• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እኚህ ሰው ማናቸው? – ፮

June 29, 2014 05:25 am by Editor 10 Comments

ከአዘጋጆቹ፤ባለፈው ሳምንት “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፭” በሚል ለቀረበው ምላሽ በድረገጻችን በመላክና በፌስቡክ ላይ በመለጠፍ የተሳተፋችሁትን በሙሉ እናመሰግናለን፡፡ በተለይ በግጥም ምላሻችሁን ለሰጣችሁ በሙሉ ከፍያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ የቅንብሩ አዘጋጅ ወለላዬ በቁጥር አምስት ለቀረበው ጥያቄ ምላሻቸውን በሚከተለው መልኩ በግጥም አስፍረዋል፡፡

መልስ

ለሀገር ለወገን – ውለታ የሰራwho-is-he-5

ስሙ ለዘለዓለም – ይኖራል ሲጠራ

ነገር ግን ታሪኩን – ያረገውን በጎ

አንባቢው አለበት – መረዳት ፈልጎ

እኛ ለማስታወስ – ይሄንን አድርገን

ለማቅረብ ችለናል – መላኩ በያንን

እኚህ ስመ ጥሩ – ኢትዮጵያዊ ዶክቶር

ሙሉ እድሜአቸውን – ደክመዋል ለሀገር።


ለዚህ ሳምንት “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፮” ወለላዬ የሚከተለውን አቅርበዋል፡፡ ምላሻችሁን በግጥም በመመለስ ለዝግጅቱ ውበት እንድትሰጡ ለማደፋፈር እንወዳለን፡፡ የዛሬ ሳምንት መልሱን በግጥም እናቀርባለን፡፡

ተጉዘው ባያልቁ – ተከታትለው በሞትwho-is-he-6

እናት ሀገራችን – ብዙዎች ነበሯት

የታሪክ ማህደር – ፋይል ሳገላብጥ

እኚህን ታላቅ ስው – አየኋቸው ከውስጥ

ላስታውስ ነው እንጂ – መቼም አታጧቸው

በሉ ተናገሩ – እኚህ ሰው ማናቸው?

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Who is This Person Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. senu says

    June 29, 2014 08:34 pm at 8:34 pm

    zeray deses ?

    Reply
    • Taddese Mammo says

      June 30, 2014 05:58 am at 5:58 am

      DR.Melaku Beyan : He was organizing pro Ethiopian forces in the USA representing Ethiopia during Ethio-Italian war as Haile Selassie special representative

      Reply
  2. Dereje Mengesha says

    June 30, 2014 01:23 pm at 1:23 pm

    ነጋድራስ ናቸው ገብረህይወት ባይከዳኝ
    በነጋ በጠባ ማናቸው እያልከኝ
    ፈተና እያመጣህ በቃ አትጨቅጭቀኝ

    Reply
  3. Zenaneh Temesgen says

    June 30, 2014 07:54 pm at 7:54 pm

    እኔጃ ነው መልሴ እንዴት ላስታውሳቸው
    የታሪክ መድብል ውስጥ የለም አልበማቸው

    Reply
  4. Mengesha Asmare says

    June 30, 2014 07:55 pm at 7:55 pm

    የአገሬ ሰዎች በበጎ ስራቸዉ ሀገር ያወቃቸዉ
    እረ ብዙ ናቸዉ
    ሁሉንም ባንድ ጊዜ ቆጥረን ባንዘልቃቸዉ
    ቀስ በቀስ እያልነ እስኪ እንዘክራቸዉ
    የሀገሬ ታሪክ ትልቁ መፀሀፍ ከከታተባቸዉ
    ገ/ህይወት ባይከዳኝ ያነን ስመ ጥሩዉ
    ይመስላል ፎቷቸዉ

    Reply
  5. Bombu says

    June 30, 2014 10:18 pm at 10:18 pm

    እንደው በግርድፉ ፎቶውን ሲያሰሉት
    የቆየ ይመሥላል ዘመን ያለፈበት

    ደግሞ ሲያስተውሉ ግለስቡን ዘልቆ
    አለባበሱንም ካዩ ተጠንቅቆ
    ወጣት ከመሆኑም ዘና ከማለቱ
    ኮፍያው ከራሱ ከረባት ባንገቱ
    ሁሉንም አሥማምቶ የተነሳው ፎቶ
    ዘመነኛነቱን ያሳያል አጉልቶ

    በውጭ አገር ኖረው ያውቃሉ ለማለት
    ነበር ሙከራዬ ይሕ ሁሉ መዋተት

    ከዚህ በተረፈ የምስማማው እኔ
    የመገምት አቅም ባይኖረኝም ወኔ
    ቢሆኑ ደስ ይላል በያን ወመላኩ
    እንደተጠቀሰው ከላይ በመድረኩ

    Reply
  6. Bombu says

    June 30, 2014 10:40 pm at 10:40 pm

    አወይ የኔ ነገር አወይ የኔ ሥራ
    ግለሰብ ለይቼ ስሙን ሳላጣራ
    ካቀያየርኩዋቸው አንዱን ወደ ሌላ
    ማሥተካከሉ ላይ እንዲፈጠር መላ
    ወለላዬ ወይም የጎልጉል አዘጋጅ
    ማንንም ሳልጠይቅ ሳላመጣ አማላጅ
    ይስተካከልልኝ ጥያቄው ከመልሱ
    እንዲሁም ይታገድ ይቆይልኝ ሒሱ

    Reply
    • Editor says

      June 30, 2014 11:32 pm at 11:32 pm

      ወዳጃችን Bombu ምንም አያስቡ
      በውል ተስተውሏ መልሱና ሃሳቡ
      የመጀመሪያውን መልስ ተገቢው ቦታ ላይ አትመነዋል፡፡ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡ ሁለተኛ በማስተካከያነት የላኩትን ውብ ግጥም ላለማጥፋት ብለን ከ“ስህተቱ” ጋር እዚሁ ትተነዋል፡፡

      አርታኢ
      ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ

      Reply
  7. Tsegaye Kassa says

    July 1, 2014 06:28 am at 6:28 am

    አላዉቀውም እንጂ ባውቀውማ ኖሮ
    እነግርህ ነበረ ከቅድም ዠምሮ
    መገመቱንማ ልገምትላቹ
    የግምት የግምት ፈስም ዳለቻ ነው አትብሉኝ ባካቹ
    እኝህ ትልቅ አባት ታሪክ ያስቀመጡ
    ዛሬ ለትዝታ በፌስቡክ የመጡ
    የዋዛ አደለም የፀግሽ ግምቱ
    ገ/ሂወት ባይከዳኝ የጥንት የጠዋቱ

    Reply
  8. henos says

    July 8, 2014 11:14 am at 11:14 am

    gebrehiwot bykedagne nachew ”yehizib ena ye mengist astedader” yemilewun metshaf yetsafut

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule