አንዱ አንበሳ ነው. . . ወገኑ ሲነካ ዘራፍ ነው የሚለው። ሌላው ደግሞ ጅብ ነው. . . የሚበላ አግኝቶ ግዳይ የጣለ ዕለት፥ ወገኑን ሳይጠራ ጭራሹን አይነካት። የኔኛው ውሻ ነው ለያውም ተናካሽ፥ የራበው ወንድሙን ወገኑን አስለቃሽ። የሞተ አግኝቶ በልቶ ይጠግብና፥ ወገኖቹ ውሾች እንዳይበሉ ይልና፥ እዛው ጋር ይተኛል እያባረራቸው፥ ትንሽ እንዳይቀምሱ ሊከለክላቸው። ግን ቁራና ጭልፊት ከሰማይ የሆኑት፥ ምንም አይላቸው ስስቱን ሲበሉት። ----- (By Gemechu Merera) 23/11/2009 … [Read more...] about የኔኛው
Literature
ጽፈኪን
የማይጮኹት . . . በዓሉ ግርማን የበሉት ጅቦች
“ይህችን ውድ የሆነች ትንሽ ቁራሽ ሕይወት እንደ አብርሃም ቤት የለኝ፣ እንደ ሙሴ መቃብሬ ላይታወቅ፡፡ መኖር - መጻፍ - ሕይወትን በተስፋ ወደፊት እየኖርኩና ወደኋላም እያስተዋልኳት፡፡” በዓሉ ግርማ - ደራሲው እውቁን ጋዜጠኛና ደራሲ በዓሉ ግርማን በአጸደ ሕይወት ካጣነው፤ በዘንድሮው የካቲት 24 ቀን 2006 ዓ.ም. ሠላሳ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ ውድ ባለቤቱ ወይዘሮ አልማዝ አበራ በዘመነ ኢሕአዴግ ስለ ባለቤቷ ከቤት እንደወጣ መቅረት ጉዳይ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ቀርባ የጠቅላይ አቃቤ ሕግ ምስክርነቷን እንድትሰጥ ተደርጋ ነበር፡፡ ያንን የእሷን የፍርድ ቤት የምስክርነት ቃል የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን አቅርቦ ካስደመጠንም ሁለት አሠርታት ዓመታት እንደዋዛ ሊቆጠሩ ነው፡፡ ውድ ባለቤቱ ወ/ሮ አልማዝ ለከፍተኛው ፍርድ ቤት ያቀረበችውና እልክና ቁጭት የተመላበት የምስክርነት ቃሏ አንድምታ እንዲህ … [Read more...] about የማይጮኹት . . . በዓሉ ግርማን የበሉት ጅቦች
መርፌ
አንድ ቀን ተነስቶ፣ መርፌ ተቆጥቶ፣ መርፌ ተበሳጭቶ፣ አልሰጥም ያለ ቀን - ያንን ቀዳዳውን፣ ክር አንጀቴን በላኝ - እንጃለት መግቢያውን። … [Read more...] about መርፌ
እኚህ ሴት ማናቸው? – ፰
ከአዘጋጆቹ፤ባለፈው ሳምንት “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፯” በሚል ለቀረበው ምላሽ በድረገጻችን በመላክና በፌስቡክ ላይ በመለጠፍ የተሳተፋችሁትን በሙሉ እናመሰግናለን፡፡ በተለይ በግጥም ምላሻችሁን ለሰጣችሁ በሙሉ ከፍያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ የቅንብሩ አዘጋጅ ወለላዬ በቁጥር ሰባት ለቀረበው ጥያቄ ምላሻቸውን በሚከተለው መልኩ በግጥም አስፍረዋል፡፡ መልስ ማራቶን ማራቶን ማራቶን ልዕልቷ አበበና ማሞ ሆኑ ባለቤቷ ማራቶን ደንግጠሽ አቤን ብትቆጪ ዕድሉ የኛው ነው የትም አታመልጪ ብለው ያወደሱ - ሜክሲኮን ኦሎምፒክ የኳስ ስም ሲነሳ - የሚታውሱ ሰርክ ግጥም ያቀበሉ - ለብዙ ዘፋኞች ዝናን ያተረፉ - በስፖርት ዓለም ሰዎች አገር የሚሸበር - ድምጻቸው ሲሰማ እኚህ ሰው ነበሩ - ስለሞን ተሰማ፡፡ ለዚህ ሳምንት “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፰” ወለላዬ የሚከተለውን … [Read more...] about እኚህ ሴት ማናቸው? – ፰
ዛፎች
ከዛፎች መካከል ዛፎች ሲቆረጡ ዎዮው ላሽሟጠጡ፡ ዎዮው ላላገጡ፡ የተጨፈጨፉት የተቆረጡቱ፡ ለምሣር እጄታ ተገጥመው ሲመጡ። … [Read more...] about ዛፎች
እኚህ ሰው ማናቸው? – ፯
ከአዘጋጆቹ፤ባለፈው ሳምንት “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፮” በሚል ለቀረበው ምላሽ በድረገጻችን በመላክና በፌስቡክ ላይ በመለጠፍ የተሳተፋችሁትን በሙሉ እናመሰግናለን፡፡ በተለይ በግጥም ምላሻችሁን ለሰጣችሁ በሙሉ ከፍያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ በተለይ በዚህኛው በርካታዎች በመሳተፋችሁና በግጥም ምላሽ በመስጠት ዝግጅቱን ላሳመራችሁ ሁሉ በድጋሚ ምስጋናችን ይድረሳችሁ - ቀጥሉበት:: የቅንብሩ አዘጋጅ ወለላዬ በቁጥር ስድስት ለቀረበው ጥያቄ ምላሻቸውን በሚከተለው መልኩ በግጥም አስፍረዋል፡፡ መልስ በአፄ ሚኒሊክ - የአገዛዝ ዘመን ኤርትራ በሚገኝ - የስዊድን ሚሽን በኋላም ውጪ ሀገር - ብዙ የተማሩ በዕውቀታቸውም - ለሀገር የሰሩ በሹመት የቆዩ - ሆነው ነጋድራስ ታሪክ ያረሳቸው - እስከዛሬ ድረስ ገብረህይወት ባይከዳኝ - በሚል የጻፋችሁ ስህተት የለውም - ልክ ነው … [Read more...] about እኚህ ሰው ማናቸው? – ፯
የአፍታ እፍታዎች
ያስገረሙኝና ፈገግ ያሰኙኝ የማህበራዊ ሚዲያ ‹‹ጥቅሶች›› 1. ‹‹የድሃ ልጅ ስሙ ሀብታሙ ነው›› 2. ‹‹ሰውና ድፎ በትዕዛዝ እንደፋለን›› 3. ‹‹ቁንጅና ይኑርሽ እንጂ ፀባይ በዱላ ይመጣል›› 4. ‹‹የሴት ልጅ ግርዛትና ሚስድኮል ይቁም›› 5. ‹‹ኡፍ በማለት ትንፋሽ እንጂ ብሶት አይወጣም›› 6. ‹‹ለህይወትህ ዋጋ፣ ለልጆችህ ዳቦ ስጥ!›› ሰፈር ውስጥ የሰማኋቸው አዲሶቹ የሸገር ልጆች ቃላት • ‹‹በጤ›› - በጣም ለማለት • ‹‹በኔ›› - በእናትህ ለማለት • ‹‹እሱ እኮ እምባ ነው›› - የቅርብ ተቆርቋሪ ነው ለማለት • ‹‹ጠበዘዝነው›› - በላነው ለማለት • ‹‹ዘጭ ብያለሁ›› - ጠግቤያለሁ ለማለት • ‹‹ኤም ጢ ›› - መስሚያዬ ጥጥ ነው/ አልሰማህም ለማለት ታክሲ ላይ ያነበብኳቸው፡ 1. ‹‹ሰው ብቻ ነው የምንጭነው፤ በስህተት የገባ ካለ … [Read more...] about የአፍታ እፍታዎች
ቅኝ ግዛት!
ምነው በቀደም ለት እንቢልታ ሲነፋ ከበሮ ሲደለቅ፣ ከዘመናት ግዞት ነፃ የወጣንበት፣ ብለህኝ አልነበር አፍሪካ ነፃ ናት? "'አፍሪካ . . . ሀገራችን አፍሪካ የኛ ናት አፍሪካ አፍሪካ. . ." ተብሎ ሲዘመር የጥቁሮች ነፃነት? ታዲያ ዛሬ ለሊት፣. . . የሰማሁት ዋይታ ያዳመጥኩት ጩህት፣ ሲያከብሩ እዳትለኝ የበአሉን ማግስት? ዋሽተህኛል እንዴ . . . ? ትርጉሙን አዛብተህ? . . . ሆኖ እንዳይሆን ብቻ፣ ነፃ መሆን ማለት ካልሆኑ አቻ ላቻ ፣ ለወሬ ማድመቂያ ዳንኪራ መርገጫ፣ ነፃነት ነፃነት እያሉ ማፋጫ፣ ድቤ መደለቂያ በባዶ መንጫጫ ? እኔን ነፃ ያርገኝ. . . በዚች መሬታችን በምንኖርባት፣ የጥቁር ደም አጥንት በግፍ ባለቀባት፣ ነፃነት አግኝቶ ደምቆ `ሚኖርባት ? የሰላምን አየር ተንፍሶ `ሚድርባት ነጭ ነው ወይ ጥቁር . . . … [Read more...] about ቅኝ ግዛት!
እኚህ ሰው ማናቸው? – ፮
ከአዘጋጆቹ፤ባለፈው ሳምንት “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፭” በሚል ለቀረበው ምላሽ በድረገጻችን በመላክና በፌስቡክ ላይ በመለጠፍ የተሳተፋችሁትን በሙሉ እናመሰግናለን፡፡ በተለይ በግጥም ምላሻችሁን ለሰጣችሁ በሙሉ ከፍያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ የቅንብሩ አዘጋጅ ወለላዬ በቁጥር አምስት ለቀረበው ጥያቄ ምላሻቸውን በሚከተለው መልኩ በግጥም አስፍረዋል፡፡ መልስ ለሀገር ለወገን - ውለታ የሰራ ስሙ ለዘለዓለም - ይኖራል ሲጠራ ነገር ግን ታሪኩን - ያረገውን በጎ አንባቢው አለበት - መረዳት ፈልጎ እኛ ለማስታወስ - ይሄንን አድርገን ለማቅረብ ችለናል - መላኩ በያንን እኚህ ስመ ጥሩ - ኢትዮጵያዊ ዶክቶር ሙሉ እድሜአቸውን - ደክመዋል ለሀገር። ለዚህ ሳምንት “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፮” ወለላዬ የሚከተለውን አቅርበዋል፡፡ ምላሻችሁን በግጥም በመመለስ ለዝግጅቱ … [Read more...] about እኚህ ሰው ማናቸው? – ፮
የሎሬት ህመሙ ቢያመኝ
ይሞላ ብዪ ስኳትን፣ ህልሜ እልም እያለ ቢፈትነኝ ለህሊናየ አድር ብዪ ስማስን፣ ድካሙ ቢሸበርክኝ ተስፋ አልቆርጥም ባልኩ በተጋሁ፣ ህመሙ ቢደቁሰኝ ብላቴን ጌታ ታወሰኝ፣ ጸጋየ ህመሙ ዘልቆ ወጋኝ የጸጋየ ህመሙን ታመምኩ መላ ቅጡን አስጠፋኝ። ውስጤ ቢደማ ቢታወክ፣ የጸጋየ ሮሮ በአይነ ህሊናየ መጣብኝ የመጨረሻው እስትንፋስ ቃሉ፣ ሎሬት ህመሙ አመመኝ "እኔ ለእኔ ኑሬ አላውቅም " ብሎ ያለን የስንብት ጸጸት ቃሉን አዘከረኝ፣ ....... ........ ....... ......... ........ ...... የጸጋየ ጸጸት ... "የማይሰማ ወጨት ጥጄ - እፍ ስል የከሰመ ፍም፣ ውርዴም ይፈወሳል ብዬ - የሰው እከክ ስዘመዝም፣ በሰው ቁስል መቁሰል በቀር - እኔ ለኔ ኖሬ አላውቅም፡፡ የማይነጋ ህልም ሳልም - የዘመን ደዌ ሳስታምም፣ የማያድግ ችግኝ … [Read more...] about የሎሬት ህመሙ ቢያመኝ










