• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ከዚህ በኋላ ፍ/ ቤት ላለመቅረብ ወስኛለሁ!…”

December 30, 2019 05:56 am by Editor Leave a Comment

(ኤርሚያስ አመልጋ – ከቂሊንጦ)

ድፍን አንድ አመት!…

በህግ ሊያስጠይቀኝ የሚችል ምንም አይነት የወንጀል ድርጊት ባልፈጸምኩበት እና ለክስ የሚያበቃ ምንም ተጨባጭ ማስረጃ በሌለበት ሁኔታ ለእስር ከተዳረግኩና ፍትህ አገኝ ብዬ ፍርድ ቤት መመላለስ ከጀመርኩ እነሆ ድፍን አንድ አመት ሞላኝ፡፡

የፌዴራል ፖሊስ፣ አቃቤ ህግ እና ፍርድ ቤት በአንድ ሳምባ በሚተነፍሱበት ስርዓት እና አገር ላይ፣ ገለልተኛ ፍርድ እና ሚዛናዊ ፍትህ ማግኘት እንደማይቻል በአንድ አመት የእስር ቤት ቆይታዬ ያረጋገጥኩት ሃቅ ነው!!!

ከዚህ በኋላ ፍትህ አገኛለሁ ብሎ ማሰብ ራስን ማጃጃል አንደሆነ ተገልጾልኛል፤ አሁን ከስርዓቱ ፍትህ የምጠብቅበት ሳይሆን በእኔ ከደረሰውና ዙሪያዬን ከማየው ተነስቼ የአገራችንን የፍትህ ስርዓት ነውረኛ ባህሪ ለህዝብ የምገልጽበት ወቅት ነው፡፡

“መርምረን እናስራለን እንጂ፣ አስረን አንመረምርም” የተባለለትን የለውጥ ዲስኩርና ፕሮፖጋንዳ ተከትሎ፣ ብዙ ተስፋ የተጣለበት የፍትህ ስርዓት፣ ዛሬም እንደ ትናንቱ ፍጹም የመንግስት ወገንተኝነቱን እና የአምባገነን መንግስት መሣሪያና መጠቀሚያ ሆኖ መቀጠሉን ለመላው ኢትዮጵያውያንና ለዓለም በድፍረት ማሳወቅ አስፈላጊ መሆኑን ከልብ አምኜበታለሁ፡፡

ከዜጎች ጎን ሆኖ ለእውነት፣ ለፍትህና ለህግ ልዕልና የሚቆም ስርዓት መገንባት ቀጣይ የአገራችን ዜጎች ትልቅ የቤት ስራ መሆኑን በአጽንኦት ማስገንዘብ እወዳለሁ፡፡

ራሳቸውን ከወገንተኝነት ካላጸዱ የፖሊስ፣ የአቃቤ ህግ እና የፍርድ ቤት ተቋማት ጋራ የተጓዝኩበት ረጅም ጎዳና፣ በፍትህ ስርዓቱ ላይ እምነት መጣሌን ትቼ ከመንገዱ ወጣ እንድልና ራሴን በጽሞና እንድጠይቅ አስገድዶኛል፤ አልፎ ተርፎም ከበስተጀርባ በስውር እጆች እየተቀነባበረ የሚሰራብኝ ትልቅ ድራማ እንዳለ ግልጽ አድርጎልኛል፡፡

ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ እንደገለጽኩት፣ ከኢምፔሪያል ሆቴል ሽያጭ ጋር በተያያዘ ፖሊስ ለመጀመሪያ ጊዜ ለቃለ-መጠይቅ እፈልግሃለሁ ብሎ ሲጠራኝ፣ ጥሪውን አክብሬ በመሄድ ስለጉዳዩ በቂ ማብራሪያ ሰጥቼ ነበር፡፡ ሊያስጠይቀኝ የሚችልና ለክስ የሚያበቃ ምንም ጉዳይ እንደሌለ በማስረዳት ተግባብተን ነበር የተለያየነው፡፡

ከዚያ ቀጥሎም፣ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ምንም አይነት የጥያቄም ሆነ የአቋም ለውጥ ሳያደርግ እንደገና በሌላ ሁለተኛ ዙር በጉዳዩ ዙሪያ ማብራሪያ እንድሰጥ ጠየቀኝ፡፡ እኔም በተጠየቅኩት መሰረት በቂ ማብራሪያ በመስጠት፣ ሊያስከስሰኝ የሚችል ምንም ጉዳይ እንደሌለ በአሳማኝ ማስረጃዎችና በምክንያታዊነት አስረዳሁ፡፡

ያቀረብኩት ማብራሪያ አሳማኝ ሆኖ ሳለ ግን፣ የመንግስት ፍላጎት በሚመስል እናባልጠበቅኩት መልኩ ወደ እስር ቤት እንድገባ ተደረግኩ፡፡ በዚህ መልኩ በቂ መረጃና ማስረጃ በሌለበት ወህኒ ከተወረወርኩና እስር ቤት ታጉሬ ፍትህ ፍለጋ ቀናትን፣ ሳምንታትንና ወራትን መቁጠር ከጀመርኩ ይሄው ድፍን አንድ አመት ሞላኝ፡፡

ባለፈው ታህሳስ 17 ቀን 2012 ዓ.ም…

ማልጄ ወደ ልደታ ፍርድ ቤት ስሄድ፣ በእለቱ የሚሰየመው ችሎት የመጨረሻ ብይን እንደሚሰጠኝ በመተማመንና በሙሉ ተስፋ ነበር፡፡ ችሎቱ ሌላ ቀጠሮ ሲሰጥ ግን፣ በውስጤ የተዘራው ተስፋ ድንገት መከነ፡፡ ቀጣይ ያልታወቁ ወራትን በእስር ስማቅቅ እንድገፋ የሚያደርገኝ ቀጠሮ የተሰጠኝ፣ ከፍርድ ቤቶች በስተጀርባ ባሉት ስውር እጆች ግፊት እንደሆነ ቁልጭ አድርጎ ታየኝ፡፡

ይህን እውነታ እየተረዳሁ፣ ፍትህ አገኛለሁ ብዬ መተማመን ከንቱ ጅልነት ነው፡፡ ፍርድ ቤቱ ከዚህ በኋላ የሚሰጠው ፍትህ ቢኖር እንኳን፣ “የዘገየ ፍትህ እንደተነፈገ ይቆጠራል” የሚለው ብሒል እንኳን የሚገልጸው አይመስለኝም፡፡

በአገራችን ነጻና ገለልተኛ ተቋማትን ለመገንባት በተደረገውረጅም ትግል የተከፈለው መስዋዕትነት፣ በጠቅላይ አቃቤ ህግ፣ በፖሊስና በፍርድ ቤቶች ነውረኛ እና ወጋኝ አካሄድ ከንቱ መቅረቱን ባሰብኩ ጊዜ ጥልቅ ሃዘን ይሰማኛል፡፡

በየዘመናቱ ለመጣው አምባገነን ስርዓት ሁሉ ትልቅ መገልገያ ሆነው የዘለቁት ከላይ የጠቀስኳቸው ተቋማት ነጻና ገለልተኛ መሆን እስካልቻሉ ድረስ፣ የዜጎች መብት ይረጋገጣል ብሎ ማሰብ ፍጹም የማይታሰብ ነው፡፡

የታመመውን የአገራችን ኢኮኖሚ ለማከም እንዲሁም በስርዓቱ ተስፋ ቢስ የሆኑ የአገራችን ወጣቶችን ወደ ዘላቂ መሻሻልና ዕድገት ሊወስዱ የሚያስችሉ ትልልቅ ዕቅዶችን ለመተግበር በተነሳሁበት ወቅት፣ከበስተጀርባ ባሉ ስውር እጆች የሚጎነጎንብኝ ሴራ እና የሚፈጸምብኝ ደባ፣ ፖለቲካዊ ባህሪ እንዳለው ለመገንዘብ ችያለሁ፤ መላው ኢትዮጵያዊም ይህንን እውነታ እንዲረዳልኝ እፈልጋለሁ፡፡

ከአሁን በኋላ ከወገንተኝነት ካልጸዳ ፍርድ ቤት ችሎት መታደም፣ “ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ” እንደሚሉት ራስን ማታለል ሆኖ አግኝቼዋለሁ፤ ስለሆነም የራሴን አቋም መያዜን እና ከዚህ በኋላ ፍትህ ፍለጋ ወደ ፍርድ ቤት ላለመሄድና ችሎት ፊት ላለመቅረብ ቁርጥ ውሳኔ ላይ መድረሴንለህዝቡ በይፋ ለማሳወቅ እፈልጋለሁ፡፡

በመጨረሻም በኖቤል የሰላም ተሸላሚው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አህመድ እንዲሁም በጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ በጠቅላይ አቃቤ ህግ እና በሌሎች ተቋማትና ሃላፊዎቻቸው ላይ የተሰማኝን ጥልቅ ሃዘንና በእነሱ ተስፋ መቁረጤን ሳልናገር ማለፍ አልፈልግም፡፡

ኢትዮጵያውያን ሁሉ ለመሰረታዊና ለሁለንተናዊ ለውጥ ዝግጁ የሚሆኑበት፤ ዘላቂ ትግል በማድረግ ነጻና ገለልተኛ ተቋማትን መገንባት የሚያስፈልግበት ጊዜው አሁን ነው!!!

(የማይነበብ ፊርማ)

ኤርሚያስ አመልጋ ፣ ታህሳስ 20 ቀን 2012 ዓ.ም፣ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት፣ አዲስ አበባ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: ermiyas amelga, Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule