• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኤርትራ ጉዳይ

September 4, 2015 10:07 pm by Editor Leave a Comment

ለብዙ ኢትዮጵያዊያን፤ የኤርትራ ከኢትዮጵያ መገንጠልና የአገነጣጠሏ ሁኔታ፤ የውስጥ አካላችንን ያኔም፣ አሁንም እያንጠረጠረው ነው። በርግጥ በየኪሳችን ያለ የየግል ንብረት ስለተነጠቀብን አይደለም። በኤርትራ መገንጠል የቀረብን የግል ጥቅም ስለነበረም አይደለም። የሀገር ጉዳይ፤ ከንብረት፣ ከአባትና እናት፣ ከኑሮ የበለጠ ክብር የምንሠጠው ነው። በወቅቱ የቅርብ ጓደኛዬ የነበረ ኤርትራዊ፤ በኤርትራ መገንጠል ፍንደቃው ጊዜ አልሠጥህ ብሎት፤ መኖሬንም ረስቶ፤ ለሳምንታት ከወገኖቹ ጋር ሲጨፍር ከረመ። በመጨረሻም ቀን ቀንን እየወለደ፤ ሳንገናኝ ብዙ ጊዜ አለፈ። መራራቅ መራራቅን ነውና የሚያስከትለው፤ በየጎጣችን ተሸጉጠን፤ በመካከላችን የነበረው ጓደኝነት፤ ጊዜን መቀራረብ አላድሰው አለና ጠፋ። በርግጥ እኔም መላዕክ አልነበርኩም። ልክ ያለሁበት ቤት እንደተቃጠለ፤ በግል ሰው እንደበደለኝ፤ ብሽቀት ሰውነቴን ወሮት፤ እልህ ዓይኖቼን አውሯቸው፤ ንዴቴን የማሳርፍበት አጥቼ፤ መለስ ዜናዊንና ኢሳያስ አፈወርቂን አግኝቼ አንቄ ልገድላቸው ተመኝቼ ነበር። በዚያ ወቅት፤ ኢትዮጵያ ብቻ መላ ሰውነቴን ወራው፤ የግል ጓደኝነት ሆነ የግል የሚባል ነገር ቦታ አልነበረውም። እናም የኤርትራ መገንጠል ልቤን ስለቦረቦረው፤ ከያዝኩት ሰውነት የቀረበ ስላልነበረኝ፤ ለምንም ጉዳይ ቦታ አልሠጠሁም ነበር። ምግቤንም እንዴት እንደበላሁት፣ በውቅቱ ሥራዬንም እንዴት እንደሠራሁ፤ የቤት ኪራዬን እንዴት እንደከፈልኩ ማሰቡ ይቸግረኛል። እናም ለኤርትራዊው ጓደኛዬ አሳቢ ነበርኩ ብዬ አልዋሽም።

በቅርብ ጊዜ አንድ ኢሜል ደረስኝ። የላኪውን የኢሜል አድራሻ ስላልለየሁት፤ ወደ ቆሻሻ ማጠራቀሚያው ልልከው ምንም አልቀረኝም ነበር። ፈታሻ እንከን አጽጂ መርማሪዬ ንጹህ ነው ሲለኝ፤ ከፈትኩት። የቀድሞ ትዝታውን ጠቃቅሶና እኔ በየድረገፆች የማወጣቸውን ጽሑፎች እንደሚመለከታቸው ገልጾ፤ መገናኘት እንደሚፈልግ የጻፈልኝ፤ የድሮው ኤርትራዊ ጓደኛዬ ነበር። ተገናኝንና ብዙ ተጫወትን። እንዳስቀየመኝ እያወቅሁ፤ ለምን እሺ ብዬ እንዳገኘሁት ጠየቀኝ። እኔም እንኳን እሱን፤ በዓለም ዙሪያ እዚህ አሜሪካ መጥቶ ከሚኖር ሰው ጋር ሁሉ ወዳጅነት እንደማደርግና፤ ለኔ በስደት ሀገር፤ የፖለቲካ ጉዳይ እንጂ የሰው ጠላት እንደሌለኝ ገልጨለት፤ ጭውውታችን ቀጠልን። ብዙ የምንስማማበት ጉዳይ ነበረን። የሁለታችንም ፍላጎት አልተሟሉም። ሁለታችንም የኢሳያስ አፈወርቂና የመለስ ዜናዊ ጠላቶች ነን። ኤርትራ ከሕልም ቅዠት ወጥታ አንዲት እርምጃ ወደፊት ካለመሄዷ አልፋ፤ ወደኋላ ተጉዛለች። ኢትዮጵያም በሰመመን አለች የለችም የምትባልበት እንጥልጥል ላይ ሆናለች። ሁለታችንም ልባችን ተሰቅሏል። እናም በመካከላችን የነበረው አራራቂ ፖለቲካ፤ ገደል ገብቷል። እኒህ ሁለት መሪዎች፣ እኒህ ሁለት አጥፊ ድርጅቶች፣ እኒህ ሁለት አፍራሽ የፖለቲካ አመለካከቶች ያደረሱትን ጉዳት በአንድ መነፅር ማየት ቻልን። ሁለታችን፤ እኒህ መናጢ እርጉሞች አልን።

በጭፍን ወደፊት መሄድ፤ መደናበር ነው። አዎ! ኤርትራ ሀገር ተብላ የራሷ ስንደቅ ዓላማና የራሷ አምባሳደሮች አሏት። ደንበሯም ከሱዳንና ከጅቡቲ ጋር የተከለለ ነው። በርግጥ ከ”ጎረቤቷ” ከኢትዮጵያ ጋር ያለው ግልጽ አይደለም። እንግዲህ፤ ይሄ ጉዳይ ለያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ምን ማለት ነው? ኤርትራ በአሰብ ወደብ ዙሪያና በባህር በርነቷ ብቻ የምትታይ ናት ወይ? የዓለም ፖለቲካስ በዚህ ረገድ ያለው እምነት ምንድን ነው? የዓለም ፖለቲካስ በዚህ ረገድ በተግባር ምን ፈጽሟል? ዓለም ዛሬ የደነገገውን ነገ የሚያፈርስበት ሀቅ አለ ወይ? በዚህ ላይ ነበር እኔና ኤርትራዊው የቀድሞ ጓደኛዬ፤ የዛሬው አዲሱ ትውውቄ የተነጋገርነው። የደረስንበትም ስምምነት እንዲህ ነበር።

መጀመሪያ በጊዜው የተደረገው የፍጥነት መገንጠል ትክክል እንዳልሆነ ተስማማን። ታዲያ እንግዲህ፤ ከዚህ የመነጨው ሁሉ ስህተት ነው፤ ማለት ነው። አፈጻጸሙም ሆነ ፍጻሜው ትክክል ያልሆነ ጉዳይ፤ ሄዶ ሄዶ ሊፈጥር የሚችለው፤ ያው ድንብርብር ነው። እናም ላሁኑ ላለንበት ሁኔታ ተጠያቂው፤ ወገንተኛው አምባገነን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባና ሕዝባዊ ኃይልታት ሓርነት ኤርትራ – ሸዓቢያ ናቸው። በነዚህ ድርጅቶች የሚመሩ መንግሥቶች፤ መፍትሔ ፍጹም ሊያመጡ አይችሉም። እንዲያውም እኒህ ሁለት ድርጅቶች የሕዝቡ ጠላቶች ናቸው። እናም መደምሰስ አለባቸው ነው። ቀጥሎ ደግሞ፤ ለማንኛውም ወደፊት ለሚቀርብ መፍትሔ፤ መጀመሪያ የተደረገውን በመመርመር፤ ስህተቱንና ጉድለቱን አጣርቶ ማውጣት አስፈላጊ ነው። አሁን በተግባር ላይ የዋለው የኤርትራ መገንጠል፤ ማንን ጠቀመ? ብለን ስናጤን፤ ሁለት እንዳሻቸው የሚያደርጉ አምባገነኖችን ከመፍጠር በቀር፤ በሕዝቡ የዕለት ተዕለት ኑሮም ሆነ የልማትና ሰላም መንገስ፤ ጉዳይ ቦታ አላገኘም። ስለዚህ፤ የምክክርና የመፍትሔ አፈላላጊ ጉዳይ ሆኖ አግኝተነዋል።

ከዚህ በተረፈ አሁን በጎን ሁሉም እንዳለ፤ እንዴት ሁለቱ ሀገሮች በሰላም ይኑሩ? እንዴት ልማትን ያስተባብሩ? እንዴት የአሰብን ጉዳይ ይወስኑ? እንዴት የየግል መሪዎቻቸውን ያጥፉ? እና የመሳሰሉት ውይይቶች፤ የአፍ ማልፊያና ጊዜ ማጥፊያ ከመሆን አያልፉም። ኤርትራዊያን ከመሪያቸውና ከመሪያቸው ፖለቲካ ነፃ ሆነው፤ ኢትዮጵያዊያንም ከመሪያችንና ከመሪያችን ፖለቲካ ነፃ ሆነን፤ ከሕዝቡ አንጻር ጉዳዩን መመልከት አለብን።

ምንልባት ስምምነት ላይ መድረስ ካስፈለገ፤ የስምምነቱ ማጥንጠኛ የሚሆነው፤ እኒህን ሁለት መሪዎችና እኩይ መሪ ድርጅቶች እንዴት እናጥፋ የሚለውን ለማስተናገድ መሆን አለበት። በርግጥም የኒህ የሕዝብ ጠላቶች መወገድ መሠረታዊ ስለሆነ፤ እነሱን ለማጥፋት መተባበሩ ግድ ነው። ከዚህ ውጪ ግን ሕዝብ ለሕዝብ የሚል ግንኙነት የወግ ነው። ሕዝብ ግንኙነት ሊመሠርት የሚችለው ነፃ ሲሆን ነው። ነፃ ባልሆነ ሕዝብ መካከል ግንኙነት ለፈጥእር አይችልም። ካለም በታጋዮቹ በኩል ነው። ከርህራሄ ቢሱ ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በማበር ወገንተኛ አምባገነኑን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ለመደምሰስ፤ ከወገነኛው አምባገነን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ጋር በማበር ርህራሄ ቢሱን ኢሳያስ አፈወርቂን ለመደምሰስ መነሳት፤ የእሬያ ታጥቦ ጭቃነት ነው። ምክንያቱም፤ ወገነተኛው አምባገነን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ለኤርትራዊያን፤ ርህራሄ ቢሱ ኢሳያስ እፈወርቂ ለኢትዮጵያዊያን፤ አያስቡማና! በርግጥ አኩርፈው ሌላ ቢቀባጥሩም፤ አንዳቸው ለሌላቸው ዘብ ሊቆሙ ይቻላሉ። መመሥረት ያለበት፤ በኤርትራዊያን ታጋዮችና በኢትዮጵያዊያን ታጋዮች መካከል ብቻ ነው።

በተጨማሪ ባሁኑ ሰዓት፤ በምንም መንገድ ቢሆን ሊከተል የሚችለው መፍትሔ፤ በሁለቱ መሪዎችም ሆነ በዓለም አቀፍ ተጽዕኖ፤ መሪዎችን የሚጠቅም እንጂ፤ ሕዝቡን የሚጠቅም ሊሆን አይችልም። ሕዝቡ የሚጠቀመው፤ አፋኝ መሪዎቹ ሲወገዱለትና በነፃ የራሱን ፍላጎት ለማሟላት መወሰን ሲችል ብቻ ነው።

አንዱዓለም ተፈራ – የእስከመቼ አዘጋጅ

eske.meche@yahoo.com

መስከረም ፩ ቀን፤ ፳፻፰ ዓመተ ምህረት


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule