የኢትዮጵያን ሕዝብ በነጻ አውጪ ስም እስካሁን በግፍ እየገዛ ያለው የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር ሥልጣን በኃይል ከመያዙ በፊት ሲፈጽም የነበረውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ፤ ሥልጣን ከያዘም በኋላ ላለፉት 25 ዓመታት ቀጥሎበታል፡፡ ህወሃት ሥልጣን ከያዘ ጀምሮ በኢትዮጵያ ውስጥ ግፍ ያልተፈጸመበት አካባቢ የለም የሚለው አባባል የተጋነነ አይደለም፡፡ “ኦጋዴን፤ የኢትዮጵያ [የህወሃት] ድብቅ ኃፍረት” በሚል ርዕስ ጋዜጠኛ ግራሃም ፔብልስ በኦጋዴን የሚካሄደውን የሚዘገንን ግፍ ሰኔ 15፤ 2008ዓም (June 22, 2016) ዩትዩብ ላይ ለቋል፡፡ (ዘጋቢ ፊልሙ እዚህ ላይ ይገኛል) “በዛፍ ላይ ለተወሰኑ ደቂቃዎች ሰቅለውኝ ነበር፤ በርካታ ደቂቃዎች ካለፉ በኋላ አወረዱኝ፤ … ከዚያም ካሁን በኋላ የምንልሽን ታደርጊያለሽ አለበለዚያ እንገድልሻለን አሉኝ” የግፍ ዶፍ የወረደባት አናብ … [Read more...] about “ኦጋዴን፤ የኢትዮጵያ [የህወሃት] ድብቅ ኃፍረት”
Archives for June 2016
ህወሃት “አምባሳደሮችን” በታማኞቹ ሊተካ ነው!
በተለያዩ አገራት የሚገኙ አምባሳደሮች በወሳኝ የህወሃት ሰዎች ሊተኩ እንደሆነ ተነገረ፡፡ በህወሃት ውስጥ ያለው ፍርሃቻና አለመረጋጋት ለሁኔታው አስገዳጅነት ምክንያት ሆኖ ቀርቧል፡፡ ህወሃት ለዓመታት ያገለገሉትን ሎሌዎች የማያምናቸው ከሆነ እነርሱም “አለመታመናቸውን” ማሳየት ይገባቸዋል፡፡ በአሜሪካ፤ በአውሮጳ፤ በአውስትራሊያና በኢትዮጵያ አጎራባች በሆኑ አገራት የሚገኙ አምባሳደሮች በቅርቡ ወሳኝ በሆኑ የህወሃት ሰዎች ሊተኩ መታሰቡን ማንነታቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የጎልጉል መረጃ አቀባይ አስታውቀዋል፡፡ ለመረጃው ቅርብ እንደሆኑና የአገራቱም ዝርዝር እንዳላቸው የተናገሩት መረጃ አቀባይ የሹምሽሩ ምክንያት ይህ ነው ተብሎ በውል ባይታወቅም ህወሃት ከውስጥና ጫና ተጠቃሽ እንደሆነ ይጠቁማሉ፡፡ በኢህአዴግ ተለጣፊና ድቃይ ድርጅቶች ታቅፈው የሥርዓቱ ሎሌ የሆኑት አምባሳደሮች በመጪዎቹ … [Read more...] about ህወሃት “አምባሳደሮችን” በታማኞቹ ሊተካ ነው!
አባቱን ነገረኝ
በአባቱ ወንበር ላይ ሳሎን ተቀምጦ በባዶ ግድግዳ ተግ ብሎ አፋጦ የፊቱን ሁኔታ እየለዋወጠ ትካዜ ተጭኖት ቃላት እያማጠ ዓይኑን አጨንቁሮ እየመረመረኝ እንደዚህ እያለ አባቱን ነገረኝ አባቴ... አባባ ኤጭ! አለ ፊቱን አጨማዶ ሁሉን ነገር ጠልቷል ውስጡ ሆኗል ባዶ በምሬት ኮምትሯል ... በጥላቻ በግኗል ... አስሬ ኤጭ! ይላል አባባ ኤጭ! አለ እንደገና ደግሞ በሳሎኑ መሀል ተገትሮ ቆሞ እንደገና ደግሞ ቁጭ አለ አንገት ደፋ ካፍጫው አወጣ እምቅ አየር ተፋ ኤጭ! አለ እንደገና ተነሳና ቆመ ሽቅብ አንጋጠጠ ጣሪያው ላይ ቆዘመ የአባባን ንዴት ይቺን አላውቃትም ከወትሮው ተለየች ብዙ አልወደድኳትም አባባ አሳዘነኝ አዝኜም ፈራሁት ምን ሆንክ? አይባልም በንዲህ ያለ ንዴት አባባ ዓይኑ ቀላ ስሩ ተገተረ በአንድ ጊዜ አረጀ ሀያ ዓመት ጨመረ እንደዛ … [Read more...] about አባቱን ነገረኝ
በሕዝብ ደም የሥልጣን ዕድሜ ማርዘም!
በዓለም ላይ ከሚታዩት መንግሥታት ውስጥ ሁለት ዓይነት መንግሥታት ጎልተው የሚታዩ ሲሆን፤ ሁለቱም ወደ ሥልጣን እርካብ የሚወጡበት መንገድ የተለያየ ነው። አንደኛው በሕዝብ ምርጫና ፍላጎት፣ በዴሞክራሲ መንገድ ሥልጣኑን ለተወሰነ ዓመት የሚረከብ ሲሆን ሌላው ደግሞ በራሱ ፍላጎትና ውሳኔ፣ የሕዝብን ድምፅና ፍላጎት ሳይሰማና ሳይጠይቅ በመሣሪያ ኃይል አስፈራርቶና ደምስሶ የሥልጣኑ ባለቤት የሚሆን ነው። የመጀመሪያውን የስልጣን ባለቤትነትን የሚከተል የግድ የዲሞክራሲን ሕግና ባህል የተቀበለና በዛም የሚያምን መሆንን፣ ችሎታንና ሕዝባዊነትን፣ አገር ወዳድነትን ይጠይቃል። በሁለተኛው የስልጣን አወጣጥ ግን ሃይልን፣ ማንአለብኝነትን፣ የተከተለ ጭካኔን ብቻ የሚጠይቅ ነው። በመሆኑም አምባገነንና ፈላጭ ቆራጭ ተብለው ይጠራሉ ወይም ይመደባሉ። አገራችን ኢትዮጵያ ላለፉት ዘመናት በሁለተኛው ዓይነት … [Read more...] about በሕዝብ ደም የሥልጣን ዕድሜ ማርዘም!
አማኒ ኢብራሂም — “ያልታወቀው” የጥበብ ሰው!
“... ሰው እያለ አጠገባችን፣ ቅንነቱን ማየት ሲያመን ከኛው አብሮ በህይወት ቆሞ፣ መልካም ስሙን መጥራት ሲያንቀን፣ “ሰው ካልሞተ ወይ ካልሄደ አይነሳም” እንላለን። እንዲህ እያልን፣ ስንቱን ጠቢብ እየሸኘን፤ አበባውን ቀጥፈን ጥለን፣ አበባ እናስቀምጣለን!!” መቼም ያለ-ግጥም ፍቅር መኖር የሚሆንልኝ አይመስለኝም። ዛሬ ግን ብዕሬን ያነሳሁት ግጥም ለመጻፍ ባለመሆኑ፣ እነሆ ! የነብይ መኮንን የሆነችውን ይህቺን ግጥም፣ ለተነሳሁለት የጽሁፍ ጭብጥ እንደ መግቢያ ሆና ታግዘኝ ዘንድ ተዋስኩ። ገጣሚ ነብይ መኮንን ይህቺን የቁጭት ስሜት አስተናጋጅ የሆነች ግጥም በመታሰቢያነት ያበረከተው፣ ለእውቁ ሰዓሊና ገጣሚ ገብረክርስቶስ ደስታ ነው። ያ! ድንቅ ኢትዮጵያዊ ሰዓሊና ገጣሚ ደግሞ በመጨረሻው የህይወት ዘመኑ፣ በስደት ባክኖ፣ በሰቀቀን ተጀቡኖ ያለፈው በአሜሪካ—ኦክላሆማ ግዛት ውስጥ … [Read more...] about አማኒ ኢብራሂም — “ያልታወቀው” የጥበብ ሰው!
ተስለክላኪ ዘንዶ – “ሌላም አውሬ ከምድር ሲወጣ አየሁ”
“ወእምዝ ወጽአ ካልዕ አርዌ እምነ ምድር፤ ወበሥልጣኑ ለቀዳማዊ አርዌ ይገብር ኩሎ በቅድሜሁ፤ ወይረስያ ለምድር ከመ እለ ይነብሩ ውስቴታ ይሰግዱ ሎቱ ለቀዳማዊ አርዌ ” (ራዕይ 13፡12) ። ሰሞኑን በቤተ ክርስቲያናችን ዙሪያ በውስጥና በውጭ የሚካሄደውን አየሁ። የሚንጫጫውንም ሰማሁ። ተጽፎ ባነበብኩትና በመገናኛ ዘዴዎች በሰማሁት ጫጫታወች ውስጥ ያለችውን ቤተ ክርስቲያንን እንዴት ልግለጻት ብየ አሰብኩ። በዚህ የሀሳብ ማእበል ውስጥ ሳለሁ፤ በአባይ በርሀ፤ በፊላው ስር ተከሰተ እየተባለ በልጅነቴ ሲነገር የሰማኌት ቀውጢ ትዝ አለችኝ። በዚያች ቅጽበት በተከሰተችው ቀውጢ ክስተት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያኔን አየኋት። ታሪኩ እንደዚህ ነው፦ ሁለት ወንድማማቾች በአባይ ዳር በፊላው ስር ሲሄዱ። ረሀብ አስክሮት የሚያድነውን ነገር እየፈለገ በመቀነዝነዝ ላይ የነበረ የቀትር ዘንዶ ከፊላው ውስጥ … [Read more...] about ተስለክላኪ ዘንዶ – “ሌላም አውሬ ከምድር ሲወጣ አየሁ”
“‘ጭካኔ የተሞላበት አፈና’ – የግድያ እና የእስራት ምላሽ፤ ለኢትዮጵያ የኦሮሞ ተቃውሞ”
ከሰብዓዊ መብቶች ጋር በምንም ዓይነት መልኩ የማይተዋወቀው፤ መተዋወቅና መግባባትም የማይችለው ህወሃት ሰሞኑን “የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን” ብሎ ባቋቋመው ጽ/ቤቱ አማካኝነት “በኦሮምያ ክልል የተቃውሞ እንቅስቃሴ ወቅት በፀጥታ ኃይሎች የተወሰደው እርምጃ አስፈላጊና ተመጣጣኝ ነበር” በማለት ዘገባ ካወጣ ጥቂት ቀናት በኋላ ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ድርጅት ማምሻውን የህወሃትን ቅጥፈት ርቃኑን የሚያወጣ ዳጎስ ያለ ዘገባ ይፋ አድርጓል፡፡ ከዘገባው ጋር በማያያዝ የተወጣው መግለጫ ከዚህ በታች ይገኛል፡፡ (ናይሮቢ፤ ሰኔ 9 ቀን 2008 ዓ.ም) – ከህዳር ወር 2008 ዓ.ም. ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል በተካሄዱ የተቃውሞ ሰልፎች የኢትዮጵያ መንግስት የጸጥታ ሀይሎች ከ400 በላይ የሚሆኑ ሰልፈኞችን የገደሉ ሲሆን ከአስር ሺህ በላይ የሚቆጠሩትን ደግሞ ማሰራቸውን ሂዩማን ራይት ወች ዛሬ ይፋ … [Read more...] about “‘ጭካኔ የተሞላበት አፈና’ – የግድያ እና የእስራት ምላሽ፤ ለኢትዮጵያ የኦሮሞ ተቃውሞ”
ዳግመኛ የመንግሥት ዋይታ በተቃዋሚዎች ላይ
ጁን 11 2016 በፍራንክፈርት ከተማ ላርበኞች ግንቦት7 የድጋፍ ማሰባሰቢያ (Fundraising) ፕሮግራም ላይ ተገኝቼ ስለነበር አንዳንድ ገጠመኞቼን በቦታው ላልነበሩ ለማሰማት የሚለው የዚህ ማስታወሻ መነሻዬ ነው። ዳሩ ግን፤ በሱ ላይ ትረካዬን ከመቀጠሌ በፊት፤ ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲሉ፤ አንድ ከ11 ዓመት በፊት የሆነና በ11.06.2016 ከሆነው ሁኔታ ጋር ተመሳሳይነት የነበረው ድርጊትን ስላስታወስኩ እሱን ላስቀድም! ኖቬምበር 2005 ዓ.ም. አንደኛ/ኮማንደር መስከረም አታላይ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሊቀ-መንበር ሁለተኛ/ አቶ ቱሃት ፖል ቻይ የኢትዮጵያ አንድነት አርበኞች ግንባር ሊቀመንበር፤ ወደጀርመን ሃገር መጥተው ስለኢትየጵያ ጊዜያዊ ሁኔታ፤ ስለየድርጅቶቻቸውም አካሄድና እንዲሁም ሊደረግላቸው ስለሚፈልጉት ድጋፍ ከኢትዮጵያውያን ጋር ውይይት እንዲያደርጉ … [Read more...] about ዳግመኛ የመንግሥት ዋይታ በተቃዋሚዎች ላይ
የህዝብ ደም የፖለቲካ ፀበል አይደለም!
ዱሮ እረኞች በነበርንበት ጊዜ ታላላቆቻችን ይሰበሰቡና እኛን ታናናሾቻቸውንን ጠርተው እርስ በርሳችን ትግል እንድንጋጠምና አሸናፊውም ከዛ ቀን ጀምሮ ላሸናፊው አለቃና አዛዥ እንዲሆን ያደርጉት ነበር፤ ውድድሩ አንዳንድ ጊዜ ከዚህም የከፋ መልክ ነበረው። ተወዳዳሪዎች መደባደሚያ ዥልጥ (የዛፍ ግንጣይ ማለት ነው) ይሰጣቸውና ጎረምሶቹ በተሰበሰቡበት እንዲደባደቡ ይደረጋል። ተጋጣሚዎቹም በፍርሃትና ባልሸነፍም እልህ ከአይንና ጥርስ በቀር አካል ሳይመርጡ ይናረታሉ። ጎረምሶቹ (ባካባቢው አጠራር ውርጋጦቹ) በሳቅ እየተንፈራፈሩ ትርኢቱን በደስታ ይመለከታሉ። ተጋጣሚ ታዳጊዎች ባልሞት ባይ ተጋዳይነት ስሜት እርስ በእርሳቸው ክፉኛ ይጨፋጨፋሉ። እጅግ የሚያሳዝን ትእይንት ነው። በመጨረሻም አቅም ያነሰውን ተጋጣሚ አሸናፊው፥ እመን፥ እያለ ያለርኽራኼ ይቀጠቅጠዋል። ተሸናፊውም ዱላ እያለቀሰ፥ በቃ አመኛለሁ፥ … [Read more...] about የህዝብ ደም የፖለቲካ ፀበል አይደለም!
አስርቱ አምባገነናዊ ትዛዛት!
"እኔ ስላንተ በበረሐ ደሜን አፍስሻለሁና ከእኔና ከአጋሮቼ በቀር ሌላ የፖለቲካ ፖርቲ በቃልህ አትስበክ በልብህም አትመን"፤ "መንግስት የኛ ናትና ወደ መንግስት አትመልከት ስልጣኑንም አትመኝ"፤ "የባለስልጣናትን ጥፋት ... የዜግነት መብቱንም በሶሻል ሚዲያ የተቸ እሱ ወዮለት፤ የባለስልጣን ሚስትም ቅምጥም ሃብትም የማይነኩ፤ የማይደፈሩ "ቅዱስ" ናቸውና ትንፍሽ እንዳትል!! ...." "ከደርግ ጨካኝ አገዛዝ አውጥቼሃለሁና... በፍፁም ልብህ በፍፁም ሃሳብህ ለእኔ ብቻ ተገዛ"፤ "ብሰርቅም፤ ባስርም፤ ብገድልም እንዳለየ እለፍ ... መብራት ቢጠፋ፤ ውሃ ቢቋረጥ ... አርፈህ ተቀመጥ"፤ "እኔ ልማታዊ መንግስትህ በስራዬ ፍፁም የማልሳሳት ነኝና በማስተዳድራት አገር ለሚደርስ ጥፋት ሁሉ የኤርትራን መንግስት ርገም"፤ "ከእኔ አርማ በስተቀር በሰማይ ይሁን በምድር እንዲሁም … [Read more...] about አስርቱ አምባገነናዊ ትዛዛት!