• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ግልፅ ደብዳቤ ለፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ

October 17, 2016 01:57 am by Editor Leave a Comment

ለፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ
ዋይት ሐውስ
1600 ፔንሲልቫንያ አቬኑ ሰሜን ምዕራብ
ዋሽንግቶን ዲሲ 20500

የተከበሩ ፕሬዚደንት ኦባማ፤

ይህንን ደብዳቤ የምጽፍሎት በኢትዮጵያ ውስጥያለውን የሰብዓዊ መብቶች ሁኔታ ላሳውቆት ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ተጎዳን፣በደል ተፈጸመብን በማለት የሚያሰማውን አቤቱታ፣ ህጋዊ ጥያቄዎችንና ሠላማዊ ሰልፎችን ሁሉ መንግሥት ከማዳመጥ ይልቅ ጉልበትንና ኃይሉን ሁሉ  እንደሚጠቀም ያውቃሉ ብዬ አምናለሁ።

ይህ ሁኔታ ባግባቡ ካልተያዘ በሀገሪቷና በአካባቢው ሁሉ ያልተጠበቀና አስከፊ ሁኔታ ሊከሠት ይችላል።የኢትዮጵያና የዩናትድ እስቴት አሜሪካ ግንኙነት ከ1903 ጀምሮ እንደሆነ ይታወቃል። ስለዚህ የንግድና የወዳጅነት ውል ተፈራርመው ኢትዮጵያም ጥብቅ ወዳጅ ተብላ ትታወቅ ነበር። ኢትዮጵያ በአፍሪካ አብላጫውን የአሜሪካን ረድኤት እንድታገኝምሆኗል። በአጸፋው ኢትዮጵያም የአሜሪካ ወዳጅ በመሆን በዓለምና በአካባቢው ሁሉ ሠላምና መረጋጋት እንዲኖር ከኮሪያ ጦርነት ጀምሮ አስተዋጽኦ አድርጋለች። አሁን በቅርቡ በተከሰተው የአገር ውስጥ ችግሯ  ኢትዮጵያውያንና ለኢትዮጵያ ቀና አመለካከት ያላቸው ሁሉ ዩናይትድ እስቴት አሜሪካ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጎን መቆም እንዳለባትና የኢትዮጵያንሕዝብ በመከፋፈልና ሰብዓዊ መብቶችን በመርገጥ ከታወቀ መንግሥት እራሷን ማራቅ አለባት ይላሉ።

በቅርቡም አንዳንድ ተቋማት እንደ አመንስቲ ኢንተርናሽናል፣ ሂዩማን ዋች ያሉትና የዩስ አሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሥሪያቤት እንደዘገቡት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሁኔታ አስጊ ደረጃ መድረሱን ዘግበዋል። ምንም እንኳን የኢትዮጵያ መንግሥት የሰብዓዊ መብቶች ጥሰትና የከፋፍለህ ግዛ ተግባሩን ላለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ማካሔዱ የታወቀ ቢሆንም አሁን ግን የኢትዮጵያ ህዝብ በቃኝ ከማለቱም በላይ ግፍ የሚሸከምበት ጫንቃ ከእንግዲህ ወዲህ የለኝም በማለት ሥርዓቱን በሰላማዊ መንገድ እየታገለው ነው።

ከዚህ በታች የኢትዮጵያ መንግሥት በሕዝቡ ላይ የሚያደርሰውን ኢዲሞክራሲያዊና ግፍ ለዋቢነት ላቅርብ፦

፩)  በተከታታይ የምርጫ ውጤቶች ተጭበርብረዋል፣ የተቃዋሚ ድርጅቶች መሪዎች፣ ጋዜጠኞችና የመንግሥትን ኢዲሞክራሲያዊ ፖሊሲዎችን የሚተቹ ለእስር ተዳርገዋል። በ2009 መንግሥት ሕዝባዊ ድርጅቶችን የሚገድብ ህግ ደንግጓል። ይህ ህግ ሕዝባዊ ድርጅቶችን፣ ሰብዓዊመብቶችን ለማስጠበቅ የቆሙትንና ተቆርቋሪ ድርጅቶችን አሽመድምዷቸዋል።  የአገሪቷ ህገ መንግሥት በሚፈቅድላቸው መሠረት የመንግሥትን ብልሹ ተግባር በይፋ  የሚቃወሙ ሁሉ ለኢላማ ተዳርገዋል፣ ተጉላልተዋል፣ ለእስር ተዳርገዋል። ስለዚህም እስር ቤቶች ውስጥ ታጉረው እስርቤቶች ጢም ብለው ሞልተዋል። የሚያሳዝነው በቅርቡ የቂሊንጦ ማጎሪያ በአብዛኛው የፖለቲካ እስረኞች በታሰሩበት ወህኒ ቤት የከፋ የእሳት ቃጠሎ አጠያያቂ በሆነ ሁኔታ ተነስቶ ነበር። ከነበልባሉ ሊያመልጡ የሞከሩ እስረኞች እስር ቤቱን ለመጠበቅ ማማ ላይ ባሉ ዘበኞች ተገድለዋል። ስለዚህ በመንግሥት  ቁጥጥርና ከለላ ውስጥያሉት እንኳን ሳይቀሩ በአሳዛኝ ሁኔታ ተገድለዋል።

፪) አገሪቱ ላለፈው አንድ ዓመት በኦሮሞ ክልል በተነሳው ሁኔታ እየተናጠች ነው። የኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄ ህጋዊ የሆነና ከቀዬቻቸው በቂ ምክንያት ተነግሯቸውና ተግባብተው የተፈናቀሉ ሳይሆኑ እንዲሁም ለንብረታቸው ተመጣጣኝ የሆነ ካሣም ተከፍሏቸው አይደለም። ተፈናቃዮች ትምህርት ቤት፣ ህክምና ቤትና መሠረታዊ የሆኑ ሁኔታዎች እንደሚሟላላቸው ቃልቢገባላቸውም  ይህ ባዶ ተስፋ ሆኖባቸዋል። በአንጻሩ ተፈናቃዮች በቀን  ከአንድ ዶላር ያነሰ እየተከፈላቸው ለቀን ሠራተኛነት ተዳረገዋል። ለከብቶቻቸውም የሣር ግጦሽና ውሃ እንኳን ተነፍጓቸዋል።

፫) በቅርቡ በአማራው አገር በጎንደር የተከሰተው ሁኔታ ሆን ተብሎ የወልቃይት ጠገዴን አካባቢ ወደ ትግራይ ግዛት፤የገዢው ክፍል ክልል ውስጥ የማጠቃለል ሁኔታ ነው። የአገሬውም ሰዎች ሆኑ በቀድሞው በአፄው ዘመን አስተዳዳሪ የነበሩት እንደሚሉት ወልቃይት ጠገዴ ትግራይን ከማዋሰን በስተቀር የትግራይ አካል ሆኖ አያውቅም ይላሉ። በታሪክ ግን ትግርኛ ተናጋሪዎች ለሥራ ፍለጋና የተሻለ የኑሮ እድል ፍለጋ በማለት ወደ ወልቃይት ጠገዴ ይመጡ ነበር። አንዳዶቹም እዚያው ኑሮ መስርተው ከአገሬው ሰው ጋር ተጋብተው ሁለት ቋንቋ እየተናገሩ በሰላምመኖር ጀመሩ። ይህ  በኢትዮጵያ ሁሉ የተለመደ ነው።

፬) እራሱ የትግራይ ክልል አንድ ትልቅ ወህኒ ቤት ሆኗል። የሕዝብ ድምፅ ታፍኗል፤ ነፃነቱንም ተገፏል።

፭) የህወሃት መጥረቢያ እንዲሁ በሰሜን ምሥራቅ ኢትዮጵያ በሚገኙት ቀይባህርን የሚያዋስኑ በነበሩት በአፋር ህዝብ ላይ አርፏል። አፋሮችም ከመንግሥት ጋር እየተናነቁ ነው። ምክንያቱም ክልላቸውወደ ትግራይ እየተዋጠ ሲሆን በግዛታቸም ውስጥከጥቅም እየተገለሉ የበይ ተመልካች ሆነዋል። ይህ ሁኔታና የመንግሥት ጎጂ ፖሊሲ በኢትዮጵያ ሁሉ እየተከሰተ ሲሆን ህዝቡም እምቢተኝነቱን እያሳየ ነው።

፮) ምናልባት ታላቁ የመንግሥት ወንጀል በ1991 ዓ.ም. መጀመሪያ ወደ ሥልጣን ከመጣ በኋላ ህዝብን ከህዝብና ያንዱን ሃይማኖት ተከታይ ከሌላው ሃይማኖት ተከታይ ጋር የማጋጨት ተግባሩ ሲሆን እየከፋፈለ እሱ ብቸኛ የበላይ ሃይል ሆኖ ለመቅረት ያደረገው ደባ ነው። ይህ መንግሥት እንደ መንግሥት በህዝብና በሃይማኖቶች መሃከል አቀራራቢ ድልድይ መዘርጋት ሳይሆን ተግባሩ የራሱን ጠባብ ጥቅም ለማስጠበቅ ብቻ የቆመ ነው።

፯) ብዙ የተለፈፈለት የኤኮኖሚዕድገት የሚባለውም የመንግሥት ባለሥልጣናትና ባለሟሎቻቸው ብቻ ጠቀመ እንጂ ለብዙኃኑ ህዝብ ይህን ያህል አልረባም። አንዳንዶቹም በአግባቡና በህጋዊ መንገድ የከበሩ አይደሉም። የህውሃት የንግድ ተቋማትም የአገሪቱን ምጣኔ ሀብት በበላይነት ጨምድደው ያለተፎካካሪ ይዘውታል።

ከዚህ በላይ ከተጠቀሱት ሌላ መንግሥት ወይም ገዢው አካል ከሥልጣን ከወረደ አገሪቱ እንደ ሩዋንዳ የህዝብ እልቂት ይደርስባታል እያሉ ያስፈራራሉ፤ ኢትዮጵያውያን ግን ለዘመናት በሠላምና በመግባባት ኖረዋል። ይህንን ታሪክ ግን ይህ መንግሥት ሆን ብሎ ያጥላላዋል። ኢትዮጵያውያን በትግላቸው ታሪክ ከጨቋኝ መንግሥታት ጋር ነው የተፋለሙት እንጂ የእርስበርስ ፍጅት ከጥቃቅን ግጭቶች ያለፈ አልነበረም። መንግሥት ሆን ብሎ ህዝብ ከህዝብ  እንዲጋጭ የሞከረው ደባ እንዳልተሳካ እንሆ አሁን በምናየው የህዝብ የጋራ ትግል እያየነው ነው። የትግላቸው መርሆ ድምፅም “የአማራው ደም የኦሮሞውም ደም ነው” “የኦሮሞው ደም የአማራውም ደም ነው” ወ.ዘ.ተ.እየተባለ ሲያስተጋባ ነው የሰማነው። እነሆ  ኢትዮጵያውያን አንድነታቸውን እያስመሰከሩ ነው። ዋናው ነገር በታሪክ እደአየነው የህዝብ እልቂት (ጀኖሳይድ) በመንግሥት የሚፈጸም እኩይ ተግባር ነው እንጂ አንዱ ህዝብ በሌላው ህዝብ ላይ የሚያውጀው ዘመቻ አይደለም። ታሪክም ይህን ይመሰክራል። አሁን የህዝቡ ሥጋት ግን ይህ መንግሥት የራሱን ሰዎች ወይም ቅጥረኞችን በህዝብ ላይ ለእልቂት ያሠማራል የሚል ነው። ይህንንም በስውር ደባ በማካሄድ እነሆ ያልኩት ደረሰ ለማለት ነው ።

በመጨረሻም ይህ ጎሰኛ መንግሥት አካባቢውን የሚያረጋጋና የምዕራባውያንን ጥቅም የሚያስጠብቅ ነው ብሎ እራሱን ለማቅረብ ይሞክራል። ባንጻሩ ግን እራሷን ኢትዮጵያን መረጋጋት እያሳጣት ነው። እንዲያውምኢትዮጵያውያን የየራሳቸው የውስጥ ችግር ወደ አለባቸው አገሮች እየሸሹ ነው። ሆን ብለው አልመው ከሚገድሉት የመንግሥት ታጣቂዎች ለማምለጥ አንዳንዶቹ በተቻለ መጠን እየሞከሩ ነው። የኢትዮጵያ መንግሥት የአገሪቱን  የመልክዓ ምድር ፖለቲካ ለእራሱ ጥቅም እያዋለውና የዓለምን ህብረተሰብ እያሳሳተ ነው። በቅርቡ እየተከሰቱያሉት የህዝብ ቁጣና ግንፈላ የመንግሥትን ተመጻዳቂነት የማክሸፍና ሐሰት ለመሆኑ ዋቢነት አለው። በየአገሩ የገነፈሉትን የህዝብ ቁጣዎችን የሚመሩ ይህንን መንግሥት ብቻ  በሚያውቁት በወጣቶችና በሌሎችም ነው። የውሸት ተስፋ ሲመገቡ አድገው አሁን ለአቅመአዳም ሲደርሱ ያ ተስፋ  እውን አልሆነም። ይህም የመንግሥትንየከሰረናእርባነ ቢስ ፖሊሲውን ያሳያል።

ስለዚህ ዩናይትድ እስቴት አሜሪካ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ያለውን ፖሊሲ መቀየር ይኖርበታል። የአሁኑ ኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተው ሁኔታ ሊቀጥል አይችልም። ኢትዮጵያውያን ለሃያ አምስት ዓመታትሙሉ የተረገጠውን መብታቸውን ለማስጠበቅ ተነስተዋል። የመቻል ትዕግሥታቸው እስከ መጨረሻው ሄዷል። ስለዚህ ክቡር ፕሬዚዳንት አደራ የምልዎ አስተዳደሮ ለኢትዮጵያ ያለውን ፖሊሲ እንዲገመገም ቢያደርጉ የሁለቱንም አገሮች የአንድ መቶ አሥራ ሶስት ዓመት ወዳጅነትን ያጠነክራሉ።

እባክዎን ክቡር ፕሬዚዳንት የሥራዎን ዘመን ጨርሰው ከመልቀቅዎ በፊት ከእውነተኛው ታሪክና ከኢትዮጵያውያን ጎን እንጂ ህዝቡን ለአስከፊ ሁኔታ ከዳረገ መንግሥት ጎን እንዳልሆኑ አሁኑኑ ያረጋግጡ።በዚች እየታመሰች ባለችው አገርና በማያስተማምነው የአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ውስጥ ሠላም እንዲሰፍን እርዳታዎን ይለግሡ። ከታሪክ ተጠያቂነት ይዳኑ። ኢትዮጵያ አሁን የሚያስፈልጋት ወደ ባሰ የሰብዓዊ፣ የምጣኔ ሀብትና የፖለቲካ ቀውስ ውስጥ ተንሸራታ እንዳትገባ እጁንየሚዘረጋላትና ዓለምን ከፀፀት የሚያድን ብቻ ነው። በዓለም በሞላፈሰው ያሉት ኢትዮጵያውያንም ድምፅ አልባ ለሆነው ወገናቸው ሁሉ ቀንበቀን በመንግሥት ለችግር ለሚዳረጉ፣ ለሚገደሉ፣ ለሚሰቃዩና ስብዕናቸው ለቆሰለ ሁሉ ድምፅ የመሆንና አጋር የመሆን የሞራልና የታሪክ ግዴታ አለባቸው። የዚህች ታላቅ አገር ታላቅ ህዝብ ከአሁኑ የተሻለ ዕጣ ፈንታ ሊያገኝ ይገባዋል።

ከአክብሮት ጋር፣

ጌታቸው መታፈሪያ፣ ፒኤቺዲ
የፖለቲካል ሳይንስ ፕሮፌሰር
ሞርጋን እስቴት ዩኒቨርሲቲ
1700 ኢስት ኮልድ እስፕሪግ ሌን
ቦልቲሞር, ሜሪላንድ 21251
getachew.metaferia@morgan.edu
ኢትዮጵያና አሜሪካ  ታሪክ፣ ዲፕሎማሲና ትንተና መጽሐፍ ደራሲ። ኒውዮርክ በአልጎራ የታተመ፣ 2009


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule