• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከዝምታው በስተጀርባ

September 5, 2015 09:15 am by Editor Leave a Comment

አንዳንድ ወገኖች የወያኔ አገዛዝ መቶ በመቶ አሸነፍኩ ያለበት ደረጃ መድረሱ እያበገናቸው፣ በሀገርና በሕዝብ ላይ የሚደርሰው ጥፋት እያስቆጫቸው የሕዝቡን ዝምታ በፍርሀት ሲገልጹት ይሰማል፡፡ አንዳንዶች እንደውም ገፋ አድርገው በቅርብ ግዜ የታየውን የአረብ አብዮት እየናሱና ተኒዚያና ግብጽን እየጠቀሱ ኢትጵያዊ በምን ያንሳል በማለት በምሬት ይናገራሉ ይጽፋሉ፡፡

የአረብ አብዮት አይነት ሰላማዊ የሕዝብ ተቃውሞና አምቢተኝነት ወያኔ አጥብቆ የሚፈራው፣ ተቀዋሚው ቢሆን የሚሻው፣ የኢትዮጵ ሕዝብ ሊያደርገው የማይችለው ነው፡፡ ሁሉም የየራሳቸው ምክንያት አላቸው፡፡ ወያኔ በሕዝብ አለመወደዱን ማወቁ፣ ለሥልጣኑ መስጋቱና ፍርሀቱ ሲሆን ፤ተቀዋሚው ለውጥ መሻቱ፣ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓትን መናፈቁ ነው፡፡ ሕዝቡ የማያደርገው ደግሞ ከጥንት እስከ ዛሬ የኖረበት ወግ ልማዱ ስላልሆነ፣ ትናንት ንጉሶች በቅርቡ ደግሞ አብዮተኞች ሥልጣን ሲነጣጠቁ ያየው በጠብ-መንጃ እንጂ በሰልፍ ስላልሆነ፣ በውርስ የተቀበለውም ሆነ በልማድ ያዳበረው ባለመሆኑ ነው፡፡

እናም አደባባይ አለመውጣቱ ሆ ብሎ ለአመጽ አለመነሳቱ ፈጽሞ ፍርሀት አይደለም፡፡ የዝምታውን ምንነትና እንዴትነት መረዳት፣ ከዝምታው በስተጀርባ ያለውን ድምጽ መስማት አለመቻል እንጂ ከሕዝቡ ዝምታ በስተጀርባ ታላቅ የሆነ ድምጽ አለ፡፡ ይህን የተረዱት እምየ ምንይልክ ናቸው፡፡ መንግሥታቸው የግብር ጭማሪ አድርጎ ባለሙሎቻቸውን ህዝቡ ምን አለ በማለት ይጠይቃሉ፣ደስተኛ አይደለም እያጉረመረመ ነው ይሉዋቸዋል፣ ቆይት ብሎ ደግሞ ሌላ የግብር ጭማሪ ይደረግና ህዝቡ ምን አለ ብለው ይጠይቃሉ እያማረረ እያጉረመረመ ነው ይሉዋቸዋል፤ ለሶስተኛ ግዜ ጭማሪ ተደርጎ ህዝቡ ምን አለ በማለት ሲጠይቁ አሁንስ ለምዶታል ምንም አላለ ሲሉዋቸው ይህኔ ነው መፍራት ማለታቸው እየተነገረ ከእኛ ደርሷል፡፡ አዎ ምንይልክ ከህዝብ ዝምታ ጀርባ ያለን ታላቅ ድምጽ ለማዳመጥ የቻሉ መሪ ስለነበሩ ነው ህዝቡ   እምየ ያላቸው፡፡

ከምርጫ 97 በኋላ ድምጻቸውም ብዕራቸውም የጠፋው ፕ/ር መድህኔ ታደሰ በ1996 ዓም መጨረሻ አካባቢ ከጦቢያ መጽሄት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ የኢትዮጵውያንን ዝምታ ምንነትና አንዴትነት አንዲህ በማለት ነበር የገለጹት፡፡ “የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲሁ በአጉራ ዘለልነት በአመጽና ቁጣ ገንፍሎ ወደ አደባባይ የሚወጣ አይደለም በታሪኩ ካየነው ማለት ነው፡፡ የውጪ ወራሪን ለመመከት ይሰለፋል አንድ ጉዳይ ነው፡፡ በውስጥ ፖለቲካ ተሳትፎ ግን ከታሪኩና ከንቃተ ህሊና ጋር ብዙ ነገር ስለሚወስነው ይህን ያህል አይደለም፡፡ አንድ ኪሎ ግራም ስኳር ስለጨመረ ነው የሱዳን ሕዝብ መንግሥት የሚገለብጠው፡፡ የኛ ግን የተለየ ነው፡፡” ያሉት ፕ/ር መድህኔ የህዝቡ ዝምታ ወያኔ አንደሚለው አገዛዙ ተስማምቶት፣ ኑሮም ተመቸትቶ አንዳልሆነ ሌላው ወገን እንደሚለውም በፍርሀት ቆፈን ተይዞ አለመሆኑን ሲገልጹ “አንድ መታወቅ ያለበት ነገር አለ፡፡ ይሄ ሕዝብ የሚያስተዳድረውን መንግሥት በመቃወም፣ በመጋፈጥ ላይታወቅ ይችላል፡፡ ተስፋ ከቆረጠ ግን አልምጥ ነው፡፡ ስለዚህ ሕዝቡ አንድ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ መመለሻ የለውም፡፡ ለተቃውሞ ተሰልፎ ባታየውም ባለመሰለፉ ጭምር ብዙ መንግሥታት ወደ መጡበት ሄደዋል፡፡ ሕዝቡ ዝም ይላል ግን ዝምታው መታሰብ ያለበት ይመስለኛል”፡፡

በምርጫ 2002 ወያኔ 99.6 በመቶ አሸነፍኩ ባለ ማግስት ፕ/ር መስፍን ወልማሪያም ሥልጣን ባህልና አገዛዝ ፖለቲካና ምርጫ በሚል ርዕስ ለንባብ ባበቁት መጽኃፍ የኢትዮጵያውያንን ውሳኔ እንዲህ ነበር የገለጹት፡፡ “የኢትዮጵያ ህዝብ ያስተላለፈው መልእክት ሁለቱንም ገዥውንም ሆነ ተቀናቃኙን አንገት የሚያስደፋና የሚያሳፍር ነው፡፡ ተሰብስቦ ሳይመካከር ሳይወያይና ሳይከራከር ተግባብቶና ተስማምቶ አንድ አይነት መልእክት ማስተላለፉ በአንድ በኩል የሰለጠነ ሕዝብ መሆኑን የሚገልጽበት ሰላማዊ የሰላማዊ ትግሉ መንገድ ነው፤ በአንድ በኩል ደግሞ አማራጭ አንዳልቀረበለት ማሳየቱ ነው፡፡ ስለዚህ ሁለቱንም አንደ አማራጭ የቀረቡለትን አንደማይፈልጋቸው በሚያውቀው የሰምና ወርቅ ዘዴው አረጋገጠላቸው፤ ያሸነፈም አለሰሸነፈ የተሸነፈም አልተሸነፈ፣ ያሸነፈም አፈረ የተሸነፈም አፈረ፣ሁለቱም የሀፍረት ማቃቸውን ለብሰው ድሉ የኔ ነው የኔ ነው እያሉ ሲጓተቱ የኢትዮጵያ ሕዝብ ኩታውን አፍንጫው ላይ ጣል አድርጎ ይታዘባል፣ ቂል ያደረጉትን ፖለቲከኞች ነን ባዮች ቂልነት፣ አላዋቂ ያደረጉትን አላዋቂነት አንደ ዕቃ የቆጠሩትን ሰዎች እቃነት እያሰበ ጥርሱን ሳያሳይ ይስቃል፣አይ ሥልጣን! ስንት ጉድ አሳየን! እያለ ይታዘባል፡፡” (ገጽ 124)

ለነጻነት የሚደረገው ትግል አደረጃጀቱና ስልቱ የቱም ይሁን የቱ ይህን የህዝብ ሥነ ልቦና የተገነዘበና ተስማሚ መንገድ የተከተለ ከሆነ ብቻ ነው ለውጤት የሚበቃው፡፡

ወያኔ በየግዜው ከንፈርነስ ስብሰባ ግገማ እያለ የህዝብን ልብ ለማወቅ ሥነ ልቦናውን ለመረዳት ጥሯል፡፡ በተለይ በምርጫ 97 ማግስት ሕዝቡን እየሰበሰበ (በተለይ አዲስ አበባ) ምን በደልናችሁ በማለት ለመለማመጥም ለመጠጋጋትም ሞክሯል፡፡ ነገር ግን በሁለት ምክንያት ውጤታማ አልሆነም፡፡ አንድ ህዝቡ ወያኔን አምኖ የልቡን መሻት ባለመናገሩ፤ ሁለት ወያኔ የደደቢት ህልሙን እንጂ የህዝብን ፍላጎት የማዳመጥና መሻቱን እውን የማድረግ ተፈጥሮ የሌለው በመሆኑ፡፡

“እናውቃለን ብንናገር እናልቃለን” የሚለውን ብሂል እየተናገረ ዝምታን የሚመርጠው ህዝብ ፕ/ር መድህኔ እንደገለጹት በዝምታው መሸኘትን ያውቅበታል፡፡ እያሞገሰ መጣልን፣ አለእናንተ እያለ ማ አለና እያለ የደገፈ መስሎ ሲጥልም አይተናል፡፡ይህን ስነ ልቦናውን የሚያውቅለት ግን እስካሁን አላገኘም፡፡ የመጣው ሁሉ እሱ በሚሻው ሳይሆን እነርሱ በሚሉት ሊገዙት ይዳዳቸዋል፡፡ የግዞት ዘመናቸው ይጠርም ይብዛ አንጂ ኋላ ግን በቅሌት ያወርዳቸዋል፤ ከህዝብ ፍላጎት በታቃራኒ የሚነጉዱ አገዛዛቸውን ማስተካከል ቀርቶ አወራረዳቸውን ማሳመር አይችሉም፡፡ ወያኔ በ1997 ምርጫ ሥልጣን ማስረከብ ቢችል ኖሮ በጫካም ሆነ በቤተ መንግሥት ቆይታው የፈጸመው እኩይ ድርጊት ሁሉ በተሰረየለት ነበር፡፡

የህዝቡ ሥነ ልቦና በሀገር ደረጃም አንድ ሊሆን እንደማይችል ማወቅም ያስፈልጋል፡፡ አንዳንድ ቦታ በዞንም ደረጃ የተለያየ የሚሆንበት አለ፡፡ ይህን ማወቅ ተስማሚ ስልት ለመንደፍ ጠቃሚ ነው፡፡ በዚህ ረገድ አንድ ተጨባጭ ማስረጃ ላቅርብና ልሰናበት፡፡

በምርጫ 97 የምሥራቅ ጎጃም አርሶ አደር ግንቦት ሰባትን(የድምጽ መስጫውን እለት)ምን ያስጠብቀናል፣ እኛ የወያኔ አገዛዝ በቃ ብለናል፤አሁኑን እንገላገል ወዘተ በማለት ምሬቱን ለውጥ መሻቱን በአደባባይ ካድሬው ባለሥልጣኑ ሁሉ ባለበት ይናገር ነበር፡፡ በአንጻሩ የምዕራብ ጎጃም ሰው በየግልም ሆነ በስብሰባ ለካድሬውና ለባለሥልጣናቱ አሁን ከእናነተ ሌላ ምን የሚመረጥ አለ ብላችሁ ነው የምትደክሙ፣ በማለት ሲያረጋጋቸውና እነርሱን እንደሚመርጥ ሲያረጋግጥላቸው ሰነበተ፡፡ በመጨረሻ ግን ከምስራቅ ጎጃም ከማርቆስ ከተማ ብቻ የቅንጅት ዕጩ ሲያሸንፍ በሙሉ ወያኔ ወሰደው፤ ምእራብ ጎጃም ደግሞ አንድ ወ/ሮ ሽታየ (የዕድሜ ልክ ምክትል አፈ ጉባኤ) ስታሸንፍ ሌላውን በመሉ የቅንጅት ዕጩዎች አሸነፉ፡፡ ይህ እንዴት ለምንና በምን ምክንያት ሊሆን አንደቻለ ጠለቅ ብሎ ማጤን የህዝቡን ሥነ ልቦና በማወቅ ትግሉን በድል ለማጠናቀቅም ሆነ ከድል በኋላ ዴሞክራሲያዊት ሀገር ለመመስረትና የህዝብን መሻት እውን የሚያደርግ አስተዳደር ለመመስረት ወሳኝ ይመስለኛል፡፡

አዎ ሊያዳምጠው ለቻለ ከህዝቡ ዝምታ በስተጀርባ ፍርሀት ሳይሆን ታላቅ መልእክት ያለው ድምጽ አለ፡፡

ይገረም አለሙ

abutam2006@gmail.com


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule