እሴት ላይ ትኩረቱን አድርጎ በተዘጋጀው መድረክ ላይ ተሳታፊዎች ምን አሉ?

የህዝቡን አብሮ የመኖር እሴት የሚሸረሽሩ ተግባራት ተነቅፈዋል።

የኦሮሞ ህዝብ በሰላም የመኖር እሴትና አኩሪ ባህል እንዳለው ተብራርቷል።

በመሰዳደብ፣ ጥላቻና ነቀፋ ላይ ያተኮሩ ተግባራትን ሊወገዙ እንደሚገባቸው ሀሳብ ተሰጥቷል።

ህዝቡን እንወክላለን የሚሉ አካላት እየተፈፀሙ ያሉ የህዝቡን አብሮነት እሴት የሚሸረሽሩ ተግባራት ተወግዘዋል።

የተወሰኑ የውይይት ተሳታፊዎች ሀሳብ፦

“ከየትኛውም ብሄርም ይሁን ሃይማኖትም ይሁን ክልል ተንኮል የሚያስብ ሰው የትም አይደርስም። በመሳደብ የሚመጣ ለውጥ የለም።”

“አዋቂና ለኦሮሞ ተስፋ ናቸው ከምንላቸው ሰዎች ያየነው ነገር የማይጠበቅ ነው። ይህ በጣም የሚያሳዝን ነው። እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም”

“ሰውነት የሚለካው በስራ ነው እንጂ በስድብ አይደለም። የአብይን ስራ ማሳነስ በእጅ መዳፍ የፀሃይን ብርሃን መከላከል እንደማለት ነው።”

“ሽማግሌ ሆኖ ልትፈርስ የነበረችን ሀገር ያዳነና ሰላምን ያወረደው ጠ/ሚ አብይ አህመድ ነው። ይህን ደግሞ ዓለም ሁሉ መስክሮለታል። እኛ እንደ ቄሮ ማንም ሰው እንዳሻው የሚጫወትብን መሆን አይገባንም።”

“እኛን እየሰደበ እና የአንድ አባት ልጆችን ለማባላት የሚመጣብንን ሰው አንፈልግም። የሚያጋጨንን ሰው በፍፁም አንቀበልም”

“እኛ ከአባጅፋር  የተማርነው አቃፊነትንና በአንድነትና በወንድማማችነት በጋራ መኖር ነው። እኛ ረገጣና ጭቆናን ነው የምንቃወመው”

“ስድብና ጥላቻ በየትኛውም ሃይማኖት ተቀባይነት የለውም። ህብረተሰቡ አብሮነቱን የሚያጠናክር እሴቶችን ሊጠብቅ ይገባዋል”

ዋልታ ያጠናከረው ቪዲዮ ከዚህ በታች ይገኛል፤

ከዚህ ሌላ ሐሙስ በጅማ ስታዲየም የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድን የለውጥ አመራር የሚደግፍ ዝግጅት እየተካሄደ ይገኛል። በርካታ ቁጥር ያለው የጅማ እና አካባቢው ነዋሪ ከጥዋት ጀምሮ ወደ ስታዲየም ሲያመራ እንደነበር የጅማ ከተማ ቲክቫህ ቤተሰቦች ገልፀዋል።

ምን አይነት መልዕክት ነው እየተላለፈ የሚገኘው ብለን የጅማ ቲክቫህ ቤተሰቦቻችን ጠይቀናል፦

  • ዶ/ር አብይ አህመድ የሰራውን በጎ ስራ በማጣጣል የሚመጣ ለውጥ የለም፤ ሀሳብ ያላቸው ለህዝቡ ሀሳብ ያቅርቡ።
  • ስድብ፣ እና ጥላቻ ባህላችን አይደለም፤ የሀገር መሪዎችን በአደባባይ መሳደብና ማንቋሸሽ ከባህላችን ያፈነገጠ ነው።
  • ሀገር ማስተዳደር የሚገልጉ ሰዎች ሀሳባቸውን ሽጠው በምርጫ ይመረጡ፤ ከዛ ውጪ ስድብ እና ማንቋሸሽ፣ የስም ማጥፋት ዘመቻ ማካሄድ ተገቢነት የለውም።
  • እኛም ዶክተር አብይ አህመድ ነን!
  • የተለያዩ ሀሰተኛ መልዕክቶችን በማስተላለፍ የኦሮሞን ህዝብ ለመከፋፈል የሚሰራው ስራ ሊቆም ይገባል።
  • ዶ/ር አብይ የሰላም እና የብልፅግና አባት ነው!
  • እኛ የአባጅፋር ልጆች አቃፊዎች ነን!
  • ስድብ እና ጥላቻ ተቀባይነት የለውም!
  • ጅማ መሬትም ሰውም አለ!
  • ጊዜው የዶክተር አብይ ነው!
  • ከዶክተር አብይ ጋር ወደብልፅግና እንሻገራለን!

ሠልፎቹን መንግሥት አበል ከፍሎ ነው ያስተባበረው?

የማህበራዊ ሚዲያዎች ርዕስ የነበረው ጉዳይ ትላንት በጅማና አጋሮ የተደረጉት ሰልፎች መንግስት አበል ሰጥቶ ያስተባበረው ነው እንጂ ሰዎች ፈልገው ያደረጉት አይደለም የሚል ነበር።

ለዚህ ጉዳይ ቢቢሲ ዛሬ ይዞት በወጣው ዘገባ ላይ የሠልፉ አስተባባሪ እንዲሁም ተሳታፊ የጅማ ወጣቶች ሊግ ኃላፊ ድማሙ ንጋቱ፦ “አበል መክፈል ይቅርና ቲሸርቶቹንና መፈክሮችን ለማሳተም እንኳ መንግሥት ምንም ዓይነት ገንዘብ አላወጣም” የሚል ምላሽ ሰጥቷል።

ምንጭ፤ የቲክቫህ ጅማ ቤተሰቦች

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Left Column, Politics Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule