በዚህ ርዕስ አጭር ጽሁፍ መፃፍ ከባድ ነው፡፡ ኢሕአፓን ያህል አንጋፋ ድርጅት ለመከፈል ብዙ ውጣ ውረድ፣ ውይይት፣ ንትርክ፣ ተደርጎበት በወቅቱ የነበሩትን አባላት አሳዝኖ የተከሰተ ሂደት ነው፡፡ በኢሕአፓ ታሪክ ተወደደም ተጠላ ይህ የመከፈል ጉዳይ በመጽሐፍ መልክ እንኳ ቢቀርብ እንዴት ነፃ ሆኖ ይቀርባል? የሚለው ይፈታተናል፡፡ ያም ሆነ ይህ መፃፉ አይቀርም፡፡ ለምን ተከፈለ? እንዴት ተከፈለ? ዋናው ምክንያት ምንድነው? ሂደቱስ? ኢሕአፓን ያህል ተመክሮ ያለው ፓርቲ እንዴት የቅራኔ አያያዝ ጥበቡ፣ ዕውቀቱ አነሰውና ለዚህ አሳፋሪ ድርጊት እጁን ሰጠ? ሂደቱ ከተከሰተም በኋላ መከፈሉን የሰሙ ደጋፊዎቹ፣ የቀድሞ አባላቱ እንደገና አንድ ለማድረግ ያደረጉት ጥረት ምነው ሳይሳካ ቀረ? ወዘተ. መልሱ እንኳንስ ሀገር ቤት ላሉት የኢሕአፓ የቀድሞ አባላት፣ ደጋፊዎችና ቤተሰቦች ሌሎችም ይቅርና ሲከፋፈል … [Read more...] about ኢሕአፓ ለምን ተከፈለ? ዛሬስ ምን መደረግ አለበት?
Opinions
የኔ ሃሳብ
“ከዚህ በኋላ ፍ/ ቤት ላለመቅረብ ወስኛለሁ!…”
(ኤርሚያስ አመልጋ - ከቂሊንጦ) ድፍን አንድ አመት!... በህግ ሊያስጠይቀኝ የሚችል ምንም አይነት የወንጀል ድርጊት ባልፈጸምኩበት እና ለክስ የሚያበቃ ምንም ተጨባጭ ማስረጃ በሌለበት ሁኔታ ለእስር ከተዳረግኩና ፍትህ አገኝ ብዬ ፍርድ ቤት መመላለስ ከጀመርኩ እነሆ ድፍን አንድ አመት ሞላኝ፡፡ የፌዴራል ፖሊስ፣ አቃቤ ህግ እና ፍርድ ቤት በአንድ ሳምባ በሚተነፍሱበት ስርዓት እና አገር ላይ፣ ገለልተኛ ፍርድ እና ሚዛናዊ ፍትህ ማግኘት እንደማይቻል በአንድ አመት የእስር ቤት ቆይታዬ ያረጋገጥኩት ሃቅ ነው!!! ከዚህ በኋላ ፍትህ አገኛለሁ ብሎ ማሰብ ራስን ማጃጃል አንደሆነ ተገልጾልኛል፤ አሁን ከስርዓቱ ፍትህ የምጠብቅበት ሳይሆን በእኔ ከደረሰውና ዙሪያዬን ከማየው ተነስቼ የአገራችንን የፍትህ ስርዓት ነውረኛ ባህሪ ለህዝብ የምገልጽበት ወቅት ነው፡፡ “መርምረን … [Read more...] about “ከዚህ በኋላ ፍ/ ቤት ላለመቅረብ ወስኛለሁ!…”
የሥራ ባልደረባዬ ሆይ! እንካ ስሙኒህን!!
አንድ አሜሪካዊ የሥራ ባልደረባዬ ተሁለት ሳምንታት በፊት አለወትሮው ቆጣ ብሎ ጸጉሩን እየነጨ ሲትከነከን አገኘሁት። “ምነው በመላጣህ ምክንያት የቁንጅና ውድድር ወደክ ወይስ የቀጠርካት ጉብል ቀረቺብህ!” ብዬ ልቀልድ ብሞክርም አለወትሮው ከንፈሮቹ አልሳሳ ጥርሶችም አልታይ አሉ። ሁለቴ ጠበቅ አድርጎ “እፍፉ…” ብሎ ታምቆ የቆዬ እስተንፋስ ከተነፈሰ በኋላ “ይህ ትራንፕ እሚባል ሰው ተቀናቃኙን ለማጥቃት ስልጣኑን መጠቀሙ ቅደመ አያቶቻችን የመሰረቱትን የአሜሪካ መሰረት የሚንድ ነው!” አለና ብሶቱን ደጋግሞ ገለጠ። አቶ ትራንፕ ተቀናቃኛቸውን በፖለቲካ ለማጥቃት የስልክ ንግግር ማድረጋቸው ይኸንን ጓደኛዬን እንደ ሽንኩርት ቁሊት ማትከንከኑ ገርሞኝ አይኔን አፍጥጬ ሳለሁ አንድ አገራችን እሰማው የነበረ ተረት ቁልጭ ብሎ ተፊቴ ተደቀነብኝ። “ማን? መቼ? የት? ” … [Read more...] about የሥራ ባልደረባዬ ሆይ! እንካ ስሙኒህን!!
Jawar Mohammed is the Al-Baghdadi of Addis Not an Oromo Activist!
Political/Social activists fight against injustice, suppression, and inequality and in the process, they give their lives to make life a little better for millions of others. Two world-famous activists are Martin Luthor King and Nelson Mandela. While the former gave his life fighting for equality for African Americans in the USA, the latter spent twenty years of his life in prison fighting Apartheid. While activists may naturally belong to one religious group, they never encourage beheadings … [Read more...] about Jawar Mohammed is the Al-Baghdadi of Addis Not an Oromo Activist!
ህወሃት ስምንት ፀሃፊያን (ghostwriters) ቀጥሮ መጽሐፍት እያፃፈ መሆኑ ተሰማ
ከመጋቢት/2010 ጀምሮ ራሱን ጦርነት ላይ እንዳለ አድርጎ የሚቆጥረው ህወሃት የለውጡን አመራር ስም ለማጥፋት ሶሻል ሚዲያውንና ሳተላይት ቴሌቪዥኖችን በመጠቀም ላይ እንዳለ ይታወቃል። በተጨማሪነት ከአገር አቀፉ ምርጫ ወዲህ እንዲደርሱ የተፈለጉ መፅሐፍቶችን ለህትመት ለማብቃት÷ ghostwriters ቀጥሮ በማፃፍ ላይ እንዳለ ለማወቅ ተችሏል። ይሄን የመፅሐፍት ዝግጅት ለመስራት ስምንት ፀሐፊያን የተመመሉ ሲሆን ፕሮጀክቱን በበላይነት ጌታቸው ረዳ ይመራዋል። ናሁሠናይ በላይ ናሁሰናይ በላይ የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ዳንኤል ብርሃኔ [አክቲቪስት] ተሳታፊ ዳንኤል ብርሃኔ ፍፁም ብርሃኔ [አክቲቪስት] ተሳታፊ ነጋ ዘሩ [ጋዜጠኛ] ተሳታፊ መሆናቸውን ሰምተናል። በተጨማሪም የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት እነ መረሳ ፀሃየ በዝግጅቱ ተሳትፎ እያደረጉ … [Read more...] about ህወሃት ስምንት ፀሃፊያን (ghostwriters) ቀጥሮ መጽሐፍት እያፃፈ መሆኑ ተሰማ
የመቀሌው መድረክ ትዝብት እና የሦስቱ ገፅ ግንባር ትራጆ ኮሚዴ
በሳምንቱ መግቢያ ላይ በመቀሌ ከተማ የተካሄደው ሃሳዊው የፌዴራሊስቶች መድረክ ከተሳታፊዎች የጀርባ መደብና ባህሪያት አንፃር ሦስት ገፅታ ነበረው። ገፅ አንድ:-የሙሰኞች ግንባር በቀዳሚው ገፅ ፊት አውራሪዎቹ ጋባዥና ተጋባዥ በሚል እንመልከታቸው። የጋባዡን ገፀ ባህሪ የሚላበሰው አባይ ፀሃዬ ሲሆን÷ የሙሰኞችን ግንባር የሚወክለው ተጋባዥ ደግሞ የቀድሞው ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዘደንት የነበረው መንበረፀሐይ ታደሰ ነው። ሁለቱን ሙሰኞች የሚያመሳስላቸው ባህርይ ሥልጣንን የሃብት ምንጭ ማድረጋቸው ብቻ ሳይሆን የፈፀሙት ምዝበራ ጉዳት ዘመን ተሻጋሪ መሆኑ ነው። አንዱ ፕሮጀክት አምካኝ ሌላው የፍትሕ ሥርዓቱን በአደባባይ የቀበረ መሆኑ የተለየ ያደረጋቸዋል። አባይ ፀሃዬ 77 ቢሊዮን ብር የስኳር ኮርፖሬሽን ፕሮጀክት ብር እንደ ሸንኮራ አገዳ ምጥጥ አድረጎ ኮርፖሬሽኑን ቀፎውን ያስቀረ … [Read more...] about የመቀሌው መድረክ ትዝብት እና የሦስቱ ገፅ ግንባር ትራጆ ኮሚዴ
31 Ethical Hackers ያወጡት መግለጫ
ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብና የኢትዮጵያ ወዳጆች አገራችንን ለአለፉት 27 ዓመታት ያሻውን በማድረግ በከፍተኛ አፈናና የጉልበት አገዛዝ ሲገዛ የነበረው ህወሃትና በሌሎች አክራሪ ብሄረተኞች ትብብርና ቅንጅት የታየውን የለውጥ ተስፋና እየተካሄዱ ያሉ ለውጦችን ለማደናቀፍ በከፍተኛ ሁኔታ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛሉ። ህወሃት በገዥነት ዘመኑ ከኢትዮጵያ ሕዝብ የዘረፈውን ሀብት በመጠቀም የተለያዩ ቡድኖችን በገንዘብ በመደለል ከትግራይ ውጭ ያለውን የአገራችንን ክፍል ከማተራመስ በላይ ወደ ማፍረስ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን በየቀኑ የአገራችንን ፖለቲካ ከሚዳስሱ ባለሙያወች በበቂ ሁኔታ ከተረዳን ቆይተናል። በዚህም ምክንያት አገራችንን ከተጋረጠባት ሴረኛ አደጋ ለመታደግ ከዚህ ቀደም በአሜሪካና አውሮፓ የምንገኝ በቁጥር 31 የምንሆን በሶፍት ዌርና ኢንፎርሜሽን ኮሚንኬሽን ሙያወች የተሰማራን … [Read more...] about 31 Ethical Hackers ያወጡት መግለጫ
“አልቃሻው ሚኒስትር ደኤታ” ኤርምያስ ለገሠ
በሕይወት በነበረበት ጊዜ ኢትዮጵያን ጠርንፎ የነበረውን ኢህአዴግን እንዲያገለግሉ የሚመለመሉ በርካታ ወዶገብ ጥቅመኞች ነበሩ። በአንድ ወቅት ተስፈኛ ካድሬዎችን ለመመልመል ሲኒየሮቹ ካድሬዎች በሄዱበት ክፍለከተማ ከተሰበሰቡት መካከል አንዱ ኤርሚያስ ለገሰ ነበር። በወቅቱ አብሮት የነበረ የቅርብ ወዳጄ እንደሚለው ከሆነ “ደርግን ገረሰስን” የሚሉት ተጋዳላዮች በወቅቱ ደረሰብን በማለት ከመድረኩ ሲያወሩ ኤርሚያስ ከሥር ሆኖ በአራት መዓዘን ያለቅስ ነበር። አገር ለመገንጠል የተነሱት የወንበዴዎች ክምችት “ቁርጠኝነታቸው፣ በቦምብ ላይ መረማመዳቸው፣ አንዱ ለሌላው ልሙት ማለቱ፣…” ነበር ኤርሚያስን ተንሰቅስቆ ያስለቀሰው፤ ይህንኑ ቃል በሌላ ጊዜ ደግሞታል። ይህንን እንስፍስፍ እጩ ካድሬ ማንነት የጠየቁ መልማዮች ወዲያውኑ በብርሃን ፍጥነት ኤርሚያስን ከክፍለከተማ አስፈነጠሩትና መድረሻውን አሁን … [Read more...] about “አልቃሻው ሚኒስትር ደኤታ” ኤርምያስ ለገሠ
ስብሃት ነጋ ስለ ደመቀ መኮንን፤ “ደመቀ የሸወደንን ያክል መሰሪው ጀበሃ (ሻእቢያ) እንኳን አልሸወደንም!”
የህወሓት ዘመን ማብቂያው አካባቢ ኃይለማርያም ደሳለኝ “ከሥልጣኔ ለቅቄአለሁ” ካለ በኋላ ለጠ/ሚ/ር ቦታ በተደረገው ሽኩቻ ዶ/ር ዐቢይ (የለማ ቡድን) አሸንፎ በወጣ ጊዜ የህወሓት ቡድን ወደ መቀሌ ሄዶ ሲመሽግ ስብሃት ነጋ በተፈጠረው ተናድዶ የሚከተለውን መናገሩ ታማጭ የመረጃ ምንጫችን አስታውቆናል። ስብሃት ነጋ በትግሪኛ የተናገረውና በአማርኛ ተተርጎመው የስብሃት ንግግር እንዲህ ይነበባል፤ “(ደመቀ) ለትህነግ ታማኝና ታዛዥ ነበር። ፈፅም! የተባለውን ነገር ለመፈፀም 'ለምን?' ብሎ እንኳን አያውቅም። አንድ ቀን ግን የሱዳን ግዛት የሆነውን አዋሳኝ መሬት ለመስጠት ‘ፈርም’ ሲባል ‘አይሆንም አልፈርምም!’ ብሎ አሻፈረኝ ሲል ያኔ ይህ ሰው አንድ ቀን እንደሚሸውደን እርግጠኛ ሁኜ ለጓዶቼ ነግሬያቸው ነበር። ሁሉም የእኔን እይታ ሳያቅማሙ ሲቀበሉኝ ጌታቸው (አሰፋ)ግን ‘አታስብ እሱ … [Read more...] about ስብሃት ነጋ ስለ ደመቀ መኮንን፤ “ደመቀ የሸወደንን ያክል መሰሪው ጀበሃ (ሻእቢያ) እንኳን አልሸወደንም!”
ሰላምን ከጦርነት፣ መፍረስን ካለመፍረስ የሚለይ ቀይ መስመር የለም!
በድሉ ዋቅጅራ (ዶ/ር) “እንደቀልድ፣ ሳናውቀው አገራችን ወደ ፍርስራሽነት ተቀየረች” አለ፣ አንድ ታዋቂ የየመን ጋዜጠኛ፤ በአንድ ቃለመጠይቁ ላይ። ነገሮች የረዥም፣ ተከታታይ ሂደት ውጤት ወይም መጨረሻ ናቸው፤ የድንገቴ ክስተት አይደሉም። ጦርነት ያለመግባባትና የቅራኔ ሂደት ውጤት ነው። ሞት ከጤንነት ጀምሮ፣ እየጠነከረ የሚሄድ ህመም ሒደት ውጤት ነው። በሥርዓትና ደንብ የቆመ ሀገር መፍረስም እንዲሁ የረዥም ጊዜ፣ ተከታታይ ከሥርዓትና ደንብ ማፈንገጥ ሒደት ውጤት ነው። የሀገር መሪዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ ፖለቲከኞች . . . ሁላችንም፣ “ኢትዮጵያ አትፈርስም” እያልን እንጮሀለን። ከጩኸቱ ጀርባ የቻሉትን እያደረጉ ያሉት ግን የሀይማኖት አባቶች ብቻ ናቸው፤ ዕንባቸውን ሽቅብ ወደ ፈጣሪ መንበር እየረጩ የመንፈስ ልጆቻቸውን ይለምናሉ፤ ምእመኑን በጸሎትና በጾም ያተጋሉ። ፖለቲከኞች … [Read more...] about ሰላምን ከጦርነት፣ መፍረስን ካለመፍረስ የሚለይ ቀይ መስመር የለም!










