• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አባቱን ነገረኝ

June 22, 2016 08:22 am by Editor Leave a Comment

በአባቱ ወንበር ላይ ሳሎን ተቀምጦ
በባዶ ግድግዳ ተግ ብሎ አፋጦ
የፊቱን ሁኔታ እየለዋወጠ
ትካዜ ተጭኖት ቃላት እያማጠ
ዓይኑን አጨንቁሮ እየመረመረኝ
እንደዚህ እያለ አባቱን ነገረኝ

አባቴ…
አባባ ኤጭ! አለ ፊቱን አጨማዶ
ሁሉን ነገር ጠልቷል ውስጡ ሆኗል ባዶ
በምሬት ኮምትሯል …
በጥላቻ በግኗል …
አስሬ ኤጭ! ይላል
አባባ ኤጭ! አለ እንደገና ደግሞ
በሳሎኑ መሀል ተገትሮ ቆሞ
እንደገና ደግሞ ቁጭ አለ አንገት ደፋ
ካፍጫው አወጣ እምቅ አየር ተፋ
ኤጭ! አለ እንደገና ተነሳና ቆመ
ሽቅብ አንጋጠጠ ጣሪያው ላይ ቆዘመ

የአባባን ንዴት ይቺን አላውቃትም
ከወትሮው ተለየች ብዙ አልወደድኳትም
አባባ አሳዘነኝ አዝኜም ፈራሁት
ምን ሆንክ? አይባልም በንዲህ ያለ ንዴት

አባባ ዓይኑ ቀላ ስሩ ተገተረ
በአንድ ጊዜ አረጀ ሀያ ዓመት ጨመረ
እንደዛ ሆነብኝ
አባባ አሳዘነኝ
አዝኜ ዝም አልኩት
ከድሮው ጨምሬ ደርቤ ፈራሁት
አባባ ምን ነካው …?
እንዴት ልጠይቀው ?
ዓይን ዓይኑን እያየሁ
ብዙ ተቀመጥኩኝ በዝምታ ቆየሁ

ሲመሽ ወደ ማታ ልሄድ ተነሳሁኝ
ዝምታዬን ላፈርጥ ከቤቱ ወጣሁኝ
ዝምታን አፈረጥኩ …
አባባን ረሳሁ መልካም ቀኔን አደስኩ
ቢራን የፈጠረ – ይመቸው ተባለ
ተበላ ተጠጣ ጨዋታ ቀጠለ
በጨዋታ ፈካሁ
በቢራው ወረዛሁ
እስከ ፍጥርጥሩ ሁሉንም ረሳሁ
ቢራው አበቃና አልኮል ተጀመረ
አገር ቀውጢ ሆነች ለጉድ ተጨፈረ
እኩለ ለሊት ላይ መጠጥ እያገሳሁ
ዝምታን ደፍጥጨ ሁሉን እንደረሳሁ
ስካሬን አዝዬ እቤቴ ስመለስ
ከሳሎን ገብቼ መብራቱን ስለኩስ

አባባ ጉድ ሰራኝ ኤጭ! እንዳለ ሄዷል
የጠላትን ሕይወት ጥሏት ተሰናብቷል
አባቴን ጠየኩት
ምነው? አባባ አልኩት
በሕይወት ፈርቼ በሞቱ ደፈርኩት
እያለ አወራልኝ
አባቱን ነገረኝ

ሀዘኑ በረታ ጓደኛዬ ከፋው
አይኖቹ ወረዙ እንባ ፊቱን ሞላው
ምነው ባልወጣሁኝ ባልሄድኩኝ  እያለ
አባቱን አስታውሶ በቁጭት ከሰለ
እንዴት አይዞህ ልበል ፍራት ፍራት አለኝ
መልኩ ተለወጠ አባቱን መሰለኝ
ኤጭ! አለ እንደ አባቱ  ኤጭታውን ጠላሁ
አሳዘነኝ ጓዴ አዝኔ አይዞህ ፈራሁ
እንደገና ቆመ አጨማዶ ፊቱን
ይንጎራደድ ጀመር ዙርያውን የቤቱን
ልክ እንደነገረኝ
ልክ እንዳወራልኝ
በሁሉም ነገሩ አባቱን ቢመስለኝ
ትቼው መሄድ ፈራሁ – ማደሩም ቀፈፈኝ።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule