• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሥራ ባልደረባዬ ሆይ! እንካ ስሙኒህን!!

December 27, 2019 05:27 am by Editor Leave a Comment

አንድ አሜሪካዊ የሥራ ባልደረባዬ ተሁለት ሳምንታት በፊት አለወትሮው ቆጣ ብሎ ጸጉሩን እየነጨ ሲትከነከን አገኘሁት። “ምነው በመላጣህ ምክንያት የቁንጅና ውድድር ወደክ ወይስ የቀጠርካት ጉብል ቀረቺብህ!” ብዬ ልቀልድ ብሞክርም አለወትሮው ከንፈሮቹ አልሳሳ ጥርሶችም አልታይ አሉ። ሁለቴ ጠበቅ አድርጎ “እፍፉ…” ብሎ ታምቆ የቆዬ እስተንፋስ ከተነፈሰ በኋላ “ይህ ትራንፕ እሚባል ሰው ተቀናቃኙን ለማጥቃት ስልጣኑን መጠቀሙ ቅደመ አያቶቻችን የመሰረቱትን የአሜሪካ መሰረት የሚንድ ነው!” አለና ብሶቱን ደጋግሞ ገለጠ።  

አቶ ትራንፕ ተቀናቃኛቸውን በፖለቲካ ለማጥቃት የስልክ ንግግር ማድረጋቸው ይኸንን ጓደኛዬን እንደ ሽንኩርት ቁሊት ማትከንከኑ ገርሞኝ አይኔን አፍጥጬ ሳለሁ አንድ አገራችን እሰማው የነበረ ተረት ቁልጭ ብሎ ተፊቴ ተደቀነብኝ። “ማን? መቼ? የት? ” እያላችሁ ነፍሰ-ገዳይ ገዥዎቻችሁን ጠይቃችሁ በማታውቁት ጥያቄዎች እንደ ንፍፊት አትወጥሩኝ። ተረት ነው እማወራው ብያለሁ።

አንድ ሰው መቶ ብር ይጠፋበታል። ይህ ያልታደለ ሰው በጠፋበት ገንዘብ ልቡ እንደ እባጭ ቆስሎና አንጀቱ እንደ ሰንበር ተመትሮ ወገቡን በግራ እጁ ደግፎና በቀኝ እጁ የሚንዠቀዠቀውን እንባውን እየጠረገ እናቱ የሞተችበትን ያህል ያለቅሳል። “መቶ ብር ይኸንን ያህል ያስለቅሳል?” በሚል ከንፈራችሁን እንደ እማማ የሻረግ አሸራማችሁ አታሽሟጡ። በተረቱ ጊዜ የነበረው መቶ ብር የዛሬው ግማሽ ቢሊዮን ብር ነበር። ይህ ሰው አንዴ ጎንበስ ሌላ ጊዜ ቀና እያለ፣ በእጁ አንዴ ወደ ፊት አየሩን እየገፋ፤ ሌላ ጊዜም ማጅራቱን ጠፍንጎ እየያዘ ሰፈር መንደሩ ድብልቅልቅ እስከሚል ድረስ “ኡኡኡ!” እያለ ወዮታውን ያቀልጠዋል። 

መቶ ብር የጠፋበት ሰው ኡኡታውን በሚለቅበት ሰዓት ተዚያው ሰፈር ሌላ ያልታደለ ሰው “ወይኔ ገንዘቤ! ወይኔ ንብረቴ፣ ወይ…ወይኔ!!” እያለ እንዲያውም ከመጀመሪያው ሰውዬ ይበልጥ እንደ ክረምት ዝናብ እንባውን እያዘነበ፣ ፊቱን እየነጨ አገሩን በለቅሶ ማናጋት ይጀምራል። ነጋዴ እሚበሳጨው እራሱ ስለከሰረ ሳይሆን ሌላው ስላተረፈ ነው ይባላል። ይህንን የተመለከተ መቶ ብር የጠፋበት ሰውየም “ለካስ ተእኔም የባሰ በዚች ምድር አለ!” ብሎ በመጽናናት ለቅሶውን ገታ አደረገና ወደዚህ ወደ ሁለተኛው ሰውዬ ጠጋ ብሎ “የኔ ወንድም እንዲያው ምን ያህል ገንዘብ ቢጠፋብህ ይሆን ይህንን ያህል ፊትህን የምትነጨው?” ብሎ የሚመልሰውን ለመስማት ጆሮውን እንደ ሙሰኛ ኪስ ቦርግዶ ይጠይቀዋል። ሁለተኛው ሰውየም አጽናኝ በማግኘቱ ልቡ ረጋ ብሎ ነገር ግን ሳግ እየተናነቀው “ እንደ ወርቅም… እንደ … አልማዝም የሚ..ያበራ የሰው እጅ ያልነካው ስሙኒ” ብሎ ይመልሳል። መቶ ብር ያጣው ሰውየም ቆጣ ብሎ “የኔ ወንድም እንካ ስሙኒህን! ለቅሶዬን አታበላሽብኝ!” ብሎ ሃያ አምስት ሳንቲሙን ለሁለተኛው አልቃሽ ሰጥቶ ዝም ካሰኘ በኋላ ትቶት የቆየውን ለቅሶውን እንደገና ማቅለጥ ጀመረ ይባላል።

የሥራ ባልደረባዬ በአቶ ትራንፕ ይትከነከን የነበረው የሚሊዮኖችን ነፍስ በመደዳ እንደ ትንኝ ያጠፉ፤ እግር እንደ ግንድ የቆረጡ፤ ጥፍር እንደ ስንጥር የነቀሉና ቆዳ እንደ ሌጦ የገሸለጡ አረመኔዎች ኢትዮጵያ ውስጥ በድሎት ስልጣን ተንፈላሰው በሚገኙበት ሰዓት ነው።

የሥራ ባልደረባዬ በአቶ ትራንፕ ስልክ ጥሪ ይትከነከን የነበረው በእኛዋ አገር ተላይ በተገልጡት ወንጀሎች ተሳታፊና ተባባሪ የነበሩት ጭራቆች “ተሰማይ የወረዱ ሙሴዎች!” እየተባሉ በሚመለኩበትና በሚሸለሙበት ሰዓት ነው።

የሥራ ባልደረባዬ ተራ ወንጀልም ባልተገኘባቸው የሕዝብ ተመራጭ ይትከነክን የነበረው የእርሱ አገር አስራ አምስት እጥፍ የእድሜ ታላቅ በሆነችዋ የእኛዋ አገር መንጋዎች በዘር ማጥፋት ወንጀል በቀጥታና በተዘዋዋሪ የተሳተፉትን የሂትለር ደቀመዛሙርት እንደገና እንደ ቅርቀብ ሊጫኑ ድብዳባቸውን ተጀርባቸው እያስቀመጡ ባለበት ጊዜ ነው። መስማት ላልታከተው ዝርዝሩ ብዙ ነው።፡

ስሙኒ የጠፋብህ የሥራ ባልደረባዬ ሆይ! ጩኸትህ የእኛን በርካታ ሚሊዮን ሕዝብ ያጣነውን ጩኸት እያበላሸው ነው። እንካ ስሙኒህን! ልቅሷችንን አታበላሽብን!

4/2/2012 በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule