• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሥራ ባልደረባዬ ሆይ! እንካ ስሙኒህን!!

December 27, 2019 05:27 am by Editor Leave a Comment

አንድ አሜሪካዊ የሥራ ባልደረባዬ ተሁለት ሳምንታት በፊት አለወትሮው ቆጣ ብሎ ጸጉሩን እየነጨ ሲትከነከን አገኘሁት። “ምነው በመላጣህ ምክንያት የቁንጅና ውድድር ወደክ ወይስ የቀጠርካት ጉብል ቀረቺብህ!” ብዬ ልቀልድ ብሞክርም አለወትሮው ከንፈሮቹ አልሳሳ ጥርሶችም አልታይ አሉ። ሁለቴ ጠበቅ አድርጎ “እፍፉ…” ብሎ ታምቆ የቆዬ እስተንፋስ ከተነፈሰ በኋላ “ይህ ትራንፕ እሚባል ሰው ተቀናቃኙን ለማጥቃት ስልጣኑን መጠቀሙ ቅደመ አያቶቻችን የመሰረቱትን የአሜሪካ መሰረት የሚንድ ነው!” አለና ብሶቱን ደጋግሞ ገለጠ።  

አቶ ትራንፕ ተቀናቃኛቸውን በፖለቲካ ለማጥቃት የስልክ ንግግር ማድረጋቸው ይኸንን ጓደኛዬን እንደ ሽንኩርት ቁሊት ማትከንከኑ ገርሞኝ አይኔን አፍጥጬ ሳለሁ አንድ አገራችን እሰማው የነበረ ተረት ቁልጭ ብሎ ተፊቴ ተደቀነብኝ። “ማን? መቼ? የት? ” እያላችሁ ነፍሰ-ገዳይ ገዥዎቻችሁን ጠይቃችሁ በማታውቁት ጥያቄዎች እንደ ንፍፊት አትወጥሩኝ። ተረት ነው እማወራው ብያለሁ።

አንድ ሰው መቶ ብር ይጠፋበታል። ይህ ያልታደለ ሰው በጠፋበት ገንዘብ ልቡ እንደ እባጭ ቆስሎና አንጀቱ እንደ ሰንበር ተመትሮ ወገቡን በግራ እጁ ደግፎና በቀኝ እጁ የሚንዠቀዠቀውን እንባውን እየጠረገ እናቱ የሞተችበትን ያህል ያለቅሳል። “መቶ ብር ይኸንን ያህል ያስለቅሳል?” በሚል ከንፈራችሁን እንደ እማማ የሻረግ አሸራማችሁ አታሽሟጡ። በተረቱ ጊዜ የነበረው መቶ ብር የዛሬው ግማሽ ቢሊዮን ብር ነበር። ይህ ሰው አንዴ ጎንበስ ሌላ ጊዜ ቀና እያለ፣ በእጁ አንዴ ወደ ፊት አየሩን እየገፋ፤ ሌላ ጊዜም ማጅራቱን ጠፍንጎ እየያዘ ሰፈር መንደሩ ድብልቅልቅ እስከሚል ድረስ “ኡኡኡ!” እያለ ወዮታውን ያቀልጠዋል። 

መቶ ብር የጠፋበት ሰው ኡኡታውን በሚለቅበት ሰዓት ተዚያው ሰፈር ሌላ ያልታደለ ሰው “ወይኔ ገንዘቤ! ወይኔ ንብረቴ፣ ወይ…ወይኔ!!” እያለ እንዲያውም ከመጀመሪያው ሰውዬ ይበልጥ እንደ ክረምት ዝናብ እንባውን እያዘነበ፣ ፊቱን እየነጨ አገሩን በለቅሶ ማናጋት ይጀምራል። ነጋዴ እሚበሳጨው እራሱ ስለከሰረ ሳይሆን ሌላው ስላተረፈ ነው ይባላል። ይህንን የተመለከተ መቶ ብር የጠፋበት ሰውየም “ለካስ ተእኔም የባሰ በዚች ምድር አለ!” ብሎ በመጽናናት ለቅሶውን ገታ አደረገና ወደዚህ ወደ ሁለተኛው ሰውዬ ጠጋ ብሎ “የኔ ወንድም እንዲያው ምን ያህል ገንዘብ ቢጠፋብህ ይሆን ይህንን ያህል ፊትህን የምትነጨው?” ብሎ የሚመልሰውን ለመስማት ጆሮውን እንደ ሙሰኛ ኪስ ቦርግዶ ይጠይቀዋል። ሁለተኛው ሰውየም አጽናኝ በማግኘቱ ልቡ ረጋ ብሎ ነገር ግን ሳግ እየተናነቀው “ እንደ ወርቅም… እንደ … አልማዝም የሚ..ያበራ የሰው እጅ ያልነካው ስሙኒ” ብሎ ይመልሳል። መቶ ብር ያጣው ሰውየም ቆጣ ብሎ “የኔ ወንድም እንካ ስሙኒህን! ለቅሶዬን አታበላሽብኝ!” ብሎ ሃያ አምስት ሳንቲሙን ለሁለተኛው አልቃሽ ሰጥቶ ዝም ካሰኘ በኋላ ትቶት የቆየውን ለቅሶውን እንደገና ማቅለጥ ጀመረ ይባላል።

የሥራ ባልደረባዬ በአቶ ትራንፕ ይትከነከን የነበረው የሚሊዮኖችን ነፍስ በመደዳ እንደ ትንኝ ያጠፉ፤ እግር እንደ ግንድ የቆረጡ፤ ጥፍር እንደ ስንጥር የነቀሉና ቆዳ እንደ ሌጦ የገሸለጡ አረመኔዎች ኢትዮጵያ ውስጥ በድሎት ስልጣን ተንፈላሰው በሚገኙበት ሰዓት ነው።

የሥራ ባልደረባዬ በአቶ ትራንፕ ስልክ ጥሪ ይትከነከን የነበረው በእኛዋ አገር ተላይ በተገልጡት ወንጀሎች ተሳታፊና ተባባሪ የነበሩት ጭራቆች “ተሰማይ የወረዱ ሙሴዎች!” እየተባሉ በሚመለኩበትና በሚሸለሙበት ሰዓት ነው።

የሥራ ባልደረባዬ ተራ ወንጀልም ባልተገኘባቸው የሕዝብ ተመራጭ ይትከነክን የነበረው የእርሱ አገር አስራ አምስት እጥፍ የእድሜ ታላቅ በሆነችዋ የእኛዋ አገር መንጋዎች በዘር ማጥፋት ወንጀል በቀጥታና በተዘዋዋሪ የተሳተፉትን የሂትለር ደቀመዛሙርት እንደገና እንደ ቅርቀብ ሊጫኑ ድብዳባቸውን ተጀርባቸው እያስቀመጡ ባለበት ጊዜ ነው። መስማት ላልታከተው ዝርዝሩ ብዙ ነው።፡

ስሙኒ የጠፋብህ የሥራ ባልደረባዬ ሆይ! ጩኸትህ የእኛን በርካታ ሚሊዮን ሕዝብ ያጣነውን ጩኸት እያበላሸው ነው። እንካ ስሙኒህን! ልቅሷችንን አታበላሽብን!

4/2/2012 በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule