• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የጣዕር ጊዜ አዋጁ” እና ኢትዮጵያ

October 20, 2016 12:10 am by Editor 2 Comments

የጀርመን ድምጽ ሬዲዮ ህወሃት በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ስላወጀው “አትኑሩ” አዋጅና የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ስለሰጡት አስተያየቶች ያቀናበረውን ከዚህ በታች እንዳል አስፍረነዋል።

የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እና ኢትዮጵያ
* “በብሔራዊ ደረጃ የመጣ ጥፋት ነዉ”

የኢትዮጵያ መንግሥት በቅርቡ የደነገገዉን የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ የሚያጠናክሩ ማብራሪያዎችን ይፋ ከተደረጉ ወዲህ የተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ስጋታቸዉን መግለጽ ጀምረዋል።

የጀርመን መራሂተ መንግሥት አንጌላ ሜርክል ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ጋር ከተነጋገሩ በኋላ፤ ይደረጋሉ የተባሉት መሻሻሎች፤ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ትንታኔ ይፋ ሲደረግ በተቃራኒዉ መንገድ የሚጓዝ ነገር መኖር እንደሚያመላክት ነዉ የተጠቀሰዉ። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከዉጭ የሚሰራጩ የሽብርተኛ ድርጅቶች ልሳን ያላቸዉን መገናኛ ብዙሃን ማዳመጥ ያግዳል፤ የዉጭ ሃገራት ዲፕሎማቶችም ከዋና ከተማ አዲስ አበባ ዉጪ ከ40 ኪሎ ሜትር በላይ ሳያሳዉቁ እንዳይወጡም ገድቧል።

ባልተጠበቀዉ የተቃዉሞ ማዕበል ምክንያት የተደነገገዉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በአንድ ወገን የሲቪሉን ኅብረተሰብ የተቃዉሞ እንቅስቃሴ ወንጀል ለማድረግ የሚሞክር መሆኑን የተጨቆኑ ሕዝቦች መብት የሚሟገተዉ የጀርመኑ ገዜልሻፍት ፉዩር በድህሮተ ፎልከር ባልደረባ ዑልሪሽ ዴሊዩስ ይናገራሉ።

«በአንድ ወገን በኦሮሚያ የሚገኘዉን ሲቪል ሕዝብ ማንኛዉንም ዓይነት ተቃዉሞ ወንጀል ለማድረግ የሚሞክር ሲሆን ይህ ደግሞ የፖለቲካ ቀዉስን የሚፈታ ጥሩ መንገድ አይደለም። በዚያም ላይ ለምንድ ነዉ ተቃዉሞዎቹ የቀጠሉት፤ በቅርቡስ የተፈጠረዉ ምንድነዉ፣ እነዚህ ሰዎችስ እስካሁን ለምን በቁጣቸዉ ቀጠሉ፤ ለምንስ በአዲስ አበባ አቅራቢያ የሚገኙ ኩባንያዎችን አቃጠሉ ለሚለዉም ተገቢ ትንታኔ አይሰጥም። አሁን የምናየዉ ባለስልጣናት በገጠሩ አካባቢ የሚደረገዉን ነገር ለመደበቅም በዋና ዋና ጎዳናዎች አካባቢ የ25 ኪሎ ሜትር አደገኛ ቀጠና ተደንግጓል፤ ስለዚህ ዓለም አቀፍ ዲፕሎማቶች በየአካባቢዉ መንቀሳቀስ አይችሉም፤ ለጋዜጠኞች ረዥም ጊዜናት ተቆጥረዋል ተንቀሳቅሰዉ መመርመር እንዳይችሉ ከተገደበ። ስለዚህ እራሳችንን ምንድነዉ የሚደብቁት ብለን እንጠይቃለን። ጋዜጠኞችም ሆኑ የመብት ተቆርቋሪዎች በገጠሩ አካባቢ ምን እንደተፈጠረ መነሻዉን እንዳይመረምሩ እንዲህ ያለ ጠንካራ ገደብስ ማድረግስ ያስፈልጋል ወይ እንላለን።»

መንግሥት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የሀገሪቱን ሰላም እና ፀጥታ ስጋት ላይ የጣሉ ፀረ ሰላም ኃይሎችን ለመቆጣጠር የታለመ መሆኑን ይናገራል። በተቃዉሞ እንቅስቃሴዉ ወቅት የንፁሐን ዜጎች ሕይወት ተቀጥፏል፤ የግል ንብረቶችም በተቃዉሞ አድራጊዎቹ ጉዳት ደርሶባቸዋል። ለመሆኑ ፀረ መንግሥት ተቃዉሞዉ ምን ያህል ሀገሪቱን ወደ ትርምስ ይከታታል ብሎ መገመት ይቻላል? እንደገና ዴሊዩስ፤

«ቢያንስ የእርስ በርስ ጦርነት አፋፍ ላይ ናት የሚል ስሜት አለን ። ነገር ግን መንግሥት  የተደራጀ አሸባሪ ቡድን የሚያካሂደዉ እንቅስቃሴ ነዉ፤ ወይም ደግሞ የዉጭ ኃይሎ እንደ ኤርትራ ወይም ግብፅ ከጀርባዉ አሉ እንደሚለዉ ነዉ ብዬ አላስብም። ጉዳዩ ወደ ዓለም አቀፍ ግጭትነት ይሻገራል ብዬ አልገምትም። ምክንያቱም በመጀመሪያ ደረጃ ይህ ብሔራዊ ግጭት፤ ብሔራዊ ችግር ነዉ። ለምን እነዚህ ሰዎች ጎዳና ላይ ወጥተዉ ይቃወማሉ የሚለዉን ማሰብ አለባቸዉ። ከመንግሥት በኩል ለምን እነዚህ ሰዎች እንደተቆጡ የሚያስረዳ ተጨባጭ ትንታኔ ያለ አይመስለኝም። እናም ይህ ሀገሪቱን በቀጣይ ወራት እጅግ አሳሳቢ ወደ ሆነ ሁኔታ ላይ ሊጥል የሚችል በብሔራዊ ደረጃ የመጣ ጥፋት ነዉ።»Ulrich Delius (Gesellschaft für bedrohte Völker)

ዑልሪሽ ዴሊዩስ እንደሚሉት ይህን መፃኢ ችግር ከወዲሁ ለማስቀረት አስፈላጊ የመፍትሄ መንገዶችን መፈለግ፤ የተመድም ሆነ ዓለም አቀፍ የመብት ተሟጋች ድርጅቶች ምን እየተካሄደ እንደሆነ ጉዳዩን እንዲመረምሩ ማድረግ ወሳኝ ነዉ። ለምድነዉ የኢትዮጵያ መንግሥት ተቃዉሞን ፈፅሞ የሚጠላዉ፤ በተለይ ደግሞ የኦሮሞ እና የአማራ ሕዝቦች የሚያካሂዱትን? ለሚለዉ ጥያቄ የዑልሪሽ ዴሊዩስ ምላሽ እንዲህ የሚል ነዉ፤

«ባለፉት ቀናት በተለይ በዋና ዋና የአማራ አካባቢዎች ኦሮሚያ ዉስጥ የተከሰተዉን በተመለከተ የመተባበር እንቅስቃሴዎች አይተናል። እናም ከዚህ ጠንካራ ገደብ ጀርባ ያለዉ ስጋት በእነዚህ አካባቢ የተነሳዉ ተቃዉሞ ወደሌላዉም የአማራ ክፍል ሊስፋፋ ይችላል የሚል ይመስለኛል። አሁን እኛ በምንነጋገርበት ሰዓት በአማራ ክልል ተፈላጊ በሆነችዉ ጎንደር ከተማ ላይ የሶስት ቀናት የስራ ማቆም አድማ መኖሩ ተሰምቷል። እናም ለዚህ መንግሥት በጣም አስቸጋሪ ነዉ። ምክንያቱም በየጊዜዉ ለዓለም ፀጥታችን የተረጋጋ ነዉ እያለ ባለወረቶችን ለሚጋብዘዉ ለዚህ መንግሥት አስቸጋሪ ነዉ። አሁን መዋዕለ ንዋይ አፍሳሾች በተጠንቀቅ ላይ ናቸዉ፤ ከኢትዮጵያ ስለመዉጣትም እየተናገሩ ነዉ፤  እናም መንግሥት እጠብቀዋለሁ ብሎ በሚሞክረዉ ኤኮኖሚዉ ላይም ከፍተኛ ተፅዕኖ ይኖረዋል።»

ኢትዮጵያ እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ስጋት
«የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከመሪዎቹ በላይ ሆኗል?»

ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች የኢትዮጵያ መንግሥት ለስድስት ወራት የደነገገዉ አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ወትሮም በቋፍ የነበረዉን የሰብዓዊ መብት ይዞታ ወደ ከፋ ደረጃ ሊያሸጋግረዉ እንደሚችል እያሳሰቡ ነዉ።

አምነስቲ ኢንተርናሽናል መንግሥት የሚቀርቡበትን ተቃዉሞዎች ለማቀዝቀዝ የሚወስዳቸዉ ርምጃዎች ይበልጥ አባባሽ እየሆኑ መሄዳቸዉን ትናንት ባወጣዉ መግለጫዉ አመልክቷል። ቻተም ሃዉስ የተሰኘዉ የብሪታኒያዉ ዓለም አቀፍ የፖለቲካ ምርምር ተቋም ለሩብ ምዕተ ዓመት በትረ ሥልጣን ጨብጦ የሚገኘዉ ገዢ ፓርቲ ሚናዉን እና ኅብረተሰቡን የሚረዳበትን ሁኔታ ዳግም ሊያጤን ከሚገባዉ ደረጃ ላይ መድረሱን አሳስቧል።

ከ25 ዓመታት የስልጣን ዘመን በኋላ ገዢዉ የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር በምህጻሩ ኢህአዴግ፤ በጣም ወሳኝ ለዉጥ ማድረግ የሚገባዉ ወቅት ላይ ደርሷል ያላል፤ ቻተም ሃዉስ። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ዉስጥ የደነገገዉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅም የሀገሪቱን ምክር ቤት ወንበሮች ከነአጋር ድርጅቶቹ የተቆጣጠረዉ ኢህአዴግ፤ በሀገሪቱ ሥርዓት ማስከበር አለመቻሉን መቀበሉን እንደሚያመለክትም ቻተም ሃዉስ ትናንት «የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከመሪዎቹ በላይ ሆኗል?» ሲል ይፋ ያደረገዉ ጽሑፍ ይዘረዝራል። ጽሑፉ አክሎም ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ይፋ ባደረጉበት ወቅት፤ የምርጫ ሂደቱ ላይ ማሻሻያ እና ከተቃዉሞ ፖለቲካ ኃይሎች ጋርም ዉይይት ሊደረግ እንደሚችል ጠቁመዉ እንደነበርም ያስታዉሳል።

መረዳት የሚገባዉ ዋናዉ ነገርም በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚታየዉ ተቃዉሞ የተነሳዉ የትጥቅም ሆነ ሰላማዊ የተቃዉሞ እንቅስቃሴ በሚያደርጉ ኃይሎች ሳይሆን ከተራዉ ሕዝቡ መሆኑንም ቻተም ሃዉስ ያመለክታል። አምነስቲ ኢንተርናሽናል በበኩሉ በሀገሪቱ ተቃዉሞዉ የተባባሰዉ መንግሥት ገንቢ በሆነ መንገድ ተቃዋዉን ማስተናገድ ስላልቻለ እንደሆነ በመግለጫዉ ገልጿል። የአፍሪቃ ቀንድ ተመራማሪ አቶ ፍሰሃ ተክሉ እንዴትነቱን ይናገራሉ።

Äthiopien Protesten der Oromo in Bishoftu (REUTERS/File Photo/T. Negeri)አምነስቲ ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለ ፍርድ ቤት ማዘዣ የማሠር እና የተሃድሶ ርምጃዎች ከዚህ ቀደም ሲወሰዱ፤ የተቃዉሞ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ሰዎች በዘፈቀደ እየታሰሩ ቤተሰብም እና ጠበቆቻቸዉ በማያገኟቸዉ ሩቅ በሆኑ ወታደራዊ ጣቢያዎች እንዲታሰሩ ማድረጉን በመግለጫዉ ጠቁሟል። ለስድስት ወራት የሚዘልቀዉ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅም እጅግ ሰፊ እና መሠረታዊ የሰብዓዊ መብቶችን ስጋት ላይ የሚጥል መሆኑን አመልክቷል። በአንድ ሀገር የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ሲታወጅ የመናገር፣ የመፃፍ እና መረጃዎችን በነፃነት የማግኘቱ መብት ሊገደብ እንደሚችል ያመለከቱት አቶ ፍሰሃ፤ ኢትዮጵያ ዉስጥ የተደረገዉ ግን ካለዉ ሁኔታ ጋር የተመጠነ አይደለም ነዉ የሚሉት። አክለዉም ካለፈዉ ዓመት ኅዳር ወር አንስቶ ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚካሄደዉን ሕዝባዊ ተቃዉሞ መንግሥት በኃይል ፀጥ ለማድረግ የሚወስደዉ ርምጃ ያባብሰዋል እንጂ አይፈታዉም ብለዋል። (ሁለቱንም ዘገባዎች ለጀርመን ድምጽ ሬዲዮ ያቀናበሩት ሸዋዬ ለገሠ እና ኂሩት መለሰ ናቸው)

በሌላ በኩል የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ባልደረባ ጽዮን ግርማ ወደ ተለያዩ ሰዎች ደውላ “ከዐዋጁ በኋላ ያላችሁበት አከባቢ ሁኔታ ምን ይመስላል?” ስትል ጠይቃለች።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ድምጽ እዚህ ላይ ያድምጡ።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Rasdejen says

    October 21, 2016 08:29 pm at 8:29 pm

    Well, Western state heads are rather pleased with woyane’s lethal declarations against Ethiopians though we hear here and there some solemn like oratories.
    The German chancellor very visit to the TPLF government at time of Ethiopians in diplomatic communication a gesture of support to the lethal declaration of TPLF.
    Ethiopians should not be deceived with what she talked but with what she did: she visited TPLF while it is killing the innocents.
    Ethiopians need to take immediate action. We need to kill any German in Ethiopia. At the same time, Ethiopians need to demolish any business owned by German so called investors. No, they are invaders. We need to wipe out any Western business from our country. They are friends of TPLF, hence enemies of Ethiopians.
    Ethiopians, take immediate action against German investors and German companies in Ethiopia in Ethiopia.

    Reply
  2. Ras Dejen says

    October 26, 2016 01:30 pm at 1:30 pm

    corr…

    Well, Western state heads are rather pleased with woyane’s lethal declarations against Ethiopians though we hear here and there some solemn like oratories.

    The German chancellor’s very visit to the TPLF government at the time Ethiopians are put under the absolute power of the gun is a gesture of support to the lethal declaration of TPLF, in a diplomatic terms.

    Ethiopians should not be deceived with what she talked but with what she did: she visited TPLF while it is killing the innocents.

    Ethiopians need to take immediate action! We need to kill any German in Ethiopia. At the same time, Ethiopians need to demolish any business owned by Germany so called investors. No, they are invaders!

    Eventually, we need to wipe out any Western business linked to TPLF. They are friends of TPLF, hence enemies of Ethiopians. They may come back afterwards for a fair business r/n rather run in Ethiopia.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule