• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢሰመጉ ከየት ወዴት?

October 27, 2016 06:31 am by Editor 2 Comments

አምስት ዓረፍተ ነገሮች፤

ኢሰመጉ መንፈሳዊ ተልእኮ ያለው መንፈሳዊ ድርጅት ነው፤ ዓላማው በሰው ልጆች መሀከል የሚከተሉትን ተልእኮዎች መዝራት ነው፡–

1.1. እኩልነትንና ነጻነትን
1.2. ፍቅርንና ስምምነትን
1.3. ፍትሕንና ሕጋዊነትን
1.4. ሰላምንና ማኅበረሰባዊ እድገትን
1.5. የእውነትንና የእውቀትን ብርሃን ማስፋፋትን

ኢሰመጉ የተቋቋመው በሁለት ምክንያቶች ነው፤–

2.1. የደርግ አገዛዝ ወድቆ አዲስ መንግሥት በአዲስ ሥርዓት ይመሠረታል በሚል ተስፋ አዲሱ ሥርዓት የኢትዮጵያን ሕዝብ ወደ ትክክለኛ አቅጣጫ እንዲመራ ለመርዳት ነበር፤
2.2. የኢትዮጵያን ሕዝብ በመብት ጉዳይ ለማንቃትና ራሱን ከተገዢነት ወደገዢነት ደረጃ እንዲለውጥ ለማስቻል ነበር፡፡

ለትውልድ የሚተላለፍና ስምን ሲያስጠራ የሚኖር ሥራ ለመሥራት ሀብት ጥሩ መሣሪያ ነው፤ በሌሎች አገሮች እንደሚደረገው ሰዎች ለኢሰመጉ ሀብት ማውረስን ቢለምዱ የኢሰመጉ ዓላማዎችን ለማስፋፋትና ማኅበረሰባችንን ወደተሻለ አቅጣጫ ለመግፋት የተሻለ ኃይል ይኖር ነበር፤ ከውጭ ሰዎችም ጥገኛነት ለመውጣትና ራሳችንን ወደሰውነት ደረጃ ለመግፋት ያስችለን ነበር፡፡

እንዲያም ሆኖ በአለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ውስጥ ጠንካራ በጎ መንፈስን ብቻ በታጠቁ ጥቂት ሰዎች፣ በትንሽ ገንዘብ አዲስ የትውልድን አቅጣጫ የሚያመለክት ሥራ የሠራ ከኢሰመጉ ጋር የሚወዳደር ድርጅት የለም፤–

3.1. ከውጭም ከውስጥም የተሰነዘረበትን ዛቻና ግፊት ተቋቁሞ ቀጥ ብሎ ዓላማውን ሳይስት የቆየ
3.2. ቢከሳም ሕይወቱን ያላጣ ድርጅት ነው፤
3.3. የኢሰመጉ መክሳት የማኅበረሰቡን መክሳት የሚያመለክት ነው፤
3.4. በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ማኅበረሰቡ ኢሰመጉን በሚገባ ባለመደገፉና እንዲከሳ በማድረጉ ራሱንም አከሳ፤ ራሱን ጎዳ፤ እስከዛሬ አንድም ባለሀብት ለኢሰመጉ ቋሚ ሀብት ያወረሰ አለመኖሩ አስተሳሰባችን ከግለሰብ ወደማኅበረሰብና ወደትውልድ አለመሸጋገሩን ያመለክታል፤
3.5. እስከዛሬም ድረስ ቢሆን ማኅበረሰቡ የኢሰመጉን መንፈሳዊ ተልእኮ በትክክል ተገንዝቦ ኢሰመጉን በመርዳት ራሱን ለመርዳት የሚያስችለው ደረጃ ላይ ገና አልደረሰም፡፡

በዚህ በዓል ላይ እኔ ያረቀቅሁትን የኢሰመጉን ደንብና ቃል ኪዳን ሁለት የሕግ ባለሙያዎች፣ ወርቁ ተፈራና ዓሥራት ገብሬ ብዙ ጊዜ አጥፍተውበት በማሻሻላቸውና የባለሙያ ሥራ በማድረጋቸው፣ በተጨማሪም የመጀመሪያው የኢሰመጉ ቢሮ በዓሥራት ገብሬ ቢሮ ውስጥ ሆኖ የሱ ጸሐፊም የኢሰመጉን ሥራ እንድትሠራ በማድረግ ያበረከተው እርዳታ ኢሰመጉ በራሱ እግር እስቲቆም ድረስ ደግፎታል፡፡

መደምደሚያ

የኔ ትውልድ አንድ በአንድ እያለ በመመናመን ላይ ነው፤ የእኔም ተራ እየደረሰ ነው፤ ለኢሰመጉ የማወርሰው መሬትና ቤት የለኝም፤ መጻሕፍት ሞልተውኛል፤ የአዋሳ ሕዝብ አሁን ኢሰመጉ ያለውን የመጻሕፍት ቤት ለሕዝብ የሚጠቅም ሊሆን በሚችልበት ደረጃ ለማድረስ የሚያስችል ቤት ቢያገኝለት አብዛኛዎቹን ለአዋሳ ለማውረስ ወስኛለሁ፤ ቤትና አስተናባሪ ከአልተገኘለት ውርሱን ለማስፈጸም አስቸጋሪ ይሆናል፤ በአዲስ አበባ ብዙ አማራጭ የመጻሕፍት ቤቶች ስላሉ የአዋሳን ኢሰመጉ መጻሕፍት ቤት ማጠናከሩ የተሻለ ይመስለኛል፤ በተጨማሪም ከኢሰመጉ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች ውስጥ አዋሳ በጣም ልቆ የቆየ በመሆኑ ለማበረታታት ነው፤ ከአዋሳ ነዋሪዎች መሀከል አንድ ቤተ መጻሕፍቱን በስሙ ለማስጠራት የሚፈልግ ሰው ለኢሰመጉ አንድ ቤት የሚሰጥ ወይም የሚያወርስ እንዲገኝ ጥረት ሊደረግ ይገባል፡፡

በመጨረሻም ለዛሬ በዓል፤

በስደት ላሉት ለአበበ ወርቄና ለዓሥራት ገብሬ
በሕመም ምክንያት በመሀከላችን ላልተገኙት አንዳርጋቸው ተስፋዬና ለጌታቸው ተሰማ
በሕይወት ለሌለው አብሮ-አደጌ ወርቁ ተፈራ፣ ነፍሱን ይማረው፤
ለቸርነቱ ወደር ለሌለው ጓደኛዬ አባተ የኔው — ኢሰመጉ ከስዊስ አምባሳደር ጋር ውዝግብ በተነሣበት ጊዜ መኪናዬንም ቢሆን ሸጬ አሥር ሺህ ዶላርህን እመልስልሃለሁ ያልሁትን በጋዜጣ እንብቦ፣ እቤቴ ድረስ መጥቶ የአሥር ሺህ ዶላር ቼክ ጽፎ ‹‹መኪናህን እንዳትሸጥ፤ ያውልህ አፍንጫው ላይ ወርውርለት!›› ያለኝ ኩሩ ኢትዮጵያዊ ሰው ነው፤ ነፍሱን ይማረው፡፡

በነዚህ በስድስት ሰዎች ስም የአምስት ወር ጡረታዬን አውጥቼ የአምስት መቶውን ብር ቲኬት በስማቸው በመግዛት ላስታውሳቸው እፈልጋለሁ፡፡

ላስታውሳቸው እፈልጋለሁ፡፡

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
ጥቅምት 2009

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    October 27, 2016 02:13 pm at 2:13 pm

    ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም አንጡራ የሃገራችን ሃብት ናቸው። ለዚህም በዘመናት መካከል ያላቸው አይበገሬ እይታና የግልና የቤተሰብ የህይወት ስኬታቸው ምስክር ነው። ሰው ሁሉ በየወገንህ ሲባል አይመቸኝም እኔ ኢትዮጵያዊ እንጂ ሌላ ልሆን አልችልም በማለት የቀኑ አለቆቻችንን የተንሻፈፈ የፓለቲካ ስልፍ አጥፊነት ገና ከጅምሩ በይፋ የተጋፈጡና በመታገል ላይ ያሉ የእድሜ ባለጸጋ ናቸው።
    አልፎ አልፎ እርሳቸውን የሚያጥላላ መጣጥፍ በዚህም በዛም በየስርቻው የተሰገሰጉ የወያኔ ፍርፋሪ ለቃሚዎች የሚለጣጥፉትንም እናውቃለን። ህዝባችን ግን ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም ማን እንደሆነ ጠንቅቆ ያውቃል። በአንድ ወቅት ፕ/ሩ ከወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ጋር ቆመዋል። በድንገት ጠበንጃ ያነገቱ የወያኔ ተቀላቢዎች በስፍራው ግር ግር ይፈጥሩና ወይዘሪቱን ወደ ማረፊያ ቤት (ለእሥር) ለመውሰድ ዙሪያውን እንደ ጅብ ከበዋታል። ፕ/ሩም ተው እኛ ወደእናነተ ጋ እናመጣታለን አታዋክቧት በማለት ይናገራሉ። የወንድምና የእህቱ ሬሳ ወድቆ ካላየ የበላየነት የማይሰማውና በብሄር ጥላቻ ውስጡ የተመረዘው ታጣቂ ፕ/ሩን በሰደፍ መታቸው። ዛሬም ወያኔ ያስፈራራቸዋል። ይምከሩን ከማለት ይልቅ እንዳይጽፉ፤ እንዳይናገሩ አፈና ያረግባቸዋል። ሌላ ሰለ ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያምና መሰሎቹ ብዙ ማለት ይቻላል። ግን ሥፍራና ጊዜ የለም። በተቻለን ሁሉ የህዝባችንንን ሰቆቃ ለማስታገስ ዘርና ወገን ሳንለይ የወያኔን ከፋፋይና እኛ ብቻ እንብላ ባይነት እንታገለው።

    Reply
  2. ሙናች says

    October 31, 2016 05:03 pm at 5:03 pm

    ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም!
    በተግባር የተገለጸ ለሃገር/ለሕዝብ ያለዎት ከልብ የመነጨ እውነተኛ ፍቅር እጅግ የሚገርመኝና በሕይወት ዘመኔ ሁሉ የማረሳው ሃብት ነው፤ ለዚህ አባባሌ ማስረጃ የሚሻ አእምሮ ላላችሁና ፕ/ርን እንደ እኔ ቀርባችሁ ሳታውቋቸው በጭፍን ጥላቻ ለምትጠሏቸውና አንዳንዶችም በዚህ ጉዳይ ላይ በግል ከእኔ ጋር ለተጋጫሁ ወገኖቼ ለማንነታቸው መረጃ እንካችሁ፡
    1/ እኔ እንኳ ባልነበረኝ አቅም መኖሪያ ቤት ተንደፋድፌ ሥሠራ አቅሙ እያላቸው ለሕዝቡ ሕይወት ቅድሚያ መስጠታቸው በቀበሌ ቤት መወሰናቸው
    2/ ብዙዎቻችን ከሃገር ለመውጣት ነፍስ ውጪ ግቢ ጥረት ስናደርግ በረካታ የውጭ ሃገር ዩኒቨርስቲዎች በሌክቸረርነት ሲለምኗቸው ሃገሬን ለማን ትቼ?
    3/ ከማንም ሰው ወይም ድርጅት ወይም መንግሥት ጋር የሚጋጩት ለሃገር/ለሕዝብ መሻሻልና ጥቅም ባለ አመለካከትና ተግባር ላይ እንጂ በግል ማንነትና ምንነት ላይ አለመሆኑ ከማንም ሰው ለየት ያደርጋቸዋል (ለምሳሌ የሕዋት አባላትንና ድርጊታቸውን ለየተው የመፈረጅ እይታ)
    4/ ቂመኞችና በቀለኛች በሁለቱም ሃገሮች (ኢትዮጵያና ኤርትራ)ውስጥ በተደረገው የማስወጣት ሥራ ላይ የፈጸሙትን ግፍና በደል አጥብቀው መቃወማቸውና ወቅታዊ መግለጫ በማውጣት መጋፈጣቸው
    5/ መንግሥትም ሆነ አንዳንድ ውሃ አላማጮች ኢሰመጉ የፕ/ር መስፍን የግል ሃብት ወይም የፖለቲካ ድርጅት ነው ለሚሉ የሃሰት አባቶች አፍ ማስያዣ ይሆን ዘንድ ኢሰመጉን የኢትዮጵያ ሕዝብ ሃብት ለማድረግ ከድርጅቱ አመራር እራሳቸውን ያገለሉበት ጊዜ እንደነበረ ምስክር ነኝ
    6/ በአጠቃላይ ፕ/ር መስፍን እንደ ሰው ለራሳቸው ያልኖሩ ሃብት ለማካበትና ስልጣን ለመያዝ ያልደከሙ ነገር ግን ከጃንሆይ ጀምረው ለራሳቸው እንጂ ለሕዝብ ያልቆሙትን 3ቱንም መንግሥታት ለሚወዱት ምስኪን ወገናቸው ፍትህና እድገት ሲሉ ብቻ በድፍረት የተጋፈጡ፣ የተንገላቱ የታሰሩና የታመሙ የምድሪቱ በረከት መሆናቸውን ለ4 ዓመታት አብሬያቸው በመሆን በቅርብ የማውቃቸው ካለመጽሐፍ ቅዱስ የክርስቶስ ኢየሱስን ወንጌል በተግባር የሰበኩ እውነተኛ ሰው በመሆናቸው ሁላችንም አርያነታቸውን ብንከተልና ለሃገር ጥቅም ብናውለው መልካም ይሆናል!!!

    ለፕ/ር መስፍን ግን የሚያነቡኝ ከሆነ:

    ካመሰገኗቸው ሰዎች መካከል እነዚያ በነፍሳቸው ጨክነው ከጎንዎ በመሆን መረጃዎችን ከማይደፈሩ ከሚመስሉ ቦታዎች/ምሳሌ ከእስር ቤት/ ፈልፍለው በማውጣት መግለጫዎች እንዲወጡ ያደርጉ የነበሩና አሁን በውጭ አገር ተበትነው አሁንም እርስዎ ያስተማሯቸው ለወገን የመጮህ ሥራቸውን ያላቋረጡትን ወጣቶች ባለማካተትዎ ቅር ብሎኛል!!! ሽምግልናው ተጭኖዎት ከሆነ ምንም አይደለም KKKKKKKKKKK = የራስዎ ሳቅ!

    ሰላምና ጤና ይስጥዎ
    እጅግ ወዳጅዎ
    ሙናች ነኝ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule