
ከአዘጋጆቹ፤ባለፈው ጊዜ “እኚህ ሴት ማናቸው? – ፰” በሚል ለቀረበው ምላሽ በድረገጻችን በመላክና በፌስቡክ ላይ በመለጠፍ የተሳተፋችሁትን በሙሉ እናመሰግናለን፡፡ በተለይ በግጥም ምላሻችሁን ለሰጣችሁ በሙሉ ከፍያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ የቅንብሩ አዘጋጅ ወለላዬ በቁጥር ስምንት ለቀረበው ጥያቄ ምላሻቸውን በሚከተለው መልኩ በግጥም አስፍረዋል፡፡
መልስ
በብዙ ትያትር – የመድረክ ዝግጅት
ዝናን ያተረፉ – ቀርበው በመታየት
«የአዛውንቶች ክበብ» – በተለይ ሲነሳ
እስከዛሬ ድረስ – ያላጡ ሙገሳ
አስካለ አመንሸዋ – ማለት እኚህ ናቸው
ከእድሜው በረከት – አሁንም ይስጣቸው።
ለዚህ ሳምንት “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፱” ወለላዬ የሚከተለውን አቅርበዋል፡፡ ምላሻችሁን በግጥም በመመለስ ለዝግጅቱ ውበት እንድትሰጡ ለማደፋፈር እንወዳለን፡፡ የዛሬ ሳምንት መልሱን በግጥም እናቀርባለን፡፡
ሥራቸው ካልቀረ – ወደፊት አስታዋሽ
ብዙዎች ሲሞቱ – ይረሳሉ ጭራሽ
አንዳንዶች ግን እንዲህ – በሙያቸው ብቃት
አይቀሩም ጨርሶ – ተሸፍነው በሞት
ከነዛ መካከል እኚህ – አንዱ ናቸው
በሉ ተጠየቁ – ንገሩኝ ማናቸው?
Wolelaye and Golgul,
I like to thank you much for this Section “Egnih Sew Man Nachew”. It is entertaining and teaching us (people like me) at the same time. I admit that I know better about many “Ferenjoch” History than my own people. This is same as “Hagerihn Iwok” and I thank you a lot for it. Please keep it up.
የቀድሞው የክብር ዘበኛ ጦር ጀነራል መንግስቱ ነዋይ ይባላሉ በስራው በተግባር የነበረ ብርቱ ዊስኪ ሻፓኝ ክትፎና ጮማ ይቅርብኝ በማለት ለህዝቡ የደማ ገርማሜ ወንድሙ ከጎኖ አቁሞ በደል እንዲቀር አነሳ ተቃውሞ የታህሳስ ግርግር ሲባል ተሰይሞ ሚኒስትር መሳፍንት ለቃቅሞ የሃገር ጉድፎች ጨረሰው አጋድሞ ይባል የነበረ በጊዜው በስውቅቱ መንግስት ግልበጣ ቅስቃሽ መሰረቱ እኝህ ናቸው ጀነራል መንግስቱ።
He is Esatu Tesema.
ሰሞኑን ባገሬ የተሰማው ዜና
አስደንጋጭ ነበር የሚነሳ ጤና
የዛ ድንጋጤ ሳይበርድለኝ ገና
እኚ ሰው ማናቸው ገፅ ገባሁና
ትኩር ብዬ ሳይ ፎቶ በጥሞና
ወለላዬን ባላውቅ ጎልጉለን ባላነብ
ኢትዮጵያዊነትን እንድናውቅ በደንብ
የማልጠራጠር ይሕን አስመልክቶ
ትንሽ ግራ ገባኝ ሳየው ይሕን ፎቶ
ደሞ በየት በኩል እንዴትስ አድርጎ
ምን ጥሩ ሰራና ተጠቃሽ በበጎ
ፎቶው የሚለጠፍ ለሁሉም እንዲታይ
የወያኔ አለቃ አቦይ አባይ ፀሀይ
ብዬ ለመናደድ እፎይታም ሳላገኝ
ከዛ ከጨፍጋጋ እንቅልፌ ባነንኩኝ
እኚህ ኢትዮጵያዊ ለሐገር አሳቢ
አባይ ፀህይ ሌላ የራቀው ውቃቢ
እንዴትስ ብሎ ነው መመሳሰላቸው
አራምባና ቆቦ ለሐገር ሥራቸው
ብሎ ለሚከስኝ ለሚጠይቅ ካሣ
ብድር ከፋይ ያርገኝ ከእንቅልፌ ስነሣ›
ፈጣኑ ግራኝ>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>>
አሁን ገባኝ
ሁሌን እመኛለሁ ትጋትን ጭምሬ>
እንደምን አመሹ ወዳጄ መምሬ
I agree with Amenen.
He is Esatu Tesema