በዶ/ር አብይ የሹመት ንግግር ውስጥ፤ ይቅርታ፣ እርቅ፣ ካሳ፣ ዲያስፖራ፣ ኤርትራ፣ ሙስና፣ ተቀናቃኝ ሃይሎች፣ የባከነ እድል፣ ስለ ዘረኝነት በሽታ እና የኢትዮጵያ ታላቅነት ተነስተዋል። “በቅጡ ሳይቧርቁ ሕይወታቸው ለተቀጠፈ ለውጥ ፈላጊ ወጣቶች ለስነ-ልቦናዊ እና አካላዊ ቀውስ ለተዳረጉ ቤተሰቦችና ግለሰቦች ከልብ የመነጨ ይቅርታ እጠይቃለሁ" ሲሉ ጀመሩ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ። በተለያየ ግዜያት መስዋዕትነትን ለከፈሉ፤ የመብት ተከራካሪዎች እና የፖለቲካ ስዎች ለደረሰው ጉዳት፣ ለፈሰሰው ደም እና ለጠፋው ህይወት፤ ይቅርታ ብቻ ብለው አላለፉም። ለተፈጠረው ችግር እልባት፤ ለተበደለ ወገን ደግሞ ካሳ እንደሚከፍሉም ተናግረዋል። “ከስህተታችን ተምረን ሃገራችንን የምንክስበት ወቅት ነው!” ማለታቸው ራሱ ንግግራቸውን በተግባር ለመተርጎም ያላቸውን ቁርጠኝነት አጉልቶ ያሳየናል። የመርህ … [Read more...] about ከዶ/ር አብይ ንግግር ትኩረት የሳቡ ነጥቦች
tplf
የዶ/ር አብይ አህመድ ፈተናዎች
እርግጥ እንደ መለስ ዜናዊ ባለ ሙሉ ስልጣን ጠቅላይ ሚኒስትር ይሆናል? ከልክ በላይ ለጥጠው፤ እንደ ልብ አንጠልጥል ፊልም ያቆዩትን ፍትግያ ትናንት በዜና ሲሰብሩት ደስታቸውን ይገልጹ የነበሩት ዜጎች ጥቂት አልነበሩም። ወትሮውን በስብሻለው ከሚለን ስራዓት አዲስ ነገር የሚጠብቅ ተስፈኛ ቢደሰት ብዙም አይደንቅም። የጠቅላይ ሚንስትር እንጂ የስራዓት ለውጥ መች ተመለከትን? ዶ/ር አብይ አህመድ በዚህ ቀውጢ ሰዓት ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኖ መመረጡ ግን ከክብሩና ከስልጣኑ ይልቅ ፈተናው ያመዝናል። ለሶስት ቀናት ተብሎ የተጀመረው ግብግብ ይሉት ክርክር በተነገረለት ቀን መቋጨት ያለመቻሉ በራሱ የሚነግረን ነገር ነበር። አወዛጋቢው የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ፣ ፓርላማ ላይ በጸደቀበት ወቅት ዶ/ር አብይ በስፍራው ባለመገኘታቸው የህወሃት ሰዎች ክፉኛ እንደተበሳጩ አይተናል። ይህንን ቅሬታ በብሎገሮቻቸውም … [Read more...] about የዶ/ር አብይ አህመድ ፈተናዎች
Ethiopia arrests 11 journalist, bloggers and activists
AHRE has found that 11 journalists, bloggers and activists arrested during the weekend, including recently released political prisoners, On March 25 2018, Ethiopian Police and Security forces arrested journalists Eskindir Nega and Temesgen Dessalege, activists Andualem Arage, Addisu Getinet, Yidnekachewu Addis, Sintayehu Chekol, Tefera Tesfaye and Woynshet Molla, and bloggers Mahlet Fantahun, Befiqadu Hailu, Zelalem Workagegnhu, and Fekadu Mehatemework, Their arrest was ordered by the Command … [Read more...] about Ethiopia arrests 11 journalist, bloggers and activists
“የክርስቲያን አገር በሆነችው ሙስሊሞች ሊነግሡባት ነው” ህወሓት ለአሜሪካ እንደራሴዎች
የአስራ ሰባት ታዋቂ ኦሮሞ ሙስሊሞችን ስም ለማስረጃነት አቅርቧል ከዝርዝሩ ውስጥ የዶ/ር አቢይ አህመድ ስም ይገኝበታል ህወሓት ከፊቱ የተጋረጠበትን የፖለቲካ ቀውስና ቀውሱን ተከትሎ ከጌቶቹ የተነሳበትን ተቃውሞና ግፊት አቅጣጫ ለማስቀየር ሃይማኖትን የተንተራሰ ስልት ተግባራዊ ማድረጉ ተሰማ። የሚካሄደው ህዝባዊ ተቃውሞ አገሪቱን ለእስልምና አክራሪ አሳልፎ ለመስጠት ያለመ እንደሆነ ህወሓት በወኪሉ በኩል ስም ዘርዝሮ አቅርቧል። የጎልጉል ዲፕሎማት የመረጃ አቀባዮች ከዋሽንግቶን ዲሲ እንዳስታወቁት ህወሓት አሁን የተነሳበትን ዙሪያ ገጠም ተቃውሞ ከእስልምና አክራሪነት ጋር በማቆራኘት የአስራ ሰባት ኦሮሞ ሙስሊም ታዋቂ ፖለቲከኞችን፣ የመብት ተሟጋቾችን፣ ወዘተ ስም ዘርዝሮ ነው ያቀረበው። ዙሪያው ገደል የሆነበት ህወሓት የስም ዝርዝሩን ባቀረበ ጊዜ ራሱን የክርስቲያን መንግሥት አድርጎ … [Read more...] about “የክርስቲያን አገር በሆነችው ሙስሊሞች ሊነግሡባት ነው” ህወሓት ለአሜሪካ እንደራሴዎች
ድምጽ የመስረቅ አባዜ
አይን እና እግር ያወጣ ውሸት ሲሰማና ሲታይ ይህ የመጀመሪያው አይደለም። "ጨፍኑ እናሞኛችሁ" አይነት ንቀት ግን አሁን ላይ ፈሩን እየለቀቀ ይመስላል። ወያኔ እንደለመደው በአደባባይ ህግ አፍርሷል። ይህ ስርዓት ራሱ ያላከበረውን ህገ-መንግስት ሌላው ሕዝብ እንዴት አድርጎ ሊያከብርለት ይችላል? ሃገሪቷን በወታደራዊ አገዛዝ ስር የሚያስገባ ሕግ ወጥ አዋጅ በተጭበረበረ ድምጽ ዛሬ አጽድቀዋል።ይህ በታሪክ መዝገብ ላይ ከሚሰፍሩ የጨለማ ቀናት አንዱ ነው። የካቲት 23 ቀን 2010 ዓ.ም፣ 122ኛው የአድዋ በዓል ከወትሮ ለየት እና ደመቅ ብሎ ተከብሯል። ይህ ቀን ለወያኔ ምኑም አልነበረም። ህወሃት የአድዋ ድል ቢቻል ባይነሳ ይመርጣል። ሃገሪቷን እየጠላ፣ ታሪኳን እያንቋሸሸ፣ ሕዝቧን እየገደለ የሚገዛ ስርዓት። ጭንቅ ሲይዘው፣ የባንዲራ ቀን ማክበር እንደጀመረ ሁሉ፣ አድዋም ዘንድሮ እንዲከበር … [Read more...] about ድምጽ የመስረቅ አባዜ
“እምቢተኛውን” ኦህዴድ በመርዝ ወይስ በመሰንጠቅ?
“ስንደመር እናሸንፋለን፣ አንድ ካልሆን እንጠፋለን” የለማ መገርሳ ተማጽንዖ!! ኦህዴድ በድንገት ያካሄደውን “ስትራቴጂክ” የተባለ የአመራር ሽግሽግ አስመልክቶ ለማ መገርሳ በሰጠው መግለጫ በተደጋጋሚ “አንድ ካልሆንን እንጠፋለን፤ ስንደመር እናሸንፋለን” ማለቱን በማስታወስ ህወሓት ኦህዴድን ለመበተን እየሠራ መሆኑን በተደጋጋሚ ለጎልጉል መረጃ የሚሰጡት የኢህአዴግ ሰዎች ተናገሩ። ወታደራዊ አገዛዙ በትሩን በኦህዴድ አመራሮች ላይ እያሳረፈ ነው። የጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የአዲስ አበባ ዘጋቢ የመረጃ ሰዎቹን ዋቢ በማድረግ እንደገለጸው የኦህዴድ መፍጠን ህወሓትን አበሳጭቷል። በድንገት ኦህዴድ ሽግሽግ ከማድረጉ በፊት የህወሓት ቅርብና ታማኝ የሚባሉ የሥራ አስፈጻሚ አባላትን አባርሯል፤ አግዷል። እንዲሁም ዝቅ በማድረግ አቅም አልባ አድርጓቸዋል። የማጽዳቱ ሥራ ጅምር እንደሆነና ወደፊትም … [Read more...] about “እምቢተኛውን” ኦህዴድ በመርዝ ወይስ በመሰንጠቅ?
Ethiopian Regime’s Misinformation Campaign On H. Res 128
FOR IMMEDIATE RELEASE Ethiopian Advocacy Network (EAN) and Ethiopian American Civic Council (EACC) would like to bring to our people’s attention a misinformation campaign aimed at thwarting the momentum of our efforts to pass H. Res 128 in the US House of representatives. It has come to our attention a high level misinformation campaign which has the hand print of the tyrannical regime in Addis is circulating false rumors to distract our people including. Deadline is postponed till … [Read more...] about Ethiopian Regime’s Misinformation Campaign On H. Res 128
ህወሓት፡ የHR 128 ፍርሃቻ እና የማግኒትስኪ ሕግ
ከዚህ በፊት በአሜሪካ ምክርቤት በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ በረቂቅ ሕግነት ከቀረቡት መካከል ህወሓት/ኢህአዴግ HR 128 እጅግ ፈርቶታል። ይህንን ረቂቅ ሕግ ለማክሸፍም የውትወታ (ሎቢ) ሥራ ከመሥራት ጀምሮ የአሜሪካ ባለሥልጣናትንና የፖለቲካ መሪዎችን በ“አልሻባብ ምስራቅ አፍሪካን ይወራል” ድራማ ለማስፈራራት ተደጋጋሚ በርካታ ሙከራዎችን ቢያደርግም አልተሳካለትም። ላለፉት በርካታ ወራትም (በቅርቡ ወደ አሜሪካ የመጡትን እነ ወርቅነህን ጨምሮ) ሊያሳምኑ ይችላሉ የሚላቸውን ሹሞቹን በመላክ ረቂቅ ሕጉ በተግባር እንዳይውል የአሜሪካ ባለሥልጣናትንን - ጊዜ ስጡን፣ ሁሉን እናስተካክላለን፣ … የመሳሰሉ ተማጽንዖዎችን ሲያቀርብ ቆይቷል። በግምባር ቀደምትነትም የህወሓት ወዳጅ የሆኑት ሴናተር ኢንሆፍ ህወሓት/ኢህአዴግን ለመታደግ ኢትዮጵያ ድረስ እስኪሄዱ ያደረሰ የውትወታ ሥራ ተካሄዷል። ይህንን ረቂቅ … [Read more...] about ህወሓት፡ የHR 128 ፍርሃቻ እና የማግኒትስኪ ሕግ
ፓርላማው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ካፀደቀ የህወሃትን ገመድ በአንገቱ ላይ በገዛ እጁ እንዳሰረ ይቆጠራል
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ፤ የህወሃት የወታደራዊ አገዛዝ አዋጅ ማለት፤ እንኳን የሰው ልጁ እንስሳትም ቢሆኑ አንገታቸው ላይ ገመድ ሊታሰር ሲል በፀጋ አይቀበሉም። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በመላ ኢትዮጵያውያን ያልተደገፈና ከውጭ አገራትም ሆነ ከአለም አቀፍ ድርጅቶችም ጠንካራ ተቃውሞ የተነሳበት መሆኑ በሚገባ ይታወቃል። የአዋጁ ዋና ዓላማ ህወሃት በኢትዮጵያ ሕዝብ የተነሳበትን ተቃውሞ ለመጨፍለቅ፤ በኦህዴድና ብአዴን እየተነሳ ያለውን የፍትህና የእኩልነት ጥያቄ ትግልን ለማጨናገፍ፤ ኦህዴድና ብአዴን የህወሃትን የበላይነት ለማስወገድ ከክልላቸው ሕዝብ ጋር ተቀራርበው ለመስራት የሚያደርጉትን ጥረት ለማደናቀፍ እና ለህወሃቶችና ለሸሪኮቻቸው አገሪቷን የመዝረፍ ዘመቻቸውን በስፋት የሚቀጥሉበትን መንገድ ለማረጋገጥ ነው። ይህ አዋጅ የአገር ወይም የሰፊው ሕዝብ ደህንነት አዋጅ ሳይሆን የጥቂቶችን የበላይነት … [Read more...] about ፓርላማው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ካፀደቀ የህወሃትን ገመድ በአንገቱ ላይ በገዛ እጁ እንዳሰረ ይቆጠራል
የአስቸኳይ ግዜ አዋጁ እና የህወሓቶች አሻጥር (የሰነድ ማስረጃ)
ጥቅምት 03/2010 ዓ.ም በተለያዩ የኦሮሚያ አከባቢዎች የተቃውሞ ሰልፍ ተካሂዶ ነበር። በወቅቱ “ይህን የተቃውሞ ሰልፍ ማን ነው የሚያስተባብረው?” የሚለው ጥያቄ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኖ ነበር። በውጪ የሚገኙ የኦሮሞ ልሂቃን የተቃውሞ ሰልፉን እንዳልጠሩ ሲገልፁ ነበር። በተመሳሳይ አዲሱ የኦህዴድ አመራር በጉዳዩ ዘሪያ እጁ እንደሌለበት መግለፁ ይታወሳል። በእርግጥ ሰልፈኞች ከወትሮ በተለየ መልኩ የኦነግን ባንዲራ ይዘው ታይተዋል። በአንፃሩ የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ደግሞ ምንም ዓይነት አመፅና ሁከት እንዳይቀሰቀስ ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል ሲያደርግ ነበር። እኔ በግሌ ከታች የሚታየውን ፎቶ ሳነሳ ፖሊሶች ስልኬን ቀምተውኝ የነበረ ሲሆን ማንነቴን ከአጣሩ በኋላ ነው የመለሱልኝ። በሌላ እንደ ዳኒኤል ብርሃኔ ያሉ ቀንደኛ የህወሓት ደጋፊዎች “የተቃውሞ ሰልፉ እየተመራ ያለው ከተጠበቀው በላይ ትልቅ … [Read more...] about የአስቸኳይ ግዜ አዋጁ እና የህወሓቶች አሻጥር (የሰነድ ማስረጃ)










