• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“… የጦር ኃይል … እና የብእር ኃይል …” ሃዲስ አለማየሁ

October 19, 2016 10:13 am by Editor 3 Comments

” … ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ አሁን እስካለንበት ድረስ ታሪኩን መለስ ብለን ብንመለከት በሰው ዘር ላይ ግዛታቸውን ለመዘርጋት፣ ሰውን ባካልም ሆነ በመንፈስ ለመግዛት፣ ሁለት ተቃራኒ ኃይሎች ሲታገሉ እናያለን፡፡ ከነዚህ አንዱ የሀይለኞች፣ ያጥቂዎች፣ የጦር ኃይል፣ ሁለተኛው የደራሲያን የብእር ኃይል ናቸው፡፡

“የጦር ኃይል በየጊዜው፣ በየቦታው የሚነሱ ኃይለኞች ሰራዊት አደራጅተው፣ የጦር መሳሪያ አከማችተው፣ ሰውን እየጨቆኑ ለግል ድሎታቸውና ፍላጎታቸው አገልጋይ የሚያደርጉበት እውር ሀይል ነው፡፡ የብእር  ኃይል በየጊዜው በየቦታው የሚነሱ ታላላቅ ደራሲያን ከስው ተለይተው፣ ከብእርና ከወረቀታቸው ጋር በየቤታቸው ተዘግተው፣ ምስጢረ ፍጥረትን እየመረመሩ፣ አዳዲስ ነገር እየፈጠሩ፣ ሰውን ከድንቁርና ሰንሰለት ተፈትቶ፣ ከእንሰሳ ባህርያት ጠርቶ፣ የመንፈስና የአካል ነጻነት አግኝቶ፣ ስርአት ያለው ህብረተሰብ መስርቶ፣ ፈጣሪ ከፍጥረት ሁሉ አልቆ ሲፈጥረው ለመደበለት ከፍተኛ ማእረግ ብቁ እንዲሆን የሚያደርገው ብሩህ ኃይል ነው፡፡

“እነዚህ ሁለት ተቃራኒ ኃይሎች በሚያደርጉት ትግል ምንም እንኩዋ ለጊዜው ጨቁዋኙ የጦር ኃይል ድል አድራጊ ቢመስል በመጨረሻ የእውነተኛው ድል አድራጊ የብእር ኃይል መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ የጦር ኃይል አስገዳጅ፣ የብእር ኃይል አስረጂ እንደመሆናቸው መጠን በማስገደድ የተመሰረተ እድሜው ማጠሩ፣ በማስረዳትና በማስወደድ የተመሰረተ ለሁልጊዜ መኖሩ የማያጠራጥር ነው፡፡ ለዚህም ኃይለኞች በጦር ኃይል የመሰረቱት ግዛት አንድ ባንድ እየፈረሰ፣ ያወጁት ትእዛዝ እየተደረመሰ፣ ዛሬ ዓለም የተቀበለው  ደራሲያን በየጊዜው ያወጁት የሃይማኖት፣ ያስተዳደርና የፍርድ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ኑሮ ስራት መሆኑን ታሪክ ይመሰክራል”፡፡ (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature, Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Ayu says

    October 20, 2016 04:17 am at 4:17 am

    Dear Editor of Golgul,
    Can you please translate this article – I link to my face book and a lots of social media -FB – users asked me.

    Kind regads

    Reply
  2. ጌታቸው፡ወልደሥላሴ says

    October 20, 2016 06:23 pm at 6:23 pm

    እንደ፡ፈረንጆቹ፡አነጋገር፡(That was in the good old days)
    አሁን፡ግን፡በብዛት፡ወጣቱም፡እናት፡አባቱም፡(Brain washed)ሆኖ፡
    እመቤታችንን፡አማላጃችንን፡ቅድስትን፡ክዶ፡በመንፈስ፡እየሞተ፡ለሥጋው፡
    እያደረ፡ነው። ያዲያቆነውም፡ሰይጣን፡ሳያቄስ፡አይቀርም፡እንደሚባለው፡
    ይሄው፡ሴይጣኑ፡ከነገሰ፡ብዙ፡ዘመናት፡አልፎአል።
    እንደድሮው፡ባሕላችን፡የባሰ፡አታምጣ፡ነው። ከዚህ፡የባሰ፡
    ምን፡እንዳለ፡እኔ፡አላውቅም።(GOD have mercy)

    Reply
  3. Tesfa says

    October 21, 2016 04:34 pm at 4:34 pm

    እውቁ ጸሃፊ አቤ ጎበኛ “ፓለቲከና ፓለቲከኞች” በተባለው ድራማዊ መጽሃፉ ላይ እንዲህ ይለናል። “ድንጋይን ማን ያናግረዋል ቢሉ ውሃ” ሆኖ አናጋሪዎች እንድናገር ስለገፉኝ የዚህን መጽሃፍ መግቢያ እንዳስፋፋው ምክንያት ሆኑኝ ይለናል። ከሽያጭና ከቅርጫ በተረፈችው በዛሬይቱ ኢትዮጵያ መኖር በዘርና በጎሳ በመሆኑ የጥቅልና የአንድነት ሃሳብ ማንሳት ነፍጠኛ ሲከፋም በጸረ ሽብሩ ህግ መሰረት ዘብጥያ ያስወርዳል። እኔንም እንዲጽፍ የሚገፉኝ አጥፊዎቹ ወያኔና ሻቢያ በህዝባችን ላይ የሚፈጽሙት ግፍ ነው። ከእነርሱ የደም ኮሮጆ እኔ ዳቦ አልሻም። ግን ዓለም እየተቀየረ ሲሄድ ዛሬም የሚያስቡበትና የሚተነፍሱበት ሳንባቸው ጫካን ተግን ያረገ መሆኑ እጅግ ያሳዝናል። ሻብያ ወንድሙን አባሮ የባህር በርን ለዓረብ!
    የቀዳማዊ ሐይለሥላሴ መንግሥት በወታደር ጭፍራ ከተተካ ጊዜ ጀምሮ ምድሪቱ የማያቋርጥ የመከራ ዶፍ ውስጥ እንዳለች የቆመ ይረዳዋል። ደርግ በሻብያ/ወያኔና በምዕራባዊያን ሴራ ከተፍረከረከ በህዋላ ሻብያ በኤርትራ ወያኔ በአዲስ አበባ አለቆች ሆነው እንሆ 25 አመታት ዘለሉ። በእነዚህ አመታት ውስጥ ይህ ነው የማይባለ ሰቆቃና ግፍ በሁለቱም መዲናዎች ተፈጽሞ አል በመፈጸምም ላይ ነው። እያደር ነገር ይሻላል በማለት ተስፋ ያረገው ህዝባችን እየቆየ ነገር እየከፋና ሃገሪቱ ጥቂቶች የትግራይ ተወላጆች መፈንጪያ መሆኑዋን ሲገነዘቡ በቃ በማለታቸው ዛሬ ላለንበት አሳር ተዳርገናል። የወያኔ ኢትዮጵያ ለወያኔ ብቻ። ሌላው ሁለተኛ ዜጋ ነው። ስትፈልግ ከተረፈው ፍርፋሪ እንካ ካልሆነ ደግሞ እሥራት፤ግርፋት፤ ሰቆቃና ሞት ድርሻህ እንዲሆን እናረጋለን እያሉ ያስፈራሩታል። የወያኔው ቆንጮ አቶ መለስ ዜናዊ ሞት ከጠራቸው ወዲህ 120 በላይ መኮንኖች የማእረግ እድገት ተለግሶአቸዋል። የሚገርመው ግን 99.9% ወያኔዎች መሆናቸው ነው።
    ሃዲስ ዓለማየሁ የኖሩበት ዘመን የጸጋ፤ የሰላም፤ ሰዎች ወደ ውጭ ለትምህርት ሲላኩ ትምህርታቸውን ጨርሰው መቼ ለሃገራቸውና ለህዝባችው ተመልሰው አገልግሎት ለመስጠት የሚናፍቁበት ወቅት ነበር። ዘርና ጎሳ ሥፍራ የሌውም። የወያኔ ብህል ሁሉም በየክልልህ በማለትና የይስሙላ የቋንቋና ውል የሌለው ክልል በማበጀት እኛ በዛ ዙሪያ ስንናከስ እነርሱ የሃገሪቱን ሃብት የሚያጋብሱበት የሳቅና የጮቤ እረገጣ ጊዜአቸው ነው። በቋንቋ እንኳን በመነጋገር እንዳንግባባ ውል አልባ የሆነ ብሄራዊነት የለለው በየጎሳው የተተለመ ባህር የማያሻገር ቋንቋን የግላቹሁ ነው ተገልገሉበት አማርኛ የጨቋኝ ቋንቋ ነው ፊደሉንም አትጠቀሙበት በማለት ገደል ከተውናል። በኢትዮጵያ ውስጥ ሰው ብቻ አይደለም የሚሰቃየው። የድርና ለማዳ እንስሳትና የምድሪቱ የተፈጥሮ ደኖች ጭምር ናቸው። ወያኔና ሻብያ በምርጫ፤ በድርድር ሥልጣን ህዝብ ለመረጠው ያስረክባሉ ብሎ ማመን ራስን ማታለል ይሆናል። የተካኑት በእሳት ነው። ስልጣናቸውንም የሚሽረው እሳት ነው። የአለም ታሪካዊው እይታም ይህን ይደግፋል። ጋዳፊ፤ ሳዳም፤ ሙባረክ ሌሎችንም በህዝብ የተቀጣጠለ እሳት ነው የለበለባቸው። የወያኔና የሻቢያ እድል ፈንታም ከዚህ ቢከፋ እንጂ አይሻልም። ይብቃኝ፡፡ በዚች ግጥም ልዝጋ።

    ነበረ ይለኛል አገኘው ይመስል
    ቤት እየቆጠረ እሳት እየጫረ
    ነገርን በነገር እየተረጎመ
    ለህዝብ ቁሜአለሁ
    ለሃገር እያለ
    ትላንትን አጥላልቶ
    ዛሬን አሞካሸ
    ለራሱ አመቻችቶ
    ሌላን አባረረ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule