የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) በመቀሌ ከተማ ባደረገው ስብሰባ ላይ በጥንቃቄ ተመርጠው የተጠሩ ታማኝ ካድሬዎችና አባላት የተቃውሞ ድምጻቸውን አሰሙ፡፡ የትግራይ ፌስቡክ ተጠቃሚዎች አብዮታዊ እርምጃ ሊወሰድባቸው መሆኑ በአባይ ወልዱ የሚመራው የህወሓት አንጃ አሳወቀ። አንጃው ይህንን አብዮታዊ እርምጃ እንደሚወስድ ያሳወቀው “12ተኛ ጉባኤ እንዴት አለፈ …?" በሚል አጀንዳ በየመንግሥት መስርያ ቤቶች፣ ከመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች፣ የክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች ካድሬዎችና ነዋሪዎች ውይይት በተካሄደበት ጊዜ ነው። በመቀሌ ማዘጋጃ ቤት ማክሰኞ 3/13/2007 ዓም በአቶ ተስፋአለም ተወልደብርሃን (የመቀሌ ከንቲባ)፣ አቶ አሰፋ ተገኝ ምክትል ከንቲባ የተመራ ስብሰባ የተካሄደ ሲሆን “የህወሓት ጉባኤ ምን ይመስላል?” የሚል አጀንዳ ተሰጥቶት ነበር። የትግራዩ አንጃ በጉባኤው ወቅት … [Read more...] about “ታማኝ ካድሬዎችና አባላት በህወሃት ስብሰባ ላይ ተቃውሞ አሰሙ”
Archives for September 2015
ሳሞራ ወይስ ሕወሃት “ሕገመንግሥቱን” የጣሱት? ወይስ ሁለቱም?
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር ስብሰባ ባደረገበት ወቅት ሳሞራ የኑስ ህወሃትን ለብሰው፣ ህወሃትን አጥልቀው (ጫማቸውና ሌላው አይታይም እንጂ) ህወሃትን ሆነው ታይተዋል፡፡ “ተጋብዘው ነው” ለማለት ለምትፈልጉ እንትኖች መልሱ ህወሃት ላይ ተጋብዘው ከተገኙ ወደፊት እንደ ሰማያዊ፣ መድረክ፣ ወዘተ ያሉ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች በሚያደርጉት ስብሰባ ላይ የፓርቲዎቹ አርማ ያለበት ባርኔጣ አድርገው ይገኛሉ ማለት ነው - የተነፈሰ ሃሳብ ነው፡፡ ሳሞራ ህወሃትን ሲያይ ዋለ ተቃዋሚ ፓርቲ የት ነሽ እያለ ከነጠላው ፉከራ መልስ - “ሕገመንግሥቱ” ያለጥርጥር ተጥሷል፤ ይህ ከሆነ ደግሞ “ሕገመንግሥቱንና ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ …” በሚል ክስ መመሥረት አለበት ማለት ነው፡፡ ይህ ሲሆን ተከሳሽ “አሸባሪ” ሊባል ነው፡፡ ከዚያ ተከሳሽ ወደ … የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር … [Read more...] about ሳሞራ ወይስ ሕወሃት “ሕገመንግሥቱን” የጣሱት? ወይስ ሁለቱም?
ጀርመን አገር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንና የግብጽ ኮፐቲክ ቤተክርስቲያን የጋራ ሲኖዶስ አቋቋሙ!
በጀርመን የኦርየንታል (የመካከለኛው ምስራቅ) ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያናት አንድ የጋራ ሲኖዶስ ለመመስረት ስለፈለጉ፤ ትላንት የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የመጀመሪያውን እርምጃ ወስደዋል። በዚህም መሰረት ጳጳስ አንባ ዳሚያን (የኮፐት ኦርቶዶክስ) እና ሊቀጳጳስ ሙሴ (የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ) ውል ተፈራርመዋል። በኮፕት ገዳም የውል ሰነድ ፊርማ፤ ሊቀጳጳስ ሙሴ (2. ከገራ ወደቀኝ) እና ጳጳስ አንባ ዳሚያን (የመካከለኛው ) (ከመሃል) ፊረማቸውን በውሉ ሰነድ ላይ አስቀመጡ። በዚሁ ጊዜ በቦታው የነበሩ፤ አባ ዳዊት ሙሳ ከግብጽ እንዲሁም የገዳሙ ጎብኝ እንግዶች/ካቶሊኮች/ ሞሲኞር ፔተር ፎን ሸታይኒትጽ (ከግራ) እና ዲያቆን ክርስቶፍ ፐሪንስ ቤተልሄም (ከቀኝ) እንዲሁም ሚዛን ገብሩ (ሁዋላ ከግራ) ማግዳሌና ግርማ፤ ሳራ ኪዳኔ እና ሞገስ ተሾመ … [Read more...] about ጀርመን አገር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንና የግብጽ ኮፐቲክ ቤተክርስቲያን የጋራ ሲኖዶስ አቋቋሙ!
ሻዕቢያ ህወሃትን አስጠነቀቀ
ቀደም ሲል የአባትና ልጅ “አፈጣጠርና ግንኙነት” የነበራቸው ወዳጆች ሻዕቢያና ወያኔ ያልተጠናቀቀውን የባድመን ጦርነት ካካሄዱ በኋላ ለዳግም ግጥሚያ ዝግጅት እያደረጉ ነው። “የጦርነቱ ሁኔታ” ያሳሰበው ሻዕቢያ በማስታወቂያ መ/ቤቱ በኩል ለህወሃት ማጠንቀቂያ ሰጥቷል። ከጥቂት ሳምንታት በፊት ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በዘገበው መሠረት መግለጫው ህወሃት ኤርትራን እንዲወጋ የአሜሪካንን ይሁንታ አግኝቷል ብሏል። የፈረንጅ የቀን አቆጣጠር የሚከተለው ሻዕቢያ በማስታወቂያ መ/ቤቱ በኩል 4 September 2015 ያወጣው መረጃ እንደጠቆመው ህወሃት የተለመደውን የጦርነት አታሞ እየመታና ሳንጃ እየሳለ እንደሆነ ጠቁሟል። የህወሃት አገዛዝ “ሌሎች ክፍሎች ከኤርትራ ጋር እንዳይወግኑ ትንኮሳ እያደረገ” መሆኑን የጠቆመው መግለጫ ወያኔ በኤርትራ ጦርነት ማካሄድ እንዲችል ከአሜሪካ ይሁንታ ማግኘቱን በገሃድ … [Read more...] about ሻዕቢያ ህወሃትን አስጠነቀቀ
በኢትዮዽያ ዲሞክራሲ ለመመስረት የሚደረጉ የትግል ስልቶች ተደጋጋፊነት እና አሰፈላጊነት
ይህ ጽሁፍ በኢትዮጵያ እየተደረገ ያለዉን ዲሞክራሲን ለመመስረት በመደረግ ላይ ያሉትን የትግል ስልቶች መርምሮ ፤ የሁለቱን የትግል ስልቶች ተደጋጋፊነት እና ተቀናባሪነትን አቅርቦ ለዉጥ ለማምጣት አብሮ መስራት አስፈላጊነቱን ያቀርባል። በኢትዮጵያ ያለውን ዘረኛ መንግስት ለማስወገድ የሚደረገው ትግል የተለያዩ ድርጅቶች የተለያዩ የትግል ስልቶች መምረጣቸዉ ይታወቃል። የሁሉም ድርጅቶች አላማ ያለዉን ዘረኛ መንግስት ማዉረድ ቢሆንም፤ የመረጡት የተለያዩ የትግል ስልቶች በድርጅቶቹ መካከል ትብብር እንዳይጎለብት ማድረጉ ግልጽ ነዉ። ዋናዉ የዚህ ጽሁፍ አላማ፤ እነዚህ የትግል ስልቶች ተደጋጋፊ መሆናቸው እና ተቀነባበረዉ የተሻለ የትግል ዉጤት ማምጣት የሚችሉ መሆናቸውን መገንዘብ ያስፈልጋል የሚል ነዉ። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) “ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” … [Read more...] about በኢትዮዽያ ዲሞክራሲ ለመመስረት የሚደረጉ የትግል ስልቶች ተደጋጋፊነት እና አሰፈላጊነት
ከዝምታው በስተጀርባ
አንዳንድ ወገኖች የወያኔ አገዛዝ መቶ በመቶ አሸነፍኩ ያለበት ደረጃ መድረሱ እያበገናቸው፣ በሀገርና በሕዝብ ላይ የሚደርሰው ጥፋት እያስቆጫቸው የሕዝቡን ዝምታ በፍርሀት ሲገልጹት ይሰማል፡፡ አንዳንዶች እንደውም ገፋ አድርገው በቅርብ ግዜ የታየውን የአረብ አብዮት እየናሱና ተኒዚያና ግብጽን እየጠቀሱ ኢትጵያዊ በምን ያንሳል በማለት በምሬት ይናገራሉ ይጽፋሉ፡፡ የአረብ አብዮት አይነት ሰላማዊ የሕዝብ ተቃውሞና አምቢተኝነት ወያኔ አጥብቆ የሚፈራው፣ ተቀዋሚው ቢሆን የሚሻው፣ የኢትዮጵ ሕዝብ ሊያደርገው የማይችለው ነው፡፡ ሁሉም የየራሳቸው ምክንያት አላቸው፡፡ ወያኔ በሕዝብ አለመወደዱን ማወቁ፣ ለሥልጣኑ መስጋቱና ፍርሀቱ ሲሆን ፤ተቀዋሚው ለውጥ መሻቱ፣ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን መናፈቁ ነው፡፡ ሕዝቡ የማያደርገው ደግሞ ከጥንት እስከ ዛሬ የኖረበት ወግ ልማዱ ስላልሆነ፣ ትናንት ንጉሶች በቅርቡ ደግሞ … [Read more...] about ከዝምታው በስተጀርባ
የኤርትራ ጉዳይ
ለብዙ ኢትዮጵያዊያን፤ የኤርትራ ከኢትዮጵያ መገንጠልና የአገነጣጠሏ ሁኔታ፤ የውስጥ አካላችንን ያኔም፣ አሁንም እያንጠረጠረው ነው። በርግጥ በየኪሳችን ያለ የየግል ንብረት ስለተነጠቀብን አይደለም። በኤርትራ መገንጠል የቀረብን የግል ጥቅም ስለነበረም አይደለም። የሀገር ጉዳይ፤ ከንብረት፣ ከአባትና እናት፣ ከኑሮ የበለጠ ክብር የምንሠጠው ነው። በወቅቱ የቅርብ ጓደኛዬ የነበረ ኤርትራዊ፤ በኤርትራ መገንጠል ፍንደቃው ጊዜ አልሠጥህ ብሎት፤ መኖሬንም ረስቶ፤ ለሳምንታት ከወገኖቹ ጋር ሲጨፍር ከረመ። በመጨረሻም ቀን ቀንን እየወለደ፤ ሳንገናኝ ብዙ ጊዜ አለፈ። መራራቅ መራራቅን ነውና የሚያስከትለው፤ በየጎጣችን ተሸጉጠን፤ በመካከላችን የነበረው ጓደኝነት፤ ጊዜን መቀራረብ አላድሰው አለና ጠፋ። በርግጥ እኔም መላዕክ አልነበርኩም። ልክ ያለሁበት ቤት እንደተቃጠለ፤ በግል ሰው እንደበደለኝ፤ ብሽቀት … [Read more...] about የኤርትራ ጉዳይ
Saluting the greatest Ethiopian “Masinko” man and dissident artist Shambel Belayneh
“Enlighten the people generally, and tyranny and oppressions of body and mind will vanish like evil spirits at the dawn of the day.” -TJ Behold, he is daring, he is a rebel and the fearsome black lion is roaring. “Endyaw zerafewa endeyaw zerafewa, Ye Gondern meret ye humeran meda, Tedanegbet enji mech dagnebet bada. Wede temari bet temeleshi kine, Wendoch kewalubet ewelalhu ene.” Millions of his fans often say Shambel Belayneh is the undisputed successor to the late legendary … [Read more...] about Saluting the greatest Ethiopian “Masinko” man and dissident artist Shambel Belayneh
የኢሳያስ (የሻዕቢያ) ስታራተጂ፤ ኢትዮጵያን ለመታደግ ወይስ እንደገና ለመግደል?
የተለያዩ ድርጅቶች የወያኔ/ ኢህአዴግን መንግስት በትጥቅ ሀይል ለማስወገድ በአስመራ ስልጣን ከያዘው ሻቢያ ጋር መቀራረብና ተባብሮ መስራትን መርጠዋል። ይህን በተመለከተ ባንድ በኩል የወያኔ/ኢህአዴግን የግፍ ስርአት ለማስወገድ ከማንም ጋር ቢሆን ማበር አስፈልጊ ነው የሚሉ ሲኖሩ ሌሎች ደግሞ የወያኔን የግፍ ስርአት ማስወገድ አስፈላጊ ሲሆን ሻዕቢያ ኢትዮጵያን በተመለከተ የሚከተለው ፖሊሲ በብሄራዊ ጥቅማችን ላይ እና በመጻኢው ነጻነታችን ላይ እጅግ ታላቅ አደጋን ስለሚያሰከትል ድንገት ብቅ ያለው ተቋርቋሪነት ከምን የመነጨ እንደሆነ ጠንቅቆ መረዳትና ታላቅ ስህተት ከመፈጸም መታቀብ ያሻል ይላሉ:: በዚህ ጽሁፌ የሻቢያ “ለኢትዮጵያ ተቆርቋሪነት” በተግባር ሲታይ ምን ማለት እንደሆነ ለማሳየት በጥቂት ውሱን ጉዳዮች ላይ በማተኮር ያለኝን አመለካከት አካፍላለሁ። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ … [Read more...] about የኢሳያስ (የሻዕቢያ) ስታራተጂ፤ ኢትዮጵያን ለመታደግ ወይስ እንደገና ለመግደል?
ጤፍ እንኳን ባቅሟ!
ትንሿ የ'ሕል ዘር፤ ዐይን እንኳ ብትገባ የማትቆረቁር፤ ድንገት ጠብ ብትል የማትገኝ ከምድር፤ ቁልቁል አሾልቃ በንቀት እያየች፤ በድሃው ወገኔ ከት ብላ ሳቀች! ........ እጅጉን አሾፈች:: አሹቅህን አውልቅ - ሽንብራህን ቆርጥም፤ ባቄላህን ጠርጥር - በቆሎህን ከርትም፤ እኔን ካሁን ወዲያ እንኳን ልትበላኝ፤ ድንገት በመንገድ ላይ ባይንህም አታየኝ፤ እያለች አፌዘች፤ በወገኔ ሳቀች !.......... በወገኔ አሾፈች !! አረም እንዳይውጣት - ወፎች እንዳይለቅሟት፤ ካቡን ዙሪያ ክቦ - ከብቶች እንዳይበሏት፤ አጭዶና ከምሮ - በሬዎች ለጉሞ፤ ሲወቃ እንዳልዋለ - ቀኑን ሙሉ ቆሞ_ _ _፤ በመንሽ አበጥሮ - በቁና ለክቶ፤ በሰፌድ አንፍሶ - በስልቻ ከቶ፤ ነቀዝ እንዳይበላት - ብርድ እንዳያጠቃት፤ ወቅቶ በጎተራ - እንዳላስቀመጣት_ _ _፤ አንተ አትቀምሰኝም! … [Read more...] about ጤፍ እንኳን ባቅሟ!