• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“… የጦር ኃይል … እና የብእር ኃይል …” ሃዲስ አለማየሁ

October 19, 2016 10:13 am by Editor 3 Comments

” … ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ አሁን እስካለንበት ድረስ ታሪኩን መለስ ብለን ብንመለከት በሰው ዘር ላይ ግዛታቸውን ለመዘርጋት፣ ሰውን ባካልም ሆነ በመንፈስ ለመግዛት፣ ሁለት ተቃራኒ ኃይሎች ሲታገሉ እናያለን፡፡ ከነዚህ አንዱ የሀይለኞች፣ ያጥቂዎች፣ የጦር ኃይል፣ ሁለተኛው የደራሲያን የብእር ኃይል ናቸው፡፡

“የጦር ኃይል በየጊዜው፣ በየቦታው የሚነሱ ኃይለኞች ሰራዊት አደራጅተው፣ የጦር መሳሪያ አከማችተው፣ ሰውን እየጨቆኑ ለግል ድሎታቸውና ፍላጎታቸው አገልጋይ የሚያደርጉበት እውር ሀይል ነው፡፡ የብእር  ኃይል በየጊዜው በየቦታው የሚነሱ ታላላቅ ደራሲያን ከስው ተለይተው፣ ከብእርና ከወረቀታቸው ጋር በየቤታቸው ተዘግተው፣ ምስጢረ ፍጥረትን እየመረመሩ፣ አዳዲስ ነገር እየፈጠሩ፣ ሰውን ከድንቁርና ሰንሰለት ተፈትቶ፣ ከእንሰሳ ባህርያት ጠርቶ፣ የመንፈስና የአካል ነጻነት አግኝቶ፣ ስርአት ያለው ህብረተሰብ መስርቶ፣ ፈጣሪ ከፍጥረት ሁሉ አልቆ ሲፈጥረው ለመደበለት ከፍተኛ ማእረግ ብቁ እንዲሆን የሚያደርገው ብሩህ ኃይል ነው፡፡

“እነዚህ ሁለት ተቃራኒ ኃይሎች በሚያደርጉት ትግል ምንም እንኩዋ ለጊዜው ጨቁዋኙ የጦር ኃይል ድል አድራጊ ቢመስል በመጨረሻ የእውነተኛው ድል አድራጊ የብእር ኃይል መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ የጦር ኃይል አስገዳጅ፣ የብእር ኃይል አስረጂ እንደመሆናቸው መጠን በማስገደድ የተመሰረተ እድሜው ማጠሩ፣ በማስረዳትና በማስወደድ የተመሰረተ ለሁልጊዜ መኖሩ የማያጠራጥር ነው፡፡ ለዚህም ኃይለኞች በጦር ኃይል የመሰረቱት ግዛት አንድ ባንድ እየፈረሰ፣ ያወጁት ትእዛዝ እየተደረመሰ፣ ዛሬ ዓለም የተቀበለው  ደራሲያን በየጊዜው ያወጁት የሃይማኖት፣ ያስተዳደርና የፍርድ፣ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ኑሮ ስራት መሆኑን ታሪክ ይመሰክራል”፡፡ (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature, Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Ayu says

    October 20, 2016 04:17 am at 4:17 am

    Dear Editor of Golgul,
    Can you please translate this article – I link to my face book and a lots of social media -FB – users asked me.

    Kind regads

    Reply
  2. ጌታቸው፡ወልደሥላሴ says

    October 20, 2016 06:23 pm at 6:23 pm

    እንደ፡ፈረንጆቹ፡አነጋገር፡(That was in the good old days)
    አሁን፡ግን፡በብዛት፡ወጣቱም፡እናት፡አባቱም፡(Brain washed)ሆኖ፡
    እመቤታችንን፡አማላጃችንን፡ቅድስትን፡ክዶ፡በመንፈስ፡እየሞተ፡ለሥጋው፡
    እያደረ፡ነው። ያዲያቆነውም፡ሰይጣን፡ሳያቄስ፡አይቀርም፡እንደሚባለው፡
    ይሄው፡ሴይጣኑ፡ከነገሰ፡ብዙ፡ዘመናት፡አልፎአል።
    እንደድሮው፡ባሕላችን፡የባሰ፡አታምጣ፡ነው። ከዚህ፡የባሰ፡
    ምን፡እንዳለ፡እኔ፡አላውቅም።(GOD have mercy)

    Reply
  3. Tesfa says

    October 21, 2016 04:34 pm at 4:34 pm

    እውቁ ጸሃፊ አቤ ጎበኛ “ፓለቲከና ፓለቲከኞች” በተባለው ድራማዊ መጽሃፉ ላይ እንዲህ ይለናል። “ድንጋይን ማን ያናግረዋል ቢሉ ውሃ” ሆኖ አናጋሪዎች እንድናገር ስለገፉኝ የዚህን መጽሃፍ መግቢያ እንዳስፋፋው ምክንያት ሆኑኝ ይለናል። ከሽያጭና ከቅርጫ በተረፈችው በዛሬይቱ ኢትዮጵያ መኖር በዘርና በጎሳ በመሆኑ የጥቅልና የአንድነት ሃሳብ ማንሳት ነፍጠኛ ሲከፋም በጸረ ሽብሩ ህግ መሰረት ዘብጥያ ያስወርዳል። እኔንም እንዲጽፍ የሚገፉኝ አጥፊዎቹ ወያኔና ሻቢያ በህዝባችን ላይ የሚፈጽሙት ግፍ ነው። ከእነርሱ የደም ኮሮጆ እኔ ዳቦ አልሻም። ግን ዓለም እየተቀየረ ሲሄድ ዛሬም የሚያስቡበትና የሚተነፍሱበት ሳንባቸው ጫካን ተግን ያረገ መሆኑ እጅግ ያሳዝናል። ሻብያ ወንድሙን አባሮ የባህር በርን ለዓረብ!
    የቀዳማዊ ሐይለሥላሴ መንግሥት በወታደር ጭፍራ ከተተካ ጊዜ ጀምሮ ምድሪቱ የማያቋርጥ የመከራ ዶፍ ውስጥ እንዳለች የቆመ ይረዳዋል። ደርግ በሻብያ/ወያኔና በምዕራባዊያን ሴራ ከተፍረከረከ በህዋላ ሻብያ በኤርትራ ወያኔ በአዲስ አበባ አለቆች ሆነው እንሆ 25 አመታት ዘለሉ። በእነዚህ አመታት ውስጥ ይህ ነው የማይባለ ሰቆቃና ግፍ በሁለቱም መዲናዎች ተፈጽሞ አል በመፈጸምም ላይ ነው። እያደር ነገር ይሻላል በማለት ተስፋ ያረገው ህዝባችን እየቆየ ነገር እየከፋና ሃገሪቱ ጥቂቶች የትግራይ ተወላጆች መፈንጪያ መሆኑዋን ሲገነዘቡ በቃ በማለታቸው ዛሬ ላለንበት አሳር ተዳርገናል። የወያኔ ኢትዮጵያ ለወያኔ ብቻ። ሌላው ሁለተኛ ዜጋ ነው። ስትፈልግ ከተረፈው ፍርፋሪ እንካ ካልሆነ ደግሞ እሥራት፤ግርፋት፤ ሰቆቃና ሞት ድርሻህ እንዲሆን እናረጋለን እያሉ ያስፈራሩታል። የወያኔው ቆንጮ አቶ መለስ ዜናዊ ሞት ከጠራቸው ወዲህ 120 በላይ መኮንኖች የማእረግ እድገት ተለግሶአቸዋል። የሚገርመው ግን 99.9% ወያኔዎች መሆናቸው ነው።
    ሃዲስ ዓለማየሁ የኖሩበት ዘመን የጸጋ፤ የሰላም፤ ሰዎች ወደ ውጭ ለትምህርት ሲላኩ ትምህርታቸውን ጨርሰው መቼ ለሃገራቸውና ለህዝባችው ተመልሰው አገልግሎት ለመስጠት የሚናፍቁበት ወቅት ነበር። ዘርና ጎሳ ሥፍራ የሌውም። የወያኔ ብህል ሁሉም በየክልልህ በማለትና የይስሙላ የቋንቋና ውል የሌለው ክልል በማበጀት እኛ በዛ ዙሪያ ስንናከስ እነርሱ የሃገሪቱን ሃብት የሚያጋብሱበት የሳቅና የጮቤ እረገጣ ጊዜአቸው ነው። በቋንቋ እንኳን በመነጋገር እንዳንግባባ ውል አልባ የሆነ ብሄራዊነት የለለው በየጎሳው የተተለመ ባህር የማያሻገር ቋንቋን የግላቹሁ ነው ተገልገሉበት አማርኛ የጨቋኝ ቋንቋ ነው ፊደሉንም አትጠቀሙበት በማለት ገደል ከተውናል። በኢትዮጵያ ውስጥ ሰው ብቻ አይደለም የሚሰቃየው። የድርና ለማዳ እንስሳትና የምድሪቱ የተፈጥሮ ደኖች ጭምር ናቸው። ወያኔና ሻብያ በምርጫ፤ በድርድር ሥልጣን ህዝብ ለመረጠው ያስረክባሉ ብሎ ማመን ራስን ማታለል ይሆናል። የተካኑት በእሳት ነው። ስልጣናቸውንም የሚሽረው እሳት ነው። የአለም ታሪካዊው እይታም ይህን ይደግፋል። ጋዳፊ፤ ሳዳም፤ ሙባረክ ሌሎችንም በህዝብ የተቀጣጠለ እሳት ነው የለበለባቸው። የወያኔና የሻቢያ እድል ፈንታም ከዚህ ቢከፋ እንጂ አይሻልም። ይብቃኝ፡፡ በዚች ግጥም ልዝጋ።

    ነበረ ይለኛል አገኘው ይመስል
    ቤት እየቆጠረ እሳት እየጫረ
    ነገርን በነገር እየተረጎመ
    ለህዝብ ቁሜአለሁ
    ለሃገር እያለ
    ትላንትን አጥላልቶ
    ዛሬን አሞካሸ
    ለራሱ አመቻችቶ
    ሌላን አባረረ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule