ከመጋቢት/2010 ጀምሮ ራሱን ጦርነት ላይ እንዳለ አድርጎ የሚቆጥረው ህወሃት የለውጡን አመራር ስም ለማጥፋት ሶሻል ሚዲያውንና ሳተላይት ቴሌቪዥኖችን በመጠቀም ላይ እንዳለ ይታወቃል። በተጨማሪነት ከአገር አቀፉ ምርጫ ወዲህ እንዲደርሱ የተፈለጉ መፅሐፍቶችን ለህትመት ለማብቃት÷ ghostwriters ቀጥሮ በማፃፍ ላይ እንዳለ ለማወቅ ተችሏል። ይሄን የመፅሐፍት ዝግጅት ለመስራት ስምንት ፀሐፊያን የተመመሉ ሲሆን ፕሮጀክቱን በበላይነት ጌታቸው ረዳ ይመራዋል። ናሁሠናይ በላይ ናሁሰናይ በላይ የፕሮጀክቱ አስተባባሪ ዳንኤል ብርሃኔ [አክቲቪስት] ተሳታፊ ዳንኤል ብርሃኔ ፍፁም ብርሃኔ [አክቲቪስት] ተሳታፊ ነጋ ዘሩ [ጋዜጠኛ] ተሳታፊ መሆናቸውን ሰምተናል። በተጨማሪም የመቀሌ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት እነ መረሳ ፀሃየ በዝግጅቱ ተሳትፎ እያደረጉ … [Read more...] about ህወሃት ስምንት ፀሃፊያን (ghostwriters) ቀጥሮ መጽሐፍት እያፃፈ መሆኑ ተሰማ
Opinions
የኔ ሃሳብ
የመቀሌው መድረክ ትዝብት እና የሦስቱ ገፅ ግንባር ትራጆ ኮሚዴ
በሳምንቱ መግቢያ ላይ በመቀሌ ከተማ የተካሄደው ሃሳዊው የፌዴራሊስቶች መድረክ ከተሳታፊዎች የጀርባ መደብና ባህሪያት አንፃር ሦስት ገፅታ ነበረው። ገፅ አንድ:-የሙሰኞች ግንባር በቀዳሚው ገፅ ፊት አውራሪዎቹ ጋባዥና ተጋባዥ በሚል እንመልከታቸው። የጋባዡን ገፀ ባህሪ የሚላበሰው አባይ ፀሃዬ ሲሆን÷ የሙሰኞችን ግንባር የሚወክለው ተጋባዥ ደግሞ የቀድሞው ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዘደንት የነበረው መንበረፀሐይ ታደሰ ነው። ሁለቱን ሙሰኞች የሚያመሳስላቸው ባህርይ ሥልጣንን የሃብት ምንጭ ማድረጋቸው ብቻ ሳይሆን የፈፀሙት ምዝበራ ጉዳት ዘመን ተሻጋሪ መሆኑ ነው። አንዱ ፕሮጀክት አምካኝ ሌላው የፍትሕ ሥርዓቱን በአደባባይ የቀበረ መሆኑ የተለየ ያደረጋቸዋል። አባይ ፀሃዬ 77 ቢሊዮን ብር የስኳር ኮርፖሬሽን ፕሮጀክት ብር እንደ ሸንኮራ አገዳ ምጥጥ አድረጎ ኮርፖሬሽኑን ቀፎውን ያስቀረ … [Read more...] about የመቀሌው መድረክ ትዝብት እና የሦስቱ ገፅ ግንባር ትራጆ ኮሚዴ
31 Ethical Hackers ያወጡት መግለጫ
ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብና የኢትዮጵያ ወዳጆች አገራችንን ለአለፉት 27 ዓመታት ያሻውን በማድረግ በከፍተኛ አፈናና የጉልበት አገዛዝ ሲገዛ የነበረው ህወሃትና በሌሎች አክራሪ ብሄረተኞች ትብብርና ቅንጅት የታየውን የለውጥ ተስፋና እየተካሄዱ ያሉ ለውጦችን ለማደናቀፍ በከፍተኛ ሁኔታ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛሉ። ህወሃት በገዥነት ዘመኑ ከኢትዮጵያ ሕዝብ የዘረፈውን ሀብት በመጠቀም የተለያዩ ቡድኖችን በገንዘብ በመደለል ከትግራይ ውጭ ያለውን የአገራችንን ክፍል ከማተራመስ በላይ ወደ ማፍረስ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን በየቀኑ የአገራችንን ፖለቲካ ከሚዳስሱ ባለሙያወች በበቂ ሁኔታ ከተረዳን ቆይተናል። በዚህም ምክንያት አገራችንን ከተጋረጠባት ሴረኛ አደጋ ለመታደግ ከዚህ ቀደም በአሜሪካና አውሮፓ የምንገኝ በቁጥር 31 የምንሆን በሶፍት ዌርና ኢንፎርሜሽን ኮሚንኬሽን ሙያወች የተሰማራን … [Read more...] about 31 Ethical Hackers ያወጡት መግለጫ
“አልቃሻው ሚኒስትር ደኤታ” ኤርምያስ ለገሠ
በሕይወት በነበረበት ጊዜ ኢትዮጵያን ጠርንፎ የነበረውን ኢህአዴግን እንዲያገለግሉ የሚመለመሉ በርካታ ወዶገብ ጥቅመኞች ነበሩ። በአንድ ወቅት ተስፈኛ ካድሬዎችን ለመመልመል ሲኒየሮቹ ካድሬዎች በሄዱበት ክፍለከተማ ከተሰበሰቡት መካከል አንዱ ኤርሚያስ ለገሰ ነበር። በወቅቱ አብሮት የነበረ የቅርብ ወዳጄ እንደሚለው ከሆነ “ደርግን ገረሰስን” የሚሉት ተጋዳላዮች በወቅቱ ደረሰብን በማለት ከመድረኩ ሲያወሩ ኤርሚያስ ከሥር ሆኖ በአራት መዓዘን ያለቅስ ነበር። አገር ለመገንጠል የተነሱት የወንበዴዎች ክምችት “ቁርጠኝነታቸው፣ በቦምብ ላይ መረማመዳቸው፣ አንዱ ለሌላው ልሙት ማለቱ፣…” ነበር ኤርሚያስን ተንሰቅስቆ ያስለቀሰው፤ ይህንኑ ቃል በሌላ ጊዜ ደግሞታል። ይህንን እንስፍስፍ እጩ ካድሬ ማንነት የጠየቁ መልማዮች ወዲያውኑ በብርሃን ፍጥነት ኤርሚያስን ከክፍለከተማ አስፈነጠሩትና መድረሻውን አሁን … [Read more...] about “አልቃሻው ሚኒስትር ደኤታ” ኤርምያስ ለገሠ
ስብሃት ነጋ ስለ ደመቀ መኮንን፤ “ደመቀ የሸወደንን ያክል መሰሪው ጀበሃ (ሻእቢያ) እንኳን አልሸወደንም!”
የህወሓት ዘመን ማብቂያው አካባቢ ኃይለማርያም ደሳለኝ “ከሥልጣኔ ለቅቄአለሁ” ካለ በኋላ ለጠ/ሚ/ር ቦታ በተደረገው ሽኩቻ ዶ/ር ዐቢይ (የለማ ቡድን) አሸንፎ በወጣ ጊዜ የህወሓት ቡድን ወደ መቀሌ ሄዶ ሲመሽግ ስብሃት ነጋ በተፈጠረው ተናድዶ የሚከተለውን መናገሩ ታማጭ የመረጃ ምንጫችን አስታውቆናል። ስብሃት ነጋ በትግሪኛ የተናገረውና በአማርኛ ተተርጎመው የስብሃት ንግግር እንዲህ ይነበባል፤ “(ደመቀ) ለትህነግ ታማኝና ታዛዥ ነበር። ፈፅም! የተባለውን ነገር ለመፈፀም 'ለምን?' ብሎ እንኳን አያውቅም። አንድ ቀን ግን የሱዳን ግዛት የሆነውን አዋሳኝ መሬት ለመስጠት ‘ፈርም’ ሲባል ‘አይሆንም አልፈርምም!’ ብሎ አሻፈረኝ ሲል ያኔ ይህ ሰው አንድ ቀን እንደሚሸውደን እርግጠኛ ሁኜ ለጓዶቼ ነግሬያቸው ነበር። ሁሉም የእኔን እይታ ሳያቅማሙ ሲቀበሉኝ ጌታቸው (አሰፋ)ግን ‘አታስብ እሱ … [Read more...] about ስብሃት ነጋ ስለ ደመቀ መኮንን፤ “ደመቀ የሸወደንን ያክል መሰሪው ጀበሃ (ሻእቢያ) እንኳን አልሸወደንም!”
ሰላምን ከጦርነት፣ መፍረስን ካለመፍረስ የሚለይ ቀይ መስመር የለም!
በድሉ ዋቅጅራ (ዶ/ር) “እንደቀልድ፣ ሳናውቀው አገራችን ወደ ፍርስራሽነት ተቀየረች” አለ፣ አንድ ታዋቂ የየመን ጋዜጠኛ፤ በአንድ ቃለመጠይቁ ላይ። ነገሮች የረዥም፣ ተከታታይ ሂደት ውጤት ወይም መጨረሻ ናቸው፤ የድንገቴ ክስተት አይደሉም። ጦርነት ያለመግባባትና የቅራኔ ሂደት ውጤት ነው። ሞት ከጤንነት ጀምሮ፣ እየጠነከረ የሚሄድ ህመም ሒደት ውጤት ነው። በሥርዓትና ደንብ የቆመ ሀገር መፍረስም እንዲሁ የረዥም ጊዜ፣ ተከታታይ ከሥርዓትና ደንብ ማፈንገጥ ሒደት ውጤት ነው። የሀገር መሪዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣ ፖለቲከኞች . . . ሁላችንም፣ “ኢትዮጵያ አትፈርስም” እያልን እንጮሀለን። ከጩኸቱ ጀርባ የቻሉትን እያደረጉ ያሉት ግን የሀይማኖት አባቶች ብቻ ናቸው፤ ዕንባቸውን ሽቅብ ወደ ፈጣሪ መንበር እየረጩ የመንፈስ ልጆቻቸውን ይለምናሉ፤ ምእመኑን በጸሎትና በጾም ያተጋሉ። ፖለቲከኞች … [Read more...] about ሰላምን ከጦርነት፣ መፍረስን ካለመፍረስ የሚለይ ቀይ መስመር የለም!
ችግራችን አጼ ምኒልክ ከሆኑ እውነቱን ተነጋግረን እኛም አርፈን ሕዝባችንን አናሳርፍ
የኢትዮጵያ ፖለቲካ እጅግ ያሳስበኛል፤ ለእኔ ብቻ ሳይሆን ለሚረከቡን ልጆችና ልጆቻቸው ጭምር ሳስብ የሀገራችን ፖለቲካ እንዳልተፈጠረ ሰው ቢታሰብ ደስ ይለኛል፤ ምክንያቱም በመኖሩ የሚፈይደው ከሌለ፡ አለመኖሩ እጅግ የሚሻል ነውና:: ነገር ግን ወደንም ሆነ ሳንወድ ተፈጥሯልና ስለእርሱ (ስለፖለቲካችን) ማሰብ ግድ እንደሚልም አምኛለሁ። በዚህ ዓለም ያሉ ምሁራን ፖለቲካ የአንድን ሰው ሕይወት የሚነካና ሰውም ከፖለቲካ ርቆ መኖር የማይችል ፍጡር ነው ይላሉ። እውነትም ፖለቲካ ብትርቀውም ተከትሎህ ባለህበት ይነካሃል፤ ብትቀርበውም ደግሞ የበለጠ ይነካሃል። በመሆኑም ምሁራን ያሉት ትክክል ነው ብየ ማሰብን ጀመርሁ። እንግዲያስ ፖለቲካ ዝም ብንለውም፣ ብንርቀውም፣ የማይለቀንና የማይተወን ከሆነ ስለ እርሱ መነጋገርና ማሰብ ግለሰባዊም ቡድናዊም ግዴታ ነው ማለት ነው፤ በዚህ ከተስማማን … [Read more...] about ችግራችን አጼ ምኒልክ ከሆኑ እውነቱን ተነጋግረን እኛም አርፈን ሕዝባችንን አናሳርፍ
ጃዋር እና ህወሓት፤ ከክህደት የመነጨ የባላንጣዎቹ ፍቅር!
የኢትዮጵያ ፖለቲካ መሰረታዊ ችግር “አለማወቅ” ነው። ይህን ስል ለአንዳንዶች ንቀት አሊያም እብሪት ሊመስል ይችላል። ነገር ግን ስለ እኔ የሚኖራችሁ ስሜት ያነሳሁትን ሃሳብ ቅንጣት ያህል አይቀይረውም። ምክንያቱም እዚህ ሀገር ያለው መሰረታዊ ችግር አላዋቂነት ነው። አዋቂ ማለት ጠያቂ ነው። ምንም ነገር ሲሆን “ምን? የት? እንዴት? ለምን?” የሚሉትን ጥያቄዎች ያነሳል። ለእነዚህ ጥያቄዎች አጥጋቢ ምላሽ ሲያገኝ እርምጃ ይወስዳል። ኢትዮጵያ ውስጥ ግን ጥያቄ የሚጀምረው ከድርጊት በኋላ ነው። በተለይ የዛሬ ትውልድ የፊት ገፅታሀን የሚያጣራው አንገትህን በሜንጫ ቆርጦ ከጣለ በኋላ ነው። ለምሳሌ አቶ ጃዋር መሃመድ በፌስቡክ ገፁ ላይ “ተከብቤያለሁ” ብሎ ሲፅፍ በዚያ ውድቅት ሌሊት ወጣቱ ድንጋይና ፌሮ ይዞ መሮጥ ከመጀመሩ በፊት “ጃዋር ማንና የት ነው? ጃዋር ለምንና እንዴት … [Read more...] about ጃዋር እና ህወሓት፤ ከክህደት የመነጨ የባላንጣዎቹ ፍቅር!
የኢትዮጵያን የ6 ½ ዓመት በጀት የሚሸፍን ገንዘብ በህወሓት ዘመን ተዘርፏል
ኢትዮጵያ ባለፉት 30 ዓመታት 30 ቢሊዮን ዶላር ተዘርፋለች! ኢህአዴግ ወደ ሥልጣን ከመጣ ጀምሮ 30 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ከኢትዮጵያ በሕገ ወጥ መንገድ መሸሸቱንና ገንዘቡንም ለማስመለስ መንግሥት ከባድ ሥራ ከፊቱ እንደሚጠብቀው ምሁራን ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ከሀገር የሸሸውን ገንዘብ ለማስመለስ ከፍተኛ ጥረት ቢጠይቅም መንግሥት ጉዳዩን እንደሚከታተለው አሳውቀው የነበረ ቢሆንም ተግባራዊ እንቅስቃሴ እንዳልታዬ ምሁራኑ ገልጸዋል። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የምጣኔ ሀብት ምሁሩ ፕሮፌሰር ዓለማየሁ ገዳ እንደገለጹት በኢህአዴግ ዘመነ አገዛዝ ከኢትዮጵያ ወደተለያዩ ሀገራት በሙስና እና ማጭበርበር የሸሸው ገንዘብ 30 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር እንደሚደርስ በጥናት ተረጋግጧል፤ ገንዘቡም በወቅቱ የኢትዮጵያን የስድስት ዓመት ተኩል በጀት መሸፈን የሚችል … [Read more...] about የኢትዮጵያን የ6 ½ ዓመት በጀት የሚሸፍን ገንዘብ በህወሓት ዘመን ተዘርፏል
ያበደውን አድረን ማወቃችን አይቀርም!
“በብዙ እብዶች መካከል ጤነኛ ያብዳል” ይባላል ይህን እውነታ ኡመር ሱሌማን ነው ከ18 አመት በፊት የተናገረው። ብዙ ሰዎች የወደዱት እምቢ ካለ ወይም እነሱ የጠሉትን ከወደደ “እብድ” ወይም “ከሃዲ መባሉ አይቀርም። በዚህ ውስጥ አልፈን ነው የመጣነው እኔ ጤንነቴን በደንብ አውቀዋለሁ የሰውም ማረጋገጫ አልፈልግም ለሰውም እንደዛው ትልቅና አስቀያሚ በሽታ ነው ያለው። ይህን ለማከምና ለማስተካከል መታገል ትክክል ነው ግን ደግሞ ትግሉ አገር በሚያፈርስ መልኩ መሆን የለበትም። የፈለገ ችግር ቢኖር ከየመን ከሊቢያና ከሶሪያ ኢትዮጵያ ትሻላለች! የመንን ወደ ኢትዮጵያ ማምጣት እንጂ ኢትዮጵያን ወደ የመን መውሰድ ጤንነት አይደለም። ሩዋንዳን የዘነጋ ሰው በራሱ በሽታ ነው። ተቀምጠው የሰቀሉትን ቆመው ማውረድ ይቸግር ይሆናል። ያጣነውን ብቻ ሳይሆን ያለንንም ማስታወስ ተገቢ ነው … [Read more...] about ያበደውን አድረን ማወቃችን አይቀርም!