The Ethiopian ruling party, for the first time in its quarter of a century in power, declared a state of Emergency following over a year of protest that claimed thousands of lives and a huge damage of property. Every day people are dying or jailed in connection with the civil disobedience that is going on in different parts of the country. The government, initially, down played the protest as a local issue that can be dealt with local governments. As the protests got momentum, the government … [Read more...] about EPRDF: Once again on the wrong side of History
Archives for October 2016
የተባበረችውን ኢትዮጵያ በጋራ እንገነባለን
በቅርቡ በአንድ የኦሮሞ ወገኖች ስብሰባ ላይ አንድ ሰው ኦሮምያ ሰላም የምታገኘው ኢትዮጵያ ስትፈራርስ ነው ኢትዮጵያ መፍረስ አለባት አለ ተብሎ ሲራገብ እያየን ነው። እኔ በግሌ የዚህን ሰው ተልእኮ ለመረዳት ቅንጣት ጊዜ አልወሰደብኝም። ከራሱ ከወያኔ በቀጥታ መልእክት እየተቀበለ የሚሰራ የወያኔ ተቀጣሪ ነው ወይም እያጃጃሉ በስልት የሚጠቀሙበት ሰው ነው። አለቀ። ይህንን ለማለት ያስቻለኝ ነገር እንደሚታወቀው ይህ መንግስት ገና ሲመሰረት ጀምሮ በስልጣን ላይ ለመቆየት የሚያስችለው መሳሪያ ህዝባዊ ድጋፍ አይደለም። በዚህ ጎጠኛ የፓለቲካ አስተሳሰቡና በሙስና ድር በተፈጠረ ሥርዓት ምን ጊዜም ሰፊ ህዝባዊ ድጋፍ አገኛለሁ ብሎ አያስብም። ይህንን መንግስት በሚገባ ያውቃል። ይህን ስርዓት እድሜ ይቀጥልለታል ተብሎ የሚታሰበው ስልት ቅራኔ ነው። ለዚህም ነው መንግስት ከህገ መንግስቱም በላይ … [Read more...] about የተባበረችውን ኢትዮጵያ በጋራ እንገነባለን
ግልፅ ደብዳቤ ለአቶ ጀዋር መሐመድ
በኢትዮሚዲያ ላይ በለንደን ላይ ያደረጉትን ንግግር ከዚህ በታች የተቀነጨበውን አየውና ይህንን ልፅፍ ተነሳሳሁ። “የኦሮሞ ወጣቶችን ወክዬ ለውጭው ማህረሰብ የማስተላልፈው መልዕክት አለኝ። ካሁን በዋላ በኢትዮጵያ ቢሆን ቢሆን ታግለን መብታችንን አስመልሰን ከሌሎች ጋር አብረን እንኖራለን። ካልሆነ ግን ያችን ሀገር በታትነን ጥለናት እንሄዳለን እንጂ እንደ ትላንቱ የማይረቡት እላያችን ላይ ተጭነው እንዲያስተዳድሩን አንፈቅድም።” ጀዋር መሐመድ፥ ከለንደን ንግግር ከኢትዮሚዲያ የተወሰደ። በመጀመሪያ አሳቤን ይረዱልኝ። በክርክር ለማሸነፍ አሳቡም ምኞቱም የለኝም። እርስዎንም እንደ ጠላት ለመቁጠርና ለመፈረጅ በልቤ ውስጥ ያለው ፍቅር አይፈቅድልኝም። ነገሬ ከአስተሳሰብዎ ጋር ነው። ለማሳመን ብዙ ትንታኔ አልገባም። ቃሌን አጭር በማድረግ ከቃሌ ጀርባ ያለውን ቅን መንፈስ እንዲረዱ ተስፋ ማድረግን … [Read more...] about ግልፅ ደብዳቤ ለአቶ ጀዋር መሐመድ
ይረገም!!
በክፉ ያነሳ ወርቃማውን ስምሽን፣ በሃሜት ያጎደፈ ፀዐዳ ክብርሽን፣ በክፋት ፈረሱ ወዳንቺ የጋለበ፣ በእሾኸም ምላሱ ሊወጋሽ ያሰበ፤ ሰላምሽን የነሳ፣ ባንቺ ላይ ሊሳለቅ፣ ሊቀልድ የቃጣ መልካም ህይወት ትክዳው! ነፍሱ ሰላም ትጣ!! ብርሃንሽን ሊያጠፋ ውበትሽን ሊያከስም፣ መዐዛሽን ሊበክል ህይወትሽን ሊያጨልም፣ በክፋት ያቀደ በሻገተ ህሊናው፣ ብርሃኑ ይደፈን ! ጨለማ ይውረሰው! ስትለመልሚ ስትፈኪ አይቶ፣ በአርኪ ፈገግታሽ በቅናት ተውጦ፣ የቆሸሸ እጁን ባንቺ የዘረጋ፣ ሽባ ይሁን ይስለል! አንደበቱ ይዘጋ! የዘመናት ስምሽን ዝናሽን ሊያጎድፍ፣ ከባዕድ አብሮ ወዲያ ሲያነፈንፍ፣ ህይወቱን በሙሉ ሳይሰራ ቁም-ነገር፣ ገብቶ ሲሽሎኮሎክ ከጢሻ ከቆንጥር...፤ ሊነክስ ያደባ የጠባውን ጡትሽን፣ ሊያጠፋ የቃጣ ሃቀኛውን ልጅሽን፣ የታሪክ መጠሪያ ቅርሳ-ቅርስ … [Read more...] about ይረገም!!
ሕዝብ ላይ የሚፈጸም የፖለቲካ ውርጃ!!
አሁን የሚፈለገው የሚያሻገሩ መሪዎችን ማግኘት ብቻ ነው። ሕዝብ በፖለቲካ መሪዎች ሃፍረትን እየተግሞጠሞጠና ደሙ ደመ ከልብ እየሆነ የሚኖርበት ዘመን እንዲያከትምለት ይፈልጋል። የአንተ ደም የእኔ ደም ነው በማለት የችግሩ ጉያ ውስጥ ሆኖ አጋርነቱን፣ አንድነቱን ሲያሰማ ሩቅ ተቀምጦ እንደ ቅጥረኛ የወገንን ሞራል ማላመጥ አግባብ አይሆንም። ውሎ አድሮ ከገዳዮቹ በላይ ያስጠይቃል። በቅጥረኛነትም ያስመድባል። ከአገራችንም ሆነ ከዓለም ዘመን የማይረሳቸው የውብ ስብእና ባለቤቶች ሕዝባቸውን አሻግረዋል። ክፉዎች የቀበሩትን የቂምና የጥላቻ ገመድ በጣጥሰው አገራቸው በልዕልና፣ ሕዝባቸው በሰላም እንዲኖር አስችለዋል። በቀናነት ጀምረው፣ በቀናነት ጨርሰዋል። በታማኝነት ሃላፊነትን ተረከበው በታማኝነት አለፈዋል። ዝርዝር ውስጥ ባንገባም በህይወት ያሉም አሉ። እንዲህ ያሉትን የሚያስቡ “እኛንስ ማን … [Read more...] about ሕዝብ ላይ የሚፈጸም የፖለቲካ ውርጃ!!
Ato Emmanuel Abraham (1913-2016)
Ato Emmanuel Abraham who had served his country in a number of important diplomatic and ministerial posts for nearly four decades and half (1931-1974) has died at a great age of 103 on Wednesday. Emmanuel was ambassador to Britain and Italy and cabinet minister and director general at the Ministry of Foreign Affairs and director general of the Ministry of Education and Fine Arts, Minister of Posts, Telegraphs and Telephones; Minister of communications and Transport; and finally, minister of … [Read more...] about Ato Emmanuel Abraham (1913-2016)
ዓለምነህና ጸጋዬ አራርሳ
ዓለምነህ በአዋዜ ፐሮግራሙ ላይ ጸጋዬ አራርሳ ‹‹ኢትዮጵያዊ ማንነት የለም›› ያለውን ይዞ በለዘበ ቋንቋና በለዘበ ድምጽ ደቁሶታል፤ ብዙ ሰዎች የገባቸው አልመሰለኝም፤ በጉዳዩ የተማረውና የተመራመረው ዶር. ጸጋዬ አራርሶም የገባው አይመስለኝም፤ እስቲ እኔ የገባኝን ልንገራችሁ፡፡ በመጀመሪያ በሁለቱ ሰዎች መሀከል ያለውን የትምህርት ደረጃ ልዩነት ዓለምነህ ራሱ እንዳለው እሱ ‹‹በትምህርት እጅግም አልገፋም›› ጸጋዬ ግን የትምህርቱን ደረጃ ጣራው ላይ አድርሶታል ተብሎ በስሙ ላይ ‹‹ዶክተር›› የሚል የትምህርት ማዕርግ እንዲጨምር አድርጓል፡፡ በትምህርት እጅግም ያልገፋው ሰው በትምህርት ጣራ ላይ በደረሰው ሰው አስተያየት ላይ የሰጠው ትችት የትምህርት ደረጃ የሚባለውንም ሆነ የሁለቱን ሰዎች እውቀትና ብስለት የሚለካ ነው፤ የዓለምነህ ትችት ስለቱ ያረፈው ጸጋዬ የሚልዮኖችን እምነት መካዱ ላይ … [Read more...] about ዓለምነህና ጸጋዬ አራርሳ
ያዳቆነ ሰይጣን
ያዳቆነ ሰይጣን ሳያቀስ አይለቅም የሚል ነባር ተረት አለ። መልእክቱም ግልፅ ነው። በአንድ አጋጣሚ ክፉ አባዜ የተፀናወተው ሰው ያው ክፉ አባዜው ለከፋ አደጋ ሳይዳርገው አይቀርም ማለት ነው። የብሂሉ ትርጉም ገብቶኝ ካልሆነ የምታውቁ አርሙኝ። እኔ ግን በጥላቻ ታሪክ የታጨቀ ኮሮጆ አንጠልጥለው የሚዞሩና ህዝብን እርስ በርስ በማጋጨት ደዌ የተለከፉ አንዳንድ የዖሮሞ ተቃዋሚና የመብት ተከራካሪነን ባይ ግለሰቦችን ይገልፅልኝ እንደሆነ ብዬ የተጠቀምኩበት ምሳሌ ነው። ሰሞኑን ከሎንዶን አካባቢ አንድ ጉድ ሰምቼ ጆሮዬን እስከማምነው ድረስ የፈጀብኝ ጊዜ ቀላል አልነበረም። በእውነቱ በቀላሉ የሚታመን ወሬ አልነበረም። ለነገሩ አሁን አለም ያወቀው ፀሃይ የሞቀው እውነት ሆኖ ሀቀኛ ኢትዮጵያውያን ዖሮሞዎችን ብቻ ሳይሆን መላ ህዝብ ጭምር አንገት ያስደፋ እውነት ስለሆነ ወሬ ልለው አልችልም። አዎ … [Read more...] about ያዳቆነ ሰይጣን
The summer of our upheaval
This is the summer the Ethiopian people declared ‘I’ve had it up to here’ and rebelled against Woyane rule. A few things ignited the rage that has now engulfed the whole country. The Addis Ababa Master plan designed to confiscate land though being in the planning stage for a while did not go do well with the poor farmers. It was Abbay Tsehaye’s turn to prove his worth and he failed miserably. TPLF embarked on its killing orgy to quiet the noise. Over a thousand lives, tens of thousands youth in … [Read more...] about The summer of our upheaval
ኢሰመጉ ከየት ወዴት?
አምስት ዓረፍተ ነገሮች፤ ኢሰመጉ መንፈሳዊ ተልእኮ ያለው መንፈሳዊ ድርጅት ነው፤ ዓላማው በሰው ልጆች መሀከል የሚከተሉትን ተልእኮዎች መዝራት ነው፡-- 1.1. እኩልነትንና ነጻነትን 1.2. ፍቅርንና ስምምነትን 1.3. ፍትሕንና ሕጋዊነትን 1.4. ሰላምንና ማኅበረሰባዊ እድገትን 1.5. የእውነትንና የእውቀትን ብርሃን ማስፋፋትን ኢሰመጉ የተቋቋመው በሁለት ምክንያቶች ነው፤-- 2.1. የደርግ አገዛዝ ወድቆ አዲስ መንግሥት በአዲስ ሥርዓት ይመሠረታል በሚል ተስፋ አዲሱ ሥርዓት የኢትዮጵያን ሕዝብ ወደ ትክክለኛ አቅጣጫ እንዲመራ ለመርዳት ነበር፤ 2.2. የኢትዮጵያን ሕዝብ በመብት ጉዳይ ለማንቃትና ራሱን ከተገዢነት ወደገዢነት ደረጃ እንዲለውጥ ለማስቻል ነበር፡፡ ለትውልድ የሚተላለፍና ስምን ሲያስጠራ የሚኖር ሥራ ለመሥራት ሀብት ጥሩ መሣሪያ ነው፤ በሌሎች አገሮች እንደሚደረገው … [Read more...] about ኢሰመጉ ከየት ወዴት?