• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሃት “አምባሳደሮችን” በታማኞቹ ሊተካ ነው!

June 22, 2016 08:43 am by Editor 2 Comments

በተለያዩ አገራት የሚገኙ አምባሳደሮች በወሳኝ የህወሃት ሰዎች ሊተኩ እንደሆነ ተነገረ፡፡ በህወሃት ውስጥ ያለው ፍርሃቻና አለመረጋጋት ለሁኔታው አስገዳጅነት ምክንያት ሆኖ ቀርቧል፡፡ ህወሃት ለዓመታት ያገለገሉትን ሎሌዎች የማያምናቸው ከሆነ እነርሱም “አለመታመናቸውን” ማሳየት ይገባቸዋል፡፡

በአሜሪካ፤ በአውሮጳ፤ በአውስትራሊያና በኢትዮጵያ አጎራባች በሆኑ አገራት የሚገኙ አምባሳደሮች በቅርቡ ወሳኝ በሆኑ የህወሃት ሰዎች ሊተኩ መታሰቡን ማንነታቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የጎልጉል መረጃ አቀባይ አስታውቀዋል፡፡ ለመረጃው ቅርብ እንደሆኑና የአገራቱም ዝርዝር እንዳላቸው የተናገሩት መረጃ አቀባይ የሹምሽሩ ምክንያት ይህ ነው ተብሎ በውል ባይታወቅም ህወሃት ከውስጥና ጫና ተጠቃሽ እንደሆነ ይጠቁማሉ፡፡

በኢህአዴግ ተለጣፊና ድቃይ ድርጅቶች ታቅፈው የሥርዓቱ ሎሌ የሆኑት አምባሳደሮች በመጪዎቹ ሳምንታትና በሐምሌ ወር ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ እንደሚደረግ ታውቋል፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የሚደረግ ዓመታዊ ስብሰባና ግምገማ ተብሎ ሽፋን የሚሠጠው ይኸው አምባሳደሮችን የመጥራት ውሳኔ በህወሃት ሰዎች የተቀነባበረና የትኞቹን አምባሳደሮች በማን ለመተካት እንደታሰበ አስቀድሞ የተወሰነ ነው፡፡ በዓለምአቀፍ የዲፕሎማሲ ህግጋት መሠረት የሚነሱት አምባሳደሮች መረጃ ለየአገራቱ ደርሷል፡፡

ለ25 ዓመታት እጅግ አሰቃቂ ወንጀሎችን በመፈጸም በነጻ አውጪ ስም ኢትዮጵያን በፍግ እየገዛ ያለው የትግራይ ነጻ አውጪ ግምባር ከፍተኛ ችግር ውስጥ በሚወድቅበት ጊዜ ታማኝ የትግራይ ተወላጆችን በተለይም ነባር ታጋዮች ላይ አመኔታውን በማድረግ “ክፉ ጊዜያትን” ሲያልፍ ቆይቷል፡፡ የአሁኑም ጉዳይ ከዚህ የተለየ እንዳልሆነ ነገራል፡፡

በተለይ በሰብዓዊ መብት ረገጣ እያደረሰ ያለው ግፍ ከበቂ በላይ በሆነ ማስረጃ በተደጋጋሚ እየወጣበት ባለበት ባሁኑ ጊዜ የወደፊቱ ሁኔታ ምን ሊሆን ይችላል የሚለው መመለስ ያለበት ጥያቄ ሆኗል፡፡ ለዚህም ይመስላል በሰሜኑ ኢትዮጵያ ከአማራው ክልል ጋር ተያይዞ ያለውን አደገኛ ሁኔታ ለማምከን የኤርትራ ካርዱን የመዘዘው በማለት አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ፡፡ ወራትን ያስቆጠረው የኦሮሞ ወጣቶች ተቃውሞ ከሁሉም በላይ አረመኔነቱንና ለሥልጣኑ ሲል የማይፈጽመው ወንጀል እንደሌለ በግልጽ ያሳየ መሆኑን ሰሞኑን የወጣው የሰብዓዊ መብት ተመልካቹ መ/ቤት (ሂውማን ራይትስ ዎች) ዘገባ ያሳያል፡፡

በተለይም በያዝነው ዓመት ጥር ወር አካባቢ የአውሮጳ ፓርላማ ኢህአዴግን “ልክ የሚያስገባ” ባለ 19 ነጥብ ውሳኔ ማስተላለፉ ይታወቃል፡፡ በወቅቱ ውሳኔው ኢህአዴግ “ልክ ሊገባ ይሆን” የሚል አመለካከት መጫሩን ጎልጉል ጠቅሶ በጻፈበት ወቅት “ረቂቁ ለውይይት እንዳይቀርብ የቻሉትን ያህል የጣሩት ቴድሮስ አድሃኖም “ዲፕሎማሲያቸው” አለመሥራቱን፤ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ውሳኔው “ውስጡ በብረት የተወጠረ የቦክስ ጓንቲ ነው” ማለታቸውን ጨምሮ ዘግቦ ነበር፡፡ ይህ በዝርዝር መረጃ ቀርቦበት ለውሳኔ የበቃው ሰነድ ቀኑን ጠብቆ ህወሃት ላይ ሰይፉን እንደሚመዝ የወንጀሉ ተዋናዮች ከማንም በላይ የሚረዱት እውነታ ሆኗል፡፡

በአሜሪካ፤ ወሳኝ በሆኑ የአውሮጳ ከተሞች (ህብረቱ ያለበትንም ጨምሮ) እንዲሁም በኢትዮጵያ አጎራባች አገራት ያሉ አምባሳደሮች በታማኝ የህወሃት ተጋዳላዮች ለመተካት መታሰቡ የዲፕሎማሲው ተጽዕኖ ያስከተለው ጫና ብቻ ሳይሆን በህወሃት ውስጥ ሌላም ፍርሃቻ ስለአለ ነው በማለት ጉዳዩን ከሌላ አንጻር የሚመለከቱ ይናገራሉ፡፡

አሊ ኦጃሊ
አሊ ኦጃሊ

ምዕራባውያን ኃይላት ትኩረታቸውን ሊቢያ ላይ አድርገው ጋዳፊን ከሥልጣን ለማውረድ እንቅስቃሴ በጀመሩበት ወቅት ዓመጹ እየተፋፋመ ሲሄድ በየአገሩ የነበሩ የጋዳፊ ታማኞች መክዳታቸው ይታወሳል፡፡ ጋዳፊ ህይወታቸው በOctober 2011 ከማለፉ ስምንት ወራት በፊት በዋሽንግተን ዲሲ ታማኝ አድርገው ያስቀመጧቸው አምባሳደር አሊ ኦጃሊ ጋዳፊን መክዳታቸው ይታወቃል፡፡ ለጋዳፊ ታማኝ በመሆን አርባ ዓመት ያህል ያገለገሉት አምባሳደሩ በወቅቱ ከከዱ በኋላ የአማጺውን ኃይል ተቀላቅለው ነበር፡፡ ከዚህ አልፈው በአሜሪካ የአማጺው አፈቀላጤና ተወካይ በመሆን ሲሰሩ ከቆዩ በኋላ የጋዳፊ መውደቅ እውን እየሆነ ሲሄድ አሜሪካ መልሳ በቦታቸው አስቀምጣቸው ነበር፡፡ ከዚህ አንጻር ህወሃትን ያስፈራው ይህንን መሰል የፖለቲካ ቁማር እንደሆነ ይነገራል፡፡

ከሎሌነት ባላለፈ አገልግሎት የሚሰጡትን “የራሴ፤ ታማኞቼ” ከሚላቸው ጋር ፈጽሞ እኩል ሊያደርጋቸው የማይፈልገው ህወሃት የፖለቲካው ትኩሳት አቅጣጫውን የቀየረ ዕለት የአሊ ኦጃሊን መንገድ ሊከተሉ ይችላሉ ብሎ የጠረጠራቸውን በቶሎ ለመተካት መወሰኑ “ከጋዳፊ ተምረናል” የሚል እንድምታ እንዳለው ይነገራል፡፡ በየትኛውም የለውጥ እንቅስቃሴ ጊዜ በተለይ በጎረቤትና በኃያላን አገራት ያሉ አምባሳደሮች መክዳት አልፎም ንቅናቄውን መቀላቀል የአምባገነኖችን ዕድሜ በማሳጠር በኩል ቁልፍ ሚና ይኖረዋል የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች ህወሃት ምዕራባውያን በተገኘው አጋጣሚ ፊታቸውን እንደሚያዞሩበት በመገመት ይህንን መሰሉን ጥንቃቄ ማድረጉ ሥልጣኑን እንዴት እንደሚንከባከብ የሚያሳይ ነው፡፡ በተለይ የኦህዴድ መሸርሸርና በክልሉ ያለው ዓመጽ እስካሁን አለመብረድ ከአምባሳደር ጀምሮ እስከ በታች እርከን የቆንስላ ተግባራት ላ የተሰማሩ ኦሮሞ ዲፕሎማቶችንና ሠራተኞችን በዓይነቁራኛ እንዲታዩ እያደረጋቸው ነው፡፡ ከዚህ አንጻር “ለችግር ጊዜ አትታመኑም” ተብለው እንደሸቀጥ እንዲመለሱ የሚጠሩት አምባሳደሮች ቀን ፊቷን ሳታዞርባቸው ለምንስ በእርግጥ “የማይታመኑ መሆናቸውን” ለህወሃት አያሳዩትም በማለት የዜናው አቀባይ ለዲፕሎማቶቹ ጥሪ አዘል ምክር ለግሰዋል፡፡   (ፎቶ: ያለፈው አመት ሹመኞች)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. gud says

    June 25, 2016 07:06 pm at 7:06 pm

    Shabian days are numbered !

    With that the days of parasite diasporas will come to an end ! Death to HGDF and it’s brainless servants !

    Reply
  2. Kebede says

    July 7, 2016 07:30 pm at 7:30 pm

    This is just another creative essay writing. Just propoganda.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule