
ከአዘጋጆቹ፤ባለፈው ሳምንት “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፭” በሚል ለቀረበው ምላሽ በድረገጻችን በመላክና በፌስቡክ ላይ በመለጠፍ የተሳተፋችሁትን በሙሉ እናመሰግናለን፡፡ በተለይ በግጥም ምላሻችሁን ለሰጣችሁ በሙሉ ከፍያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ የቅንብሩ አዘጋጅ ወለላዬ በቁጥር አምስት ለቀረበው ጥያቄ ምላሻቸውን በሚከተለው መልኩ በግጥም አስፍረዋል፡፡
መልስ
ስሙ ለዘለዓለም – ይኖራል ሲጠራ
ነገር ግን ታሪኩን – ያረገውን በጎ
አንባቢው አለበት – መረዳት ፈልጎ
እኛ ለማስታወስ – ይሄንን አድርገን
ለማቅረብ ችለናል – መላኩ በያንን
እኚህ ስመ ጥሩ – ኢትዮጵያዊ ዶክቶር
ሙሉ እድሜአቸውን – ደክመዋል ለሀገር።
ለዚህ ሳምንት “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፮” ወለላዬ የሚከተለውን አቅርበዋል፡፡ ምላሻችሁን በግጥም በመመለስ ለዝግጅቱ ውበት እንድትሰጡ ለማደፋፈር እንወዳለን፡፡ የዛሬ ሳምንት መልሱን በግጥም እናቀርባለን፡፡
እናት ሀገራችን – ብዙዎች ነበሯት
የታሪክ ማህደር – ፋይል ሳገላብጥ
እኚህን ታላቅ ስው – አየኋቸው ከውስጥ
ላስታውስ ነው እንጂ – መቼም አታጧቸው
በሉ ተናገሩ – እኚህ ሰው ማናቸው?
zeray deses ?
DR.Melaku Beyan : He was organizing pro Ethiopian forces in the USA representing Ethiopia during Ethio-Italian war as Haile Selassie special representative
ነጋድራስ ናቸው ገብረህይወት ባይከዳኝ
በነጋ በጠባ ማናቸው እያልከኝ
ፈተና እያመጣህ በቃ አትጨቅጭቀኝ
እኔጃ ነው መልሴ እንዴት ላስታውሳቸው
የታሪክ መድብል ውስጥ የለም አልበማቸው
የአገሬ ሰዎች በበጎ ስራቸዉ ሀገር ያወቃቸዉ
እረ ብዙ ናቸዉ
ሁሉንም ባንድ ጊዜ ቆጥረን ባንዘልቃቸዉ
ቀስ በቀስ እያልነ እስኪ እንዘክራቸዉ
የሀገሬ ታሪክ ትልቁ መፀሀፍ ከከታተባቸዉ
ገ/ህይወት ባይከዳኝ ያነን ስመ ጥሩዉ
ይመስላል ፎቷቸዉ
እንደው በግርድፉ ፎቶውን ሲያሰሉት
የቆየ ይመሥላል ዘመን ያለፈበት
ደግሞ ሲያስተውሉ ግለስቡን ዘልቆ
አለባበሱንም ካዩ ተጠንቅቆ
ወጣት ከመሆኑም ዘና ከማለቱ
ኮፍያው ከራሱ ከረባት ባንገቱ
ሁሉንም አሥማምቶ የተነሳው ፎቶ
ዘመነኛነቱን ያሳያል አጉልቶ
በውጭ አገር ኖረው ያውቃሉ ለማለት
ነበር ሙከራዬ ይሕ ሁሉ መዋተት
ከዚህ በተረፈ የምስማማው እኔ
የመገምት አቅም ባይኖረኝም ወኔ
ቢሆኑ ደስ ይላል በያን ወመላኩ
እንደተጠቀሰው ከላይ በመድረኩ
አወይ የኔ ነገር አወይ የኔ ሥራ
ግለሰብ ለይቼ ስሙን ሳላጣራ
ካቀያየርኩዋቸው አንዱን ወደ ሌላ
ማሥተካከሉ ላይ እንዲፈጠር መላ
ወለላዬ ወይም የጎልጉል አዘጋጅ
ማንንም ሳልጠይቅ ሳላመጣ አማላጅ
ይስተካከልልኝ ጥያቄው ከመልሱ
እንዲሁም ይታገድ ይቆይልኝ ሒሱ
ወዳጃችን Bombu ምንም አያስቡ
በውል ተስተውሏ መልሱና ሃሳቡ
የመጀመሪያውን መልስ ተገቢው ቦታ ላይ አትመነዋል፡፡ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡ ሁለተኛ በማስተካከያነት የላኩትን ውብ ግጥም ላለማጥፋት ብለን ከ“ስህተቱ” ጋር እዚሁ ትተነዋል፡፡
አርታኢ
ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ
አላዉቀውም እንጂ ባውቀውማ ኖሮ
እነግርህ ነበረ ከቅድም ዠምሮ
መገመቱንማ ልገምትላቹ
የግምት የግምት ፈስም ዳለቻ ነው አትብሉኝ ባካቹ
እኝህ ትልቅ አባት ታሪክ ያስቀመጡ
ዛሬ ለትዝታ በፌስቡክ የመጡ
የዋዛ አደለም የፀግሽ ግምቱ
ገ/ሂወት ባይከዳኝ የጥንት የጠዋቱ
gebrehiwot bykedagne nachew ”yehizib ena ye mengist astedader” yemilewun metshaf yetsafut