• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ከዚህ በኋላ ፍ/ ቤት ላለመቅረብ ወስኛለሁ!…”

December 30, 2019 05:56 am by Editor Leave a Comment

(ኤርሚያስ አመልጋ – ከቂሊንጦ)

ድፍን አንድ አመት!…

በህግ ሊያስጠይቀኝ የሚችል ምንም አይነት የወንጀል ድርጊት ባልፈጸምኩበት እና ለክስ የሚያበቃ ምንም ተጨባጭ ማስረጃ በሌለበት ሁኔታ ለእስር ከተዳረግኩና ፍትህ አገኝ ብዬ ፍርድ ቤት መመላለስ ከጀመርኩ እነሆ ድፍን አንድ አመት ሞላኝ፡፡

የፌዴራል ፖሊስ፣ አቃቤ ህግ እና ፍርድ ቤት በአንድ ሳምባ በሚተነፍሱበት ስርዓት እና አገር ላይ፣ ገለልተኛ ፍርድ እና ሚዛናዊ ፍትህ ማግኘት እንደማይቻል በአንድ አመት የእስር ቤት ቆይታዬ ያረጋገጥኩት ሃቅ ነው!!!

ከዚህ በኋላ ፍትህ አገኛለሁ ብሎ ማሰብ ራስን ማጃጃል አንደሆነ ተገልጾልኛል፤ አሁን ከስርዓቱ ፍትህ የምጠብቅበት ሳይሆን በእኔ ከደረሰውና ዙሪያዬን ከማየው ተነስቼ የአገራችንን የፍትህ ስርዓት ነውረኛ ባህሪ ለህዝብ የምገልጽበት ወቅት ነው፡፡

“መርምረን እናስራለን እንጂ፣ አስረን አንመረምርም” የተባለለትን የለውጥ ዲስኩርና ፕሮፖጋንዳ ተከትሎ፣ ብዙ ተስፋ የተጣለበት የፍትህ ስርዓት፣ ዛሬም እንደ ትናንቱ ፍጹም የመንግስት ወገንተኝነቱን እና የአምባገነን መንግስት መሣሪያና መጠቀሚያ ሆኖ መቀጠሉን ለመላው ኢትዮጵያውያንና ለዓለም በድፍረት ማሳወቅ አስፈላጊ መሆኑን ከልብ አምኜበታለሁ፡፡

ከዜጎች ጎን ሆኖ ለእውነት፣ ለፍትህና ለህግ ልዕልና የሚቆም ስርዓት መገንባት ቀጣይ የአገራችን ዜጎች ትልቅ የቤት ስራ መሆኑን በአጽንኦት ማስገንዘብ እወዳለሁ፡፡

ራሳቸውን ከወገንተኝነት ካላጸዱ የፖሊስ፣ የአቃቤ ህግ እና የፍርድ ቤት ተቋማት ጋራ የተጓዝኩበት ረጅም ጎዳና፣ በፍትህ ስርዓቱ ላይ እምነት መጣሌን ትቼ ከመንገዱ ወጣ እንድልና ራሴን በጽሞና እንድጠይቅ አስገድዶኛል፤ አልፎ ተርፎም ከበስተጀርባ በስውር እጆች እየተቀነባበረ የሚሰራብኝ ትልቅ ድራማ እንዳለ ግልጽ አድርጎልኛል፡፡

ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ እንደገለጽኩት፣ ከኢምፔሪያል ሆቴል ሽያጭ ጋር በተያያዘ ፖሊስ ለመጀመሪያ ጊዜ ለቃለ-መጠይቅ እፈልግሃለሁ ብሎ ሲጠራኝ፣ ጥሪውን አክብሬ በመሄድ ስለጉዳዩ በቂ ማብራሪያ ሰጥቼ ነበር፡፡ ሊያስጠይቀኝ የሚችልና ለክስ የሚያበቃ ምንም ጉዳይ እንደሌለ በማስረዳት ተግባብተን ነበር የተለያየነው፡፡

ከዚያ ቀጥሎም፣ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ምንም አይነት የጥያቄም ሆነ የአቋም ለውጥ ሳያደርግ እንደገና በሌላ ሁለተኛ ዙር በጉዳዩ ዙሪያ ማብራሪያ እንድሰጥ ጠየቀኝ፡፡ እኔም በተጠየቅኩት መሰረት በቂ ማብራሪያ በመስጠት፣ ሊያስከስሰኝ የሚችል ምንም ጉዳይ እንደሌለ በአሳማኝ ማስረጃዎችና በምክንያታዊነት አስረዳሁ፡፡

ያቀረብኩት ማብራሪያ አሳማኝ ሆኖ ሳለ ግን፣ የመንግስት ፍላጎት በሚመስል እናባልጠበቅኩት መልኩ ወደ እስር ቤት እንድገባ ተደረግኩ፡፡ በዚህ መልኩ በቂ መረጃና ማስረጃ በሌለበት ወህኒ ከተወረወርኩና እስር ቤት ታጉሬ ፍትህ ፍለጋ ቀናትን፣ ሳምንታትንና ወራትን መቁጠር ከጀመርኩ ይሄው ድፍን አንድ አመት ሞላኝ፡፡

ባለፈው ታህሳስ 17 ቀን 2012 ዓ.ም…

ማልጄ ወደ ልደታ ፍርድ ቤት ስሄድ፣ በእለቱ የሚሰየመው ችሎት የመጨረሻ ብይን እንደሚሰጠኝ በመተማመንና በሙሉ ተስፋ ነበር፡፡ ችሎቱ ሌላ ቀጠሮ ሲሰጥ ግን፣ በውስጤ የተዘራው ተስፋ ድንገት መከነ፡፡ ቀጣይ ያልታወቁ ወራትን በእስር ስማቅቅ እንድገፋ የሚያደርገኝ ቀጠሮ የተሰጠኝ፣ ከፍርድ ቤቶች በስተጀርባ ባሉት ስውር እጆች ግፊት እንደሆነ ቁልጭ አድርጎ ታየኝ፡፡

ይህን እውነታ እየተረዳሁ፣ ፍትህ አገኛለሁ ብዬ መተማመን ከንቱ ጅልነት ነው፡፡ ፍርድ ቤቱ ከዚህ በኋላ የሚሰጠው ፍትህ ቢኖር እንኳን፣ “የዘገየ ፍትህ እንደተነፈገ ይቆጠራል” የሚለው ብሒል እንኳን የሚገልጸው አይመስለኝም፡፡

በአገራችን ነጻና ገለልተኛ ተቋማትን ለመገንባት በተደረገውረጅም ትግል የተከፈለው መስዋዕትነት፣ በጠቅላይ አቃቤ ህግ፣ በፖሊስና በፍርድ ቤቶች ነውረኛ እና ወጋኝ አካሄድ ከንቱ መቅረቱን ባሰብኩ ጊዜ ጥልቅ ሃዘን ይሰማኛል፡፡

በየዘመናቱ ለመጣው አምባገነን ስርዓት ሁሉ ትልቅ መገልገያ ሆነው የዘለቁት ከላይ የጠቀስኳቸው ተቋማት ነጻና ገለልተኛ መሆን እስካልቻሉ ድረስ፣ የዜጎች መብት ይረጋገጣል ብሎ ማሰብ ፍጹም የማይታሰብ ነው፡፡

የታመመውን የአገራችን ኢኮኖሚ ለማከም እንዲሁም በስርዓቱ ተስፋ ቢስ የሆኑ የአገራችን ወጣቶችን ወደ ዘላቂ መሻሻልና ዕድገት ሊወስዱ የሚያስችሉ ትልልቅ ዕቅዶችን ለመተግበር በተነሳሁበት ወቅት፣ከበስተጀርባ ባሉ ስውር እጆች የሚጎነጎንብኝ ሴራ እና የሚፈጸምብኝ ደባ፣ ፖለቲካዊ ባህሪ እንዳለው ለመገንዘብ ችያለሁ፤ መላው ኢትዮጵያዊም ይህንን እውነታ እንዲረዳልኝ እፈልጋለሁ፡፡

ከአሁን በኋላ ከወገንተኝነት ካልጸዳ ፍርድ ቤት ችሎት መታደም፣ “ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ” እንደሚሉት ራስን ማታለል ሆኖ አግኝቼዋለሁ፤ ስለሆነም የራሴን አቋም መያዜን እና ከዚህ በኋላ ፍትህ ፍለጋ ወደ ፍርድ ቤት ላለመሄድና ችሎት ፊት ላለመቅረብ ቁርጥ ውሳኔ ላይ መድረሴንለህዝቡ በይፋ ለማሳወቅ እፈልጋለሁ፡፡

በመጨረሻም በኖቤል የሰላም ተሸላሚው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ አህመድ እንዲሁም በጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ በጠቅላይ አቃቤ ህግ እና በሌሎች ተቋማትና ሃላፊዎቻቸው ላይ የተሰማኝን ጥልቅ ሃዘንና በእነሱ ተስፋ መቁረጤን ሳልናገር ማለፍ አልፈልግም፡፡

ኢትዮጵያውያን ሁሉ ለመሰረታዊና ለሁለንተናዊ ለውጥ ዝግጁ የሚሆኑበት፤ ዘላቂ ትግል በማድረግ ነጻና ገለልተኛ ተቋማትን መገንባት የሚያስፈልግበት ጊዜው አሁን ነው!!!

(የማይነበብ ፊርማ)

ኤርሚያስ አመልጋ ፣ ታህሳስ 20 ቀን 2012 ዓ.ም፣ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት፣ አዲስ አበባ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: ermiyas amelga, Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule