ጁን 11 2016 በፍራንክፈርት ከተማ ላርበኞች ግንቦት7 የድጋፍ ማሰባሰቢያ (Fundraising) ፕሮግራም ላይ ተገኝቼ ስለነበር አንዳንድ ገጠመኞቼን በቦታው ላልነበሩ ለማሰማት የሚለው የዚህ ማስታወሻ መነሻዬ ነው። ዳሩ ግን፤ በሱ ላይ ትረካዬን ከመቀጠሌ በፊት፤ ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲሉ፤ አንድ ከ11 ዓመት በፊት የሆነና በ11.06.2016 ከሆነው ሁኔታ ጋር ተመሳሳይነት የነበረው ድርጊትን ስላስታወስኩ እሱን ላስቀድም!
ኖቬምበር 2005 ዓ.ም. አንደኛ/ኮማንደር መስከረም አታላይ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሊቀ-መንበር ሁለተኛ/ አቶ ቱሃት ፖል ቻይ የኢትዮጵያ አንድነት አርበኞች ግንባር ሊቀመንበር፤ ወደጀርመን ሃገር መጥተው ስለኢትየጵያ ጊዜያዊ ሁኔታ፤ ስለየድርጅቶቻቸውም አካሄድና እንዲሁም ሊደረግላቸው ስለሚፈልጉት ድጋፍ ከኢትዮጵያውያን ጋር ውይይት እንዲያደርጉ ፕሮገራም ይዘጋጅላቸዋል፤ እነዚህን ሁለት ሰዎች ወደጀርመን አገር ጋብዘው ያስመጧቸው አቶ ከሳየ መርሻ የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር የውጭ አካል የአመራር አባል ከሌሎች ተባባሪዎቻቸው ጋር በመሆን ነበር። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)
“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡
Leave a Reply