• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሻዕቢያ ህወሃትን አስጠነቀቀ

September 8, 2015 09:13 am by Editor 1 Comment

ቀደም ሲል የአባትና ልጅ “አፈጣጠርና ግንኙነት” የነበራቸው ወዳጆች ሻዕቢያና ወያኔ ያልተጠናቀቀውን የባድመን ጦርነት ካካሄዱ በኋላ ለዳግም ግጥሚያ ዝግጅት እያደረጉ ነው። “የጦርነቱ ሁኔታ” ያሳሰበው ሻዕቢያ በማስታወቂያ መ/ቤቱ በኩል ለህወሃት ማጠንቀቂያ ሰጥቷል። ከጥቂት ሳምንታት በፊት ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በዘገበው መሠረት መግለጫው ህወሃት ኤርትራን እንዲወጋ የአሜሪካንን ይሁንታ አግኝቷል ብሏል።

የፈረንጅ የቀን አቆጣጠር የሚከተለው ሻዕቢያ በማስታወቂያ መ/ቤቱ በኩል 4 September 2015 ያወጣው መረጃ እንደጠቆመው ህወሃት የተለመደውን የጦርነት አታሞ እየመታና ሳንጃ እየሳለ እንደሆነ ጠቁሟል። የህወሃት አገዛዝ “ሌሎች ክፍሎች ከኤርትራ ጋር እንዳይወግኑ ትንኮሳ እያደረገ” መሆኑን የጠቆመው መግለጫ ወያኔ በኤርትራ ጦርነት ማካሄድ እንዲችል ከአሜሪካ ይሁንታ ማግኘቱን በገሃድ እየተናገረ እንደሚገኝ ጠቅሷል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ከአራት ሳምንታት በፊት “ኢህአዴግ በኤርትራ አራት አቅጣጫዎች ጥቃት ሊሰነዝር አስቧል፤ አሜሪካ ሃሳቡ ቀርቦላታል ተብሏል” በሚል ርዕስ ባስነበበው ዜና ላይ እንዲህ ብሎ ነበር። “አሜሪካ ኢህአዴግ “አሸባሪ” ብሎ የሚፈርጃቸውን በሙሉ በሽብርተኛነት በመፈረጅ የመን የተጫወተችውን አይነት ሚና እንድትደግም ተጠይቃለች። … አሜሪካ የቀረበላትን ጥያቄዎች ስለመቀበሏ ያልጠቀሱት የመረጃው ባለቤቶች፣ ኤርትራ ውስጥ መተራመስ ሳይፈጠርና ክልሉና ቀጣናው ሳይናጋ ጥንቃቄ የተሞላበት ርምጃ ቢወሰድ አሜሪካ ተቃውሞ እንደማይኖራት ማረጋገጫ መስጠቷን አመልክተዋል። ይህ አቋም ኦባማ አዲስ አበባ ከመሄዳቸው በፊት በተለያዩ ደረጃዎች ተመክሮበት ከስምምነት የተደረሰበት ስለመሆኑም ገልጸዋል።”

ሻዕቢያ በመግለጫው ይህንን ቢልም በኢትዮጵያ በኩል ጦሩን ከአንድ ስፍራ የማንቀሳቀስ ሂደት እየተደረገ እንደሆነ ይታያል። ለዚህም የሚሰጠው ምላሽ ቀለል ያለ ብወዛ እንደሆነ ቢነገርም ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ለየት ባለ መልኩ በአማራው ክልል የሠራዊቱ ቁጥር እየጨረ መምጣቱን ከሥፍራው የሚገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአንድ ዓመት በፊት የአሰብ ወደብ እንዲታደስና በአዲስ መልክ እንዲደራጅ መደረጉ ከተለያዩ ምንጮች ሲነገር የቆየ መሆኑ ይታወሳል። ከዚህ ጋር በተያያዘ በሰሞኑ የህወሃት “ጨዋታ” የአዲስ አበባውን አንጃ ይመራሉ የተባለላቸው አርከበ ዕቁባይ ከጥቂት ወራት በፊት የኤርትራንና አሰብን ጉዳይ በተመለከተ ሲናገሩ “በኤርትራም ሁኔታው መቀየሩ አይቀርም፤ አሁን ያለው ሁኔታ ለዘለዓለም ይኖራል ብለን አንገምትም። በእኔ ግምት በሚቀጥሉት አስር ዓመታት ውስጥ ለውጥ ይመጣል ባይ ነኝ። የኤርትራን ወደብ (አሰብን) እንጠቀማለን” ማለታቸውን የሚጠቅሱ አስተያየት ሰጪዎች በወያኔና በሻዕቢያ መካከል የሚወራው የጦርነት ዝግጅትና አታሞ “ድለቃ” ግራ የሚያጋባ እንደሆነ ይናገራሉ።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

የዛሬ ወር አካባቢ ጎልጉል ያተመውን ዜና ከዚህ በታች በድጋሚ አቅርበነዋል፡-

ኢህአዴግ በኤርትራ አራት አቅጣጫዎች ጥቃት ሊሰነዝር አስቧል

አሜሪካ ሃሳቡ ቀርቦላታል ተብሏል

four front map

ኢህአዴግ በአራት አቅጣጫዎች የጦር ጥቃት ለመሰንዘር ማሰቡ ተሰማ፡፡ ይኸው ሃሳብ ለአሜሪካ ቀርቦላታል፡፡

በቅርቡ የተጠናከረ እንቅስቃሴ የጀመረው የአርበኞች ግንቦት ፯ ኃይል በተደጋጋሚ በሚያወጣው መረጃ በተለያዩ ቦታዎች ጥቃት ማድረሱን በይፋ ቢገልጽም ኢህአዴግ ጥቃቱን በቀጥታ ለማስተባበል እስካሁን አልወደደም። ይሁን እንጂ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ “ህዝብ አስፈቅደን” ሲሉ ኤርትራን እንደሚወጉ ይፋ አድርገዋል። አብዛኞች እንደሚስማሙበት ዛቻው ግጭት ስለመኖሩ የሚያረጋግጥ ነው። በሌላው አንጻር ደግሞ ይህንን የሃይለማርያም ንግግር የኤርትራው ሹም በዓለምአቀፍ መድረክ ላይ የተለመደ የህወሃት/ኢህአዴግ ማስፈራሪያና ዛቻ በማለት አጣጥለውታል፡፡

የግጭቱን ደረጃና በኢህአዴግ ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን ኢሳት ይፋ ካደረገበት ጊዜ ጀምሮ ኤርትራን መውቀሰና ማስፈራራት የጀመረው ኢህአዴግ፣ ቀጣናው ሊተራመስ እንደሚችል ስጋቱን ገልጾ ኤርትራን ለመደብደብ የሚያስችለውን ፈቃድ ስለማግኘቱ ጎልጉል መረጃ ደርሶታል። በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት (ስቴት ዲፓርትመንት) አራተኛዋ ሹም ዊንዲ ሼርማን ግንቦት ፯ን በስም በመጥቀስ በተቃወሙ ማግስት የባለሥልጣኗን የድጋፍ ቃል አስመልክቶ ቴድሮስ አድሃኖም በኢህአዴግ በኩል ያለውን ውለታ ሲናገሩ “ለምንከፍለው ዋጋ መጠን ተመጣጣኝ ክፍያ ነው” ሲሉ ውስጡ በርካታ የፖለቲካ “ጥሬ ሃብት” የሞላበት አስተያየት ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ሰጥተው ነበር።

የጎልጉል ታማኝ የመረጃ ምንጭ እንዳሉት ፕሬዚዳንት ኦባማ አዲስ አበባ በነበሩበት ወቅት የህወሃት ሰዎች ይህንኑ ጉዳይ በዋናነት አንስተው ነበር። ኢህአዴግ በሶማሊያ እያበረከተ ላለው ተግባር መሰናክል ተደርጎ የቀረበው የኤርትራ ተቃዋሚዎችን የመርዳት ጉዳይ እልባት እንዲበጅለት አሜሪካ ድጋፍ እንድትሰጥ የጠየቀው ኢህአዴግ፣ አሜሪካ ያሉ የከፍተኛ ተቃዋሚ አመራሮች ገደብ እንዲጣልባቸው ተማጽኗል። አሜሪካ ኢህአዴግ “አሸባሪ” ብሎ የሚፈርጃቸውን በሙሉ በሽብርተኛነት በመፈረጅ የመን የተጫወተችውን አይነት ሚና እንድትደግም ተጠይቃለች። ጥያቄው የቅዠትም ሆነ የምር፣ የግንቦት ፯ አመራሮች ነቅለው አስመራ መግባታቸው ጥያቄውን ዋጋ ቢስ አድርጎታል የሚሉ አሉ።

አሜሪካ የቀረበላትን ጥያቄዎች ስለመቀበሏ ያልጠቀሱት የመረጃው ባለቤቶች፣ ኤርትራ ውስጥ መተራመስ ሳይፈጠርና ክልሉና ቀጣናው ሳይናጋ ጥንቃቄ የተሞላበት ርምጃ ቢወሰድ አሜሪካ ተቃውሞ እንደማይኖራት ማረጋገጫ መስጠቷን አመልክተዋል። ይህ አቋም ኦባማ አዲስ አበባ ከመሄዳቸው በፊት በተለያዩ ደረጃዎች ተመክሮበት ከስምምነት የተደረሰበት ስለመሆኑም ገልጸዋል። ከዚህ አንጻር አቶ ስብሃት ነጋ “ከኤርትራ ጋር የሚካሄድ ውጊያ ጥንቃቄ ይጠይቃል” ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል።

በዚሁ መነሻ ኢህአዴግ በጎንደር፣ በሱዳን ድንበር፣ በአፋርና በትግራይ የተለያዩ ግንባሮች ድንገተኛ ማጥቃት ለመሰንዘር በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ተጠቁሟል። ወቅቱ የዝናብ መሆኑ እንዳለ ሆኖ፣ ለዚሁ ጥቃት ሠራዊቱ የሚወጋው “ተቃዋሚ የሆኑ የራሱን ወገኖች ሳይሆን ሻእቢያን ነው” በሚል የማነቃቂያ ስራ እየተሰራ እንደሆነ የመረጃው ሰዎች ተናግረዋል። በድጋሚ የመሥራቱ ጉዳይ ገና ባይታወቅም ይህ አካሄድ በባድመ እንደተደረገው የወኔ ማነቃቂያ እና የውጊያ ሞራል ማነሳሻ ለማድረግ ታስቦ በጥናት የተደረገ ለመሆኑ የመረጃው አቀባዮች ያስረዳሉ፡፡ አያይዘውም “ጦርነቱ ኢህአዴግ ካሰበው ውጪ ባንድ በኩል ከተሰበረ በጦሩ ውስጥ የሚገኙ የሌሎች ኅብረተሰብ ክፍል አባላት የሆኑ ወታደሮች ሊከዱና የተቃዋሚ ኃይሎችን ሊቀላቀሉ ይችላሉ” የሚል ስጋት ስለመኖሩ ሪፖርት መቅረቡን ይጠቅሳሉ።

በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ ያለው ሚዛን ያልጠበቀ የኃላፊነት ደረጃና የህወሃት አባላት ያላቸው የተጋነነ የበላይነት በመሃል አገር ከሚፈጸመው ረገጣ ጋር ተዳምሮ የተከማቸው ቅሬታ ሊፈነዳ ይችላል የሚል ጥርጣሬ እንዳለም እነዚሁ ክፍሎች ያስረዳሉ።

ኢህአዴግ የትጥቅ ትግል አውጀው ኤርትራ ከመሸጉና መሣሪያ አንግበው ትግል እያደረጉ መሆናቸውን ይፋ ካደረጉ ግንባሮች ሁሉ በድርጅታዊ አቅሙ ከፍተኛ የሚባለውን (ደሚት/ትህዴን) የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄን እስካሁን በሽብርተኛነት አለመፈረጁ ይታወቃል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tsionawi @ ETK says

    September 9, 2015 02:05 am at 2:05 am

    This is a true evidence that HEWEHAT and by extension the US obama Administration has
    been on the wrong calculation that eventually hit a dead end ” NOT BEYOND THIS LINE”
    sign. Many genuine Ethiopian and Eritrean Scholars and independent political Analysits have
    informed and warned of the dangers of this erratic calculation of postponing or putting away
    the inevitable or issue that needed to be dealt with by HEWEHAT before further stride can be
    made. Yet what HEWEHAT chose to do is to further complicate the already erratic calculations
    and fully undermine EPRDF no matter what the outcome wold be for Ethiopia. HEWEHAT’s short
    sighted myopic and erratic approach to the Ethiopian problem only created a bottle neck to further deteriorating situation at the expence of the whole country for organization’s benefit.
    Not only undermining EPRDF’s political values and assets AND making erratic and zero sum
    calculations BUT ALSO stagnancy and unable to stride with the already developing Ethiopian
    political transforamtion and culture also put HEWEHAT at odds with time and space puting it
    in a corner that it will not be able to continue further but die and leave the scene for good.
    These situation was eloquently told by many schlars who follow the Ethiopian political situation
    and its transformation and developments since the 1990’s. But unfortunately due to the obstinacy of HEWEHAT and its arrogant and un illuminated political behaviour and culture it
    had fallen on deaf ears only to haunt it as nightmare by reapearing time and again.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule