• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለዋዜማ ሬዲዮ – የህዳሴውን ግድብ ዜናችሁን ላስተካክልላችሁ

February 6, 2020 01:19 am by Editor 2 Comments

የውሃ ሃብት ባለሙያ ነኝ፤ የግድቡ ጉዳይ ቀጥታ ከሙያዬ ጋር ባይገናኝም እንደዜጋ ሁኔታውን በቅርብ እከታተላለሁ፤ ፖለቲካንም እንዲሁ። የዋዜማን ሰዎች ዋዜማ ሳትሆኑ ነው የማውቃችሁ፤ ካገር ከመውጣታችሁ በፊት ማለቴ ነው። የማውቃችሁም በግል ሳይሆን እንደማንኛውም የሚዲያ ተጠቃሚ ነው፤ ስለዚህ እናንተ አታውቁኝም። አሁንም ዋዜማን እከታተላለሁ። ከዳያስፖራ ከሚመነጩት የዜና ዘገባዎችና መረጃዎች የእናንተ በተሻለ መጠን ተዓማኒነትና ሥርዓት የያዘ ነው ብዬ ስለማምን አነባችኋለሁ።

“ኢትዮጵያን ቋሚ ባለዕዳ የሚያደርገው የህዳሴ ግድብ ስምምነት ላይ መንግስት የመፈረም ፍላጎት እያሳየ ነው” በሚል ርዕስ ያወጣችሁትን ዘገባ አንብቤዋለሁ። ዘገባው እንደሚለው ለረጅም ጊዜ የተጠበቀውን ሰነድ ስምምነት እንድትፈርም ኢትዮጵያ ግፊት እየተደረገባት እንደሆነ፤ ይህም “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ የሚያደርግ መሆኑን”፤ ረቂቅ ሰነዱ እጃችሁ እንደገባ፤ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ላይ ተጽዕኖ እያደረጉባቸው እንደሆነ፣ ኢትዮጵያ ካልፈረመች ከአሜሪካ የምታገኘው ድጋፍ መስተጓጎል እንደሚገጥመው ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ “በገደምዳሜ መጠቆማቸው” በእናንት በኩል ግምት እንዳለ፣ ወዘተ የሚያትት ነው።

ዜናው መረጃ የሚያስተላለፍ መሆን ሲገባው ግምት፣ መላምት፣ ጠማማነትና ምኞትን የሚገልጽ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ከዚህ ይልቅ ግን የዘነጋው አንድ ትልቅ እውነታ አለ – ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ስምምነቱ እንዳይፈረም መመሪያ ስለመስጠታቸው ነው።

ሰኞ ዕለት ጠ/ሚ/ር ዐቢይ በተወካዮች ም/ቤት በኩል ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ባስተላለፉት መልዕክት ላይ “የህዳሴ ግድብ ስምምነት ፊርማ እንዲዘገይ አመራር ሰጥቻለሁ” ብለዋል። ዶ/ር ዐቢይ ረቂቁን ተመለከቱ፣ የትራምፕን፣ የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት እና የአሜሪካውን የገንዘብ ሚ/ር አነጋገሩ፤ ፍላጎታቸው ምን እንደሆነ በስልክ ንግግራቸው ተረዱ፤ ረቂቁ እንዳይፈረም ትዕዛዝ ሰጡ። እንዲያውም በውጭ አገር ከሚገኙ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች የሚሰጣቸው የሙያ ምክር ጠቃሚ መሆኑን በመጥቀስ ምስጋና ሁሉ አቅርበው ነበር። ይህ ሊያስመሰግናቸውና እናንተም ባወጣችሁት ጽሁፍ መግለጽ የሚገባችሁ ነበር። የኢትዮጵያን ጥቅም አሳልፈን አንሰጥም ነው ያሉት!

የውሃ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትራችን ዶ/ር ኢንጂነር ስለሺም ረቡዕ ዕለት ለሚዲያ ሰዎች ሲናገሩ “በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ በሚደረገው ስምምነት የኢትዮጵያን በወንዙ የመጠቀም መብት በዘላቂነት በማያስጠብቅ ሁኔታ አንድም ቃል ከተካተተ ኢትዮጵያ” አትፈርምም ነው ያሉት። ይህንንም ጨምረዋል፤ “የግድቡ የውኃ ሙሌትና አለቃቀቅን በሚመለከት ውይይት የተደረገ ሲሆን፥ በተለይም ድርቅ በሚከሰትበት ወቅት የሦስቱን ሀገራት ጥቅም በሚያስጠብቅ መልኩ ተካሂዷል” ነው ያሉት። መቼም ዐቢይን ባታምኗቸው ዶ/ር ስለሺን የምትጠራጠሯቸው አይመስለኝም።

ይህ ሁሉ እውነታ እያለ ኢትዮጵያን ባለዕዳ የሚያደርግ ስምምነት ሊፈረም ነው ብሎ መናገሩ የሚዲያችሁን ተዓማኒነት ትልቅ ጥያቄ ላይ ጥሎታል፤ በተለይ ለእኔ። ሌሎቹንም ዘገባዎቻችሁን በጥንቃቄና በዓይነቁራኛ እንዳነብ ያስገደደኝ ሆኗል። በተለይ እናንተ ከለውጡ ጋር በተያያዘ በአገር በቀል መፍትሔ ፍለጋ ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ እያደረጋችሁ ያላችሁ በዚህ መልኩ ይህንን ዘገባ ማውጣታችሁ “ውይ እንደነ እንትና ዋዜማም …” አስብሎኛል። ልድገመውና – ረቂቁ አልተፈረምም፤ እንዳይፈረም ዶ/ር ዐቢይ ትዕዛዝ ሰጥተዋል። እንደ መሪ ይህ ትክክለኛና ተጠቃሽ ተግባር ነው።

እናንተ በዘገባችሁ ሌላው ያከላችሁት ነገር ኢትዮጵያ ተጽዕኖ እየተደረገባት ነው፤ እነ ዶ/ር ዐቢይም ሊፈርሙ እየተዘጋጁ ነው የሚል ነው። ለዚህም ያቀረባችሁት መላምት ኢትዮጵያ ካልፈረመች አሜሪካ የምትሰጠውን ዕርዳታ መያዣ አድርጋባታለች የሚል ነው። ሌላውና ውሃ የማይቋጥረው መላምታችሁ ትራምፕ ለፍልስጤምና እስራኤል ያቀረቡት የሰላም ሃሳብ “በመላው የዓረቡ አለም ተቀባይነት ባለማግኘቱ” ግብጽ የአረቡ ዓለም ተጽዕኖ ፈጣሪ በመሆኗ ይህንን ሰነድ አረቡ ዓለም እንዲቀበል ካግባባች “(ለ)ውለታዋ የህዳሴ ግድብ እንደ እጅ መንሻ” እንደቀረበላት ነው።

ይህንን በጣም የወረደ አመክንዮ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ሲጀመር የትራምፕን የሰላም ዕቅድ “መላው የዓረቡ አለም” አልተቃወመውም። ሳዑዲ አረቢያ፣ አረብ ኤሜሬትስ፣ ግብጽ፣ ኳታርና ሞሮኮ ከአዎንታዊ አስተያየት እስከ ጥንቃቄ የተሞላበት ድጋፍ ሰጥተዋል። በተለይ ሳዑዲ አረቢያ ከመቼውም በተለየ መልኩ እስራኤልን በመደገፍ መቆሟ አነጋጋሪ ጉዳይ ሆኗል።

ሌላውና ዋንኛው ነጥብ በዚህ የፍልስጤም ተወካይ ወይም መሃሙድ አባስ በሌሎበት ትራምፕና የእስራኤሉ ጠ/ሚ/ር ኔታንያሁ ብቻቸውን ይፋ ያደረጉት “ፕላን” ፍልስጤምን ታሳቢ ያላደረገ የፖለቲካ ቁማር ነው። ኔታኒያሁ ከሙስና እና ማጭበርበር ጋር በተያያዘ ትልቅ ክስ ተመሥርቶባቸው ግራ ገብቷቸዋል። ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ ደግሞ አገር አቀፍ ምርጫ ይጠብቃቸዋል። ለሕዝባቸው “የሚሸጡት” የምርጫ ሸቀጥ ያስፈልጋቸዋል። ለዚህም ደግሞ እስራኤልን በጭፍን ከሚደግፍ ፕላን የተሻለ አይኖርም።  

ትራምፕ በዩክሬይን ጉዳይ ከፍተኛ ቅሌት ገጥሟቸው የውጭ ጉዳይ አመራር ላይ ዜሮ ናቸው የሚለው ቁጥር የጨመረበት ወቅት ላይ ናቸው። እጅግ ውስብስብ የሆነውን የፍልስጤምና እስራኤል ጉዳይ ለመፍታት ከመድፈር አልፎ የሰላም ዕቅድ ይዘው ብቅ ማለታቸው የውጭ ጉዳይ ፖለቲካ ላይ በሳል ናቸው ከማስባል ባለፈ ለዚህ ዓመቱ (የፈረንጆች) የአሜሪካ ምርጫ ጥሩ ደጋፊ እንዲያስገኝላቸው ታልሞ የተሠራ ነው። እሳቸውም የራሳቸውን ዕቅድ “የክፍለዘመኑ ስምምነት” በማለት የጠሩት ያለምክንያት አይደለም።

ሌላው ቢቢሲ እንደዘገበው ይህ ዕቅድ ለትራምፕ የዚህ ዓመት ምርጫ ትልቅ ድጋፍ የሚያሰጣቸው ነው፤ በተለይ በ2016ቱ ምርጫ በጭፍን ለደገፏቸው የኢቫንጀሊካል (ወንጌላውያን) ክርስቲያኖች። እነዚህ ኢቫንጀሊካሎች ለእስራኤል ጭፍን ድጋፍ ያላቸው ከመሆን በተጨማሪ ለትራምፕ ምርጫ ትልቅ የገንዘብ ድጋፍ አድራጊዎችም ናቸው። ያለፈውን ዓይነት ድጋፍ በዚህኛው የምርጫ ዘመቻ ለማግኘት ይህንን መሰሉ የመካከለኛው ምስራቅ ዕቅድ ማውጣት ወሳኝ ነው። በዚህ ላይ የትራምፕ ምክትል ማይክ ፔንስና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማይክ ፖምፔዎ ተጠቃሽ ኢቫንጀሊካል ናቸው።

ይህ የፖለቲካ ጥቅም ከማስገኘት ያላለፈ ምኞት ያለውንና ፍልስጤምን ያላሳተፈ ዕቅድ የተቃወሙትን አረብ አገራት ለማሳመን ከግብጽ ይልቅ ባልተለመደ ሁኔታ ለእስራኤል ልዩ ድጋፍ እያደረገች ያለችውና ዕቅዱን የደገፈችው ሳዑዲ አረቢያ የተሻለችና ዋንኛ ተመራጭ ነች።

ለማንኛውም እናንተ እጃችን ገብቷል ያላችሁትን ረቂቅ፥ የስምምነት ሰነድ ሆኖ እንዳይፈረም ጠ/ሚ/ር ዐቢይ መመሪያ ሰጥተውበታል። ይህ መጠቀስ የሚገባው ትልቅ ሥራ ነው። ዕቅዱን የተቃወሙትን የአረብ አገራት ለማሳመን ግብጽ የተሻለች ነች፤ ይህንንም ካደረገች የአባይን ግድብ ስምምነት እሷን እንዲጠቅም ተደርጎ እንዲወሰን ይደረጋል የሚለውም የዓለምን በተለይም የአሜሪካንና የመካከለኛው ምስራቅ ፖለቲካ ያላገናዘበ ስንኩል “ትንታኔ” ነው።

ዋዜማዎች እንደ አንዳንድ ስም አይጠሬ ጭፍን ሚዲያ እንዳትሆኑ ተጠንቀቁ። ውሃ ሲወስድ እያሳሳቀ ነው።

ባለሙያው ነኝ       


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Left Column, Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Segel says

    February 6, 2020 06:20 pm at 6:20 pm

    (ፕሬዚዳንት ትራምፕ ጠ/ሚ/ር ዐቢይ ላይ ተጽዕኖ እያደረጉባቸው እንደሆነ፣ ኢትዮጵያ ካልፈረመች ከአሜሪካ የምታገኘው ድጋፍ መስተጓጎል እንደሚገጥመው ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ “በገደምዳሜ”…) Hahaha ?
    Quid pro quo

    Reply
  2. ተፈራ says

    February 8, 2020 12:40 am at 12:40 am

    ከዚህ ከላይ ከተቀመጠው መቃወሚያ በሁዋላ የዋዜማ አቋም ወይም ምላሽ ምን እንደሆነ ባልረዳም የሁሉንም ወገን ሃሳብ ሳነብ የታየኝና የገባኝ አንድ ጉዳይ ቢኖር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ባገዱት ወይም ፊርማ እንዳይፈረም ካዘዙ በራሱ የዜናው አስፈላጊነት በዜና ደረጃ መሆን ያለበት አይመስለኝም። ምክንያቱም ዋዜማ አገኘሁት ያለው ሰነድ ነው ፊርማ እንዳይኖርበት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያስቆሙት። ስለዚህ ባደባባይ፣ ህዝብ እየሰማ፣ ዲፕሎማቶችና የውጭ አገር ሚዲያዎች እየቀዱት፣ ግብጾች እየሰሙ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ” እንዳትፈርሙ” ካሉ ሌላ ተከላካይ ጠበቃ የሚያሻቸው አይሆንም።
    እንደ መሪ አቋም ወስደዋል። እንደ መሪ የወሰዱትን አቋም ለፓርላማና ለህዝብ ገልጠዋል። እንደ መሪ ቃል የገቡትን የኢትዮጵያን ጥቅም ማስጠበቅቃቸውን አረጋግጠዋል። ታዲያ እኝህ ሰው በዚህ ጉዳይ ላይ መመሪያ ሰጡ፣ ቃላቸውን ጠበቁ፣ መመሪያ ሰጡ በሚል ቃላቸውና ተጋባራቸው ተጠቅሶ ዜናው መሰራት ሲገባው እሳቸው የተቃወሙትንና መመሪያ በመስጠት ያስቆሙትን የድርድር ሃሳብ አስመልክቶ እንዴት ሰይፍ ይመዘዝባቸዋል?
    ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ አገራቸውን ለማገልገል ትልቅ ክፍያና ኑሮ ጥለው ወደ አገራቸው የገቡ ድንቅ ባለሙያ፣ አገር ወዳድና ባለ መልካም ተሞክሮ መሆናቸውን የሚያውቋቸው ይመሰክራሉ። እሳቸውና ቲማቸው ይህንኑ በተደጋጋሚ ያረጋግጣሉ። እናም እኚህንም ሰው .…

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule