የጀርመን ድምጽ ሬዲዮ ህወሃት በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ስላወጀው "አትኑሩ" አዋጅና የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ስለሰጡት አስተያየቶች ያቀናበረውን ከዚህ በታች እንዳል አስፍረነዋል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እና ኢትዮጵያ * "በብሔራዊ ደረጃ የመጣ ጥፋት ነዉ" የኢትዮጵያ መንግሥት በቅርቡ የደነገገዉን የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ የሚያጠናክሩ ማብራሪያዎችን ይፋ ከተደረጉ ወዲህ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ስጋታቸዉን መግለጽ ጀምረዋል። የጀርመን መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ጋር ከተነጋገሩ በኋላ፤ ይደረጋሉ የተባሉት መሻሻሎች፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ትንታኔ ይፋ ሲደረግ በተቃራኒዉ መንገድ የሚጓዝ ነገር መኖር እንደሚያመላክት ነዉ የተጠቀሰዉ። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከዉጭ የሚሰራጩ የሽብርተኛ ድርጅቶች ልሳን ያላቸዉን መገናኛ ብዙሃን ማዳመጥ ያግዳል፤ … [Read more...] about “የጣዕር ጊዜ አዋጁ” እና ኢትዮጵያ
Archives for October 2016
INTERNATIONAL ALERT REGARDING ETHIOPIA TO WESTERN POLICY MAKERS, DONORS AND STAKEHOLDERS
Open letter to the Western Governments and Donor Countries concerning the deteriorating situation of human rights and political instability in Ethiopia that is shifting from bad to worse day after day. Your Excellency, The State of Emergency declared by the ruling ethnic apartheid regime of the TPLF/EPRDF, which is an attempt to enforce draconian measures to repress the emerging vocalization of discontent by the people of Ethiopia, will undoubtedly fail, with unknown results. Some of these … [Read more...] about INTERNATIONAL ALERT REGARDING ETHIOPIA TO WESTERN POLICY MAKERS, DONORS AND STAKEHOLDERS
“… የጦር ኃይል … እና የብእር ኃይል …” ሃዲስ አለማየሁ
" ... ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ አሁን እስካለንበት ድረስ ታሪኩን መለስ ብለን ብንመለከት በሰው ዘር ላይ ግዛታቸውን ለመዘርጋት፣ ሰውን ባካልም ሆነ በመንፈስ ለመግዛት፣ ሁለት ተቃራኒ ኃይሎች ሲታገሉ እናያለን፡፡ ከነዚህ አንዱ የሀይለኞች፣ ያጥቂዎች፣ የጦር ኃይል፣ ሁለተኛው የደራሲያን የብእር ኃይል ናቸው፡፡ "የጦር ኃይል በየጊዜው፣ በየቦታው የሚነሱ ኃይለኞች ሰራዊት አደራጅተው፣ የጦር መሳሪያ አከማችተው፣ ሰውን እየጨቆኑ ለግል ድሎታቸውና ፍላጎታቸው አገልጋይ የሚያደርጉበት እውር ሀይል ነው፡፡ የብእር ኃይል በየጊዜው በየቦታው የሚነሱ ታላላቅ ደራሲያን ከስው ተለይተው፣ ከብእርና ከወረቀታቸው ጋር በየቤታቸው ተዘግተው፣ ምስጢረ ፍጥረትን እየመረመሩ፣ አዳዲስ ነገር እየፈጠሩ፣ ሰውን ከድንቁርና ሰንሰለት ተፈትቶ፣ ከእንሰሳ ባህርያት ጠርቶ፣ የመንፈስና የአካል ነጻነት አግኝቶ፣ ስርአት ያለው … [Read more...] about “… የጦር ኃይል … እና የብእር ኃይል …” ሃዲስ አለማየሁ
“ባንዶች ሀገራችሁን እንደጎዳችሁ ዛሬ ደግሞ የምትክሱበት ጊዜ ነው” ጄኔራል ለማ ገ/ማርያም
ጄኔራል ለማ ገብረማርያም የኢጣልያ ፋሺሽቶች ኢትዮጵያን በወረሩበት ዘመን በጽንዓት ተዋግተው ከነበሩት የኢትዮጵያ አርበኞች አንደኛው ነበሩ። በፈጸሙት አኩሪ ትግል ኢጣልያዊ ስለ መማረካቸውና አሁን ደግሞ ሕይወተ ሕልፈት ያጋጠማቸው መሆኑን፤ Ethiopian Media Forum የዘገበውን ከዚህ በታች መመልከት ይቻላል። ጄኔራል ለማ ለሐገር ነጻነትና ክብር ካከናወኑት እጅግ የሚያኮራ ተግባር ውስጥ አብሮ ሊደነቅ የሚገባው አንዱ አስተዋጽኦዋቸው ቫቲካን በፋሺሽቱ ወረራ ዘመን ለፋሺሽት ኢጣልያ ላከናወነችው ያልተቆጠበ ድጋፍ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እንድትጠይቅ በማመልከት ከዚህ ጋር የተያያዘውን ግልጽ ደብዳቤ ማስተላለፋቸው ነው። (ደብዳቤውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) በልጅነታቸው ጊዜ ብቻ ሳይሆን በሽምግልናቸው፤ በ97 እድሜያቸው ጭምር ጀኔራል ለማ ለሐገራቸው ያልተቆጠበ ጥረት ያበረክቱ … [Read more...] about “ባንዶች ሀገራችሁን እንደጎዳችሁ ዛሬ ደግሞ የምትክሱበት ጊዜ ነው” ጄኔራል ለማ ገ/ማርያም
“ምጽአተ ዐማራ” አዲስ መጽሐፍ
ይህ መጽሐፍ ባለ 657 ገፆች ነው። በዘጠኝ ምዕራፎች ተከፋፍሏል። እነርሱም፦ የኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት መከፋፈል፣ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ኃይማኖት ተከታዩና ዐማራው የከፈሉት ዋጋ የኢትዮጵያ አንድነት ትንሣኤ፣ የዐማራው የአንድነትና የፀረ-አንድነት ትግል ውጤት ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ፤ የፍፁማዊ ዘውዳዊ አገዛዝ የአንድነት ግንባታ ሂደት ድምድም እና የኢትዮጵያ ዳግም ብተና ጽንስ የለውጥ ፈላጊው ትውልድ የኃይል አሰላለፍ ዘረኛው የትግሬ-ወያኔ ከ1972 እስከ 2007 ዓም ድረስ በዐማራው ነገድ ላይ ያደረሰው የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል ስለ ዐማራና ስለ ኢትዮጵያዊነት ምሑራን ምን ይላሉ? የመላው ዐማራ ሕዝብ ድርጅት (መዐሕድ)፦ ዐማራው ላይ የደረሰው ሰቆቃ የወለደው ነፍስ አድን ድርጅት ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት፦ የአሥራት ዘር ፍሬ … [Read more...] about “ምጽአተ ዐማራ” አዲስ መጽሐፍ
ደንቁሩ በአዋጅ!
እግዚአብሔር ዓይንን ፈጠረና እዩበት አለ፤ እግዚአብሔር ጆሮን ፈጠረና ስሙበት አለ፤ እግዚአብሔር አእምሮን ፈጠረና አስቡበት አለ፤ እግዚአብሔር አንደበትን ፈጠረና ተናገሩበት አለ፤ ወያኔ አይሆንም አለ! በዓይንህ አትይ፤ በጆሮህ አትስማ፤ በአእምሮህ አታስብ፤ በአንደበትህ አትናገር፤ አበሻ ተዋረደ! ዓለም እየሰማ ድንቁርና ታወጀበት! ማን ያሸንፋል? እግዚአብሔር አለ፤ ወይስ ወያኔ አለ? (ምንጭ: Prof. Mesfin Wolde-Mariam Blog) … [Read more...] about ደንቁሩ በአዋጅ!
ላም እሳት ወለደች!
አጉል ዘመን ገጥሟት በረት ብትከሳ፤ ከብቶች በመዥገሮች አዩ ብዙ አበሳ፡፡ ጡቶቿን አቃጣይ የነበልባል ጥጃ ላም እሳት ወለደች፤ ብ’ተው በማይተዋ ዘልለው ባልጠገቡ ወይፈኖች ነደደች፡፡ የከበረው ባህል ባለጌ ረጋግጦት እንደጨው ቀለለ፤ ወፍ ዘራሾች ነግሠው ባጥለቀለቁት ደም ምድር ተበከለ፡፡ አዎ፣ ላም እሳት ወለደች! እንደዮዲት ጉዲት እቶኑ የሚፋጅ፤ ዕረፍት በማያ’ቅ ሠይፍ እንደነደርቡሾች እንደግራኝ አህመድ፤ ጭንቅላትን ገምሶ አንገትን ቆራርጦ ዜጎችን የሚያነድ፡፡ “አጥንትና ደሜ ይሄው የናንተው ነው፤ እኔ ከሌለሁኝ እናተም እንዲያው ነው፤ እርቧችሁ ጠግቤ፣ ብድንም ሞታችሁ፤ ማንም ስለሌለ ከኔ ‘ሚለያችሁ፤ እስከመጨረሻው አጅቡኝ ባካችሁ፡፡ ” እያለ እሳት ጥጃው ሕዝብን ይማጠናል፤ መስሎት የማናውቀው ቁርበት ዘርጉ ይላል፡፡ ክፋትና ተንኮል ተፈጥሮው የሆነ፤ ሕግና … [Read more...] about ላም እሳት ወለደች!
ግልፅ ደብዳቤ ለፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ
ለፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ ዋይት ሐውስ 1600 ፔንሲልቫንያ አቬኑ ሰሜን ምዕራብ ዋሽንግቶን ዲሲ 20500 የተከበሩ ፕሬዚደንት ኦባማ፤ ይህንን ደብዳቤ የምጽፍሎት በኢትዮጵያ ውስጥያለውን የሰብዓዊ መብቶች ሁኔታ ላሳውቆት ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ተጎዳን፣በደል ተፈጸመብን በማለት የሚያሰማውን አቤቱታ፣ ህጋዊ ጥያቄዎችንና ሠላማዊ ሰልፎችን ሁሉ መንግሥት ከማዳመጥ ይልቅ ጉልበትንና ኃይሉን ሁሉ እንደሚጠቀም ያውቃሉ ብዬ አምናለሁ። ይህ ሁኔታ ባግባቡ ካልተያዘ በሀገሪቷና በአካባቢው ሁሉ ያልተጠበቀና አስከፊ ሁኔታ ሊከሠት ይችላል።የኢትዮጵያና የዩናትድ እስቴት አሜሪካ ግንኙነት ከ1903 ጀምሮ እንደሆነ ይታወቃል። ስለዚህ የንግድና የወዳጅነት ውል ተፈራርመው ኢትዮጵያም ጥብቅ ወዳጅ ተብላ ትታወቅ ነበር። ኢትዮጵያ በአፍሪካ አብላጫውን የአሜሪካን ረድኤት እንድታገኝምሆኗል። በአጸፋው … [Read more...] about ግልፅ ደብዳቤ ለፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ
My two cents to break the deadlock between the Oromos and Unity Camps
Researches recognized that many change agendas fail not because of resistance to change. It is due to wrong responses to resistances. Many people tend to think that all resistances are one and the same. And hence, they use the same response to all resistances. To give you a quick background, experts in the field agree that there are three major levels of resistances to change. People resist at Level 1 since they don’t understand the change at all. Those who resist at Level 2, they capture the … [Read more...] about My two cents to break the deadlock between the Oromos and Unity Camps
መንፈሳዊ ወኔና ሥልጣን
ባለሥልጣኖቻችን ሚስቶቻቸውንና ልጆቻቸውን በጣም የናቋቸው ይመስላል፤ ሚስቶቻቸውና ልጆቻቸው የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያውቀውን ሁሉ ያውቃሉ፤ የኢትዮጵያን ቴሌቪዥን ያያሉ፤ የኢትዮጵያን ራድዮ ይሰማሉ፤ ባሎቻቸውና አባቶቻቸው የዛሬ ሳምንት የተናገሩትን ረስተው፣ ወይም ክደው፣ ወይም ዋሽተው ተቃራኒውን ሲናገሩ መሸማቀቃቸው አይቀርም፤ እንዲህ ያለው የንግግር መገለባበጥ የእምነት መገለባበጥን፣ የማሰብ ችግርን፣ የመንፈስ ልልነትን ያሳያል፤ ታዲያ ሚስቶችና ልጆች እየተሸማቀቁ አካላቸውም ነፍሳቸውም ሲያልቅ ለባለሥልጣኖቹ አይታወቃቸውም? ወይስ የቤተሰብ አባሎች ጠባይ እየሆነ ሽታዬ ሽታዬ እየተባባሉ ነው? አንዳንዶች ባለሥልጣኖች ወንበሩ ላይ የወጡት እግዚአብሔርን ሳይይዙ ነው፤ አንዳንዶቹ ደግሞ እግዚአብሔርን ይዘው ወንበሩ ላይ ይወጡና እግዚአብሔርን ከተቆናጠጡ በኋላ እግዚአብሔርን ከውስጣቸው የሚያስወጡት … [Read more...] about መንፈሳዊ ወኔና ሥልጣን