“አሁን አሜሪካኖቹ እያመረሩ ነው” የሚለው ዜና አየሩን ወጥሮታል። በተለይም የኦባማ አስተዳደር ለኢህአዴግ/ህወሃት የጻፈው የከረረ ደብዳቤና ትዕዛዝ ለአገዛዙ የመቀመጫ ላይ ቁስል ሆኖበታል። ለዚህም ይመስላል ሃይለማርያም ሳይፈልጉ መለስን እንዲሆኑ ታዝዘው አሜሪካንን ወርፈዋል። ይኸው የሃይለማርያም ዘለፋ ያበሳጫቸው የስቴት ዲፓርትመንት ኃላፊዎች “ሰዎቹ ከማን ጋር እንደሚያወሩም አያውቁም። ደቡብ ሱዳን መሰልናቸው” ማለታቸውን የመሰክሩ ለጎልጉል ገልጸዋል። ይህንኑ ተከትሎ ሃይለማርያም ደሳለኝ ባስቸኳይ አሜሪካ እንዲመጡ ታዝዘዋል። በወቅታዊው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ቀውስ ዙሪያ የአሜሪካ መንግስት ከህወሃት/ኢህአዴግ ጋር እያደረገ ያለውን ግንኙነት በቅርብ የሚከታተሉና በቂ መረጃ ያላቸውን በመጠቀስ የጎልጉል የአሜሪካ ዜና አቀባይ እንደዘገበው፣ የኦባማ አስተዳደር የጻፈው ደብዳቤ ሃይለማርያምን … [Read more...] about አሜሪካ ስለ ህወሃት – “እጃችንን ብናነሳ በህይወት አይኖሩም”
Middle Column
ጥልቅ ተሃድሶ “በመበስበስ” ጀመረ!
የኢህአዴግ አካል የሆነው ኦህዴድ “ጥልቅ ተሃድሶውን” “በመበስበስ” መጀመሩን የኢህአዴግ ንብረትና የንግድ ተቋም የሆነው ፋና ብሮድካስቲንግ ያሰራጨው ዜና አመልክቷል፡፡ ዜናውን ተከትሎ “በጥልቀት የመታደሱ” ጉዳይ “በመበስበስ” መጀመሩ አመላካች ነው ተብሏል፡፡ በሌሎች ክልሎችም የመበስበስ መጠናቸው የጠለቀና ለህወሃት ከመታመን ውጪ ተስፋ በሌላቸው ታማኞች በመተካት ሹምሽር እንደሚቀጥል ይጠበቃል፡፡ የኦህዴድ ምክትል ሆነው የተሾሙት ጄኔራል፣ ዶክተር፣ አቶ፣ አሁን ደግሞ ምክትል ሊቀመንበር ሆነው ብቅ ያሉት የኦሮሞን ብሔር የማይወክሉ የትግራይ ተወላጅ እንዶኑ በስፋት የሚነገርላቸው ሻሸመኔ ያደጉት ወርቅነህ ገበየሁ ናቸው፡፡ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ “ወርቅነህ ገበየሁ ለምን ወደ ትራንስፖርት ሚኒስትርነት?” በሚል ርዕስ (July 6, 2013) ስለ ወርቅነህ ገበየሁ “ነገዎ” መጠነኛ ዘገባ … [Read more...] about ጥልቅ ተሃድሶ “በመበስበስ” ጀመረ!
“እኛ ዝናብ ነው ‘ሚወርድብን ያገሬ ልጆች ግን ደማቸው እየፈሰሰ ነው” የ1 ዓመት ህጻን እናት
ከዋሽንግተን ዲሲና ከአካባቢው እንዲሁም ከተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች የመጡ ኢትዮጵያውንና ኢትዮጵያውያን አሜሪካውያን በዛሬው እለት በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት፣ በዋይት ሃውስ እና በዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት ደጃፎች የተቃውሞ ሰልፍ አካሄዱ። ሕጻናት የያዙ እናቶችና አዛውንቶች ጭምር የነበሩበት እጅግ የበዛ ቁጥር ያለው ሰላማዊ ሰልፈኛ ከማለዳው አንስቶ ነው “በዚያች አገር እየተካሄደ ነው” ያለውን ግድያ “በአፋጣኝ አስቁሙ!” እና “ለመንግስቱ የምትሰጡትንም እርዳታ አቋረጡ” የሚሉ ጥያቄዎችን ላቀረበላቸው የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ባለሥልጣናትና የምክር ቤት አባላት ሲያሰማ የዋለው። ሳያቋርጥ ቀኑን በዘለቀው ካፊያ ውስጥ ከውጭ ጉዳይ ሚንስቴር መሥሪያ ቤት ወደ በዋይት ሃውስ አልፎ ከምክር ቤት የሚያደርሱትን የከተማይቱን ጎዳናዎች ሞልቶ ሲሰማ የዋለውን … [Read more...] about “እኛ ዝናብ ነው ‘ሚወርድብን ያገሬ ልጆች ግን ደማቸው እየፈሰሰ ነው” የ1 ዓመት ህጻን እናት
“ይቺ ሀገር እንደ ሀገር እንድትቀጥል ከተፈለገ እኛ አድማጭ እናንተ ተናጋሪ የምትሆኑበት አካሄድ ማክተም አለበት”
በዩኒቨርሲቲው የቦርድ ሊቀመንበር አቶ ካሳ ተ/ብርሀን አጠቃላይ የውይይት መድረኩ መነሻ አሳብ ትረካ እና የእለቱ የውይይት አጀንዳ በሆነው ያለፉት 25 ዓመታት የትምህርት ጥራትና ተደራሽነት ጉዞ ዙሪያ የሚያጠነጥን ገለፃ በኋላ በምርጦቹ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን የተነሱ አስተያቶች እና የአካሄድ ጥያቄዎች:- 1. የመጀመሪያ ተናጋሪ፡- 1.1 “የዚህ ወይይት አጀንዳ ከጠበኩት በታች ወርዶብኛል በወላይቲኛ አንድ አባባል አለ - ያቺ እንትን'ኮ ወደቀች ቢሏት፤ ቀድሞም አቀማመጧ ለመውደቅ ነው አለች”፡፡ 1.2 “ካሳ! አንተ ሚኒስትር ነህ በዛ ላይ የዩኒቨርሲቲያችን የቦርድ ሊቀመንበር በዚህ ሁሉ ኃላፊነት ውስጥ ሆኖ PhD candidate መሆን አይቻልም ስለዚህ ስራህን ልቀቅ” 1.3 “ጠቅላይ ሚኒሰትሩ ይምጣና ያወየን፣ እናንተ ውረዱና ከእኛ ጋር ተቀመጡ” 2. ሁለተኛ ተናጋሪ … [Read more...] about “ይቺ ሀገር እንደ ሀገር እንድትቀጥል ከተፈለገ እኛ አድማጭ እናንተ ተናጋሪ የምትሆኑበት አካሄድ ማክተም አለበት”
የተወጠረችው አዲስ አበባ ታስፈራለች – ብሶት ይንፈቀፈቅባታል!!
እድሜው አርባዎቹን ስለመሻገሩ ገጹ ይናገራል። በተፈጥሮ ያለው እርጋታ አዲስ አበባ ካጋጠመው ትንግርት ጋር ተዳምሮ አፍዞታል። ፊቱን ፈገግ የሚያደርገው ስለ አዲስ አበባ አራዳዎች ሲናገር በቻ ነው። ጨዋታውን የጀመረው በጫማ አሳማሪዎች ነበር። ጫማ አሳማሪዎች ደረጀ ወጥቶላቸዋል። “የታቀፉና ያልታቀፉ” ሁሉንም ገጠመኞቹን ሲያስረዳ “አዲስ አበባ እንደ ወበቅ ነች” ይላል። የወበቅ ጭንቀት የሚለቀው በደንብ ሲዘንብና አየሩን አፍኖ የያዘው ደመና ሲገፈፍ ነው። ወበቅ ለሱ በሽታ ነው። ነዋሪነቱ አውሮጳ ሲሆን አዲስ አበባ የከረመበት ምክንያት ቤት ቢጤ ስላለው እሱኑ ሸጦ ለአንዴና ላልተወሰነ ጊዜ የሚወዳትን “ወበቃም” ከተማ ለመለየት ነው። ቦሌ ፒኮክ ቁጭ ብለን ስናውጋ ቀድሞ አደራ ያለኝ ፊቱ ማስታወሻ አውጥቼ የሚነግረኝን እንዳልጽፍ ነው። ለወትሮም ቢሆን ስለማላደረርገው ተስማማሁና አወጋን። … [Read more...] about የተወጠረችው አዲስ አበባ ታስፈራለች – ብሶት ይንፈቀፈቅባታል!!
“ህወሃቶች – ምንድነው የሚፈልጉት? ደም አይጠግቡም?”
“ሊገባኝ አልቻለም” ሲሉ ይጀምራሉ። በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው የጅምላ ጭፍጨፋ ረፍት እንደነሳቸው ያስረዳሉ። አገሪቱ በደም እየታጠበችና በቂም እየነፈረች ጥቅም ህሊናና አእምሯቸውን ስለዘጋባቸው “ዜጎች” ማሰብ ለበሽታ አጋልጧቸዋል፤ ያነባሉ። ግራ በመጋባት “ህወሃቶች - ምንድነው የሚፈልጉት? ደም አይጠግቡም?” በማለት ይጠይቁና አጭሩን መልዕክት “ከርስ እንደዚህ እውር ያደርጋል?” የሚል ጥያቄ ጠይቀው ይሰናበታሉ። “በጥልቅ ስንታደስ የጥፋት ሃይሎች ጊዚያዊ መነቃቃት ይከስማል” ሲል የአዲስ አበባ ኢህአዴግ ጽ/ቤት በህዳሴ ጋዜጣ ላይ ያሰፈረውን አመልክተው፣ “በፍጥነት ወደ ጥልቁ ብትገቡ ለአገሪቱ ዘላለማዊ መነቃቃት ይሆን ነበር” የሚል ርዕስ በመስጠት ከላይ በመግቢያ የተገለጸውን የጠቆሙት የሃዋሳ ነዋሪ መሆናቸውን የጠቆሙ ደንበኛችን ናቸው። ብዙዎች እንደሚስማሙት ራሱን … [Read more...] about “ህወሃቶች – ምንድነው የሚፈልጉት? ደም አይጠግቡም?”
“ሕዝቡ እኔን አይቶ መታረቅ አለበት” ፈይሣ ሌሊሣ
አትሌት ፈይሣ ሌሊሣ ዛሬ በፌሰቡክ ከጋቢና ቪኦኤ ጋር የቀጥታ ውይይት አካሂዷል፡፡ ስላሳ ደቂቃ አካባቢ በፈጀው ቆይታው ከፕሮግራሙ ተከታታዮች ለቀረበለት ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ሕወሃት ደንቁሯል እንጂ ከዚህ በላይ መልዕክት አያስፈልገውም ነበር፡፡ ዜግነቱን ለመቀየር ሃሳብ እንደሌለውና ራሱን ጀግና ብሎ እንደማይቆጥር የተናገረው ፈይሣ ለትግራይ ተወላጆች፣ ትግራዮችን በትግሬነታቸው ለሚጠሉ፣ ለትግራይ ወጣቶች፣ በሥልጣን ለሚገኙት ግፈኛ የህወሃት ባለሥልጣናት፣ ለነ ኃይሌ ገ/ሥላሴና መሰል አንጋፋ አትሌቶች፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ለወጣቶች፣ … እስኪበቃው ተናግሯል፡፡ የሰላም ታጋይና ዕርቅ ወዳድ የሆነው ፈይሣ ስለ ዕርቅም በሚገባው ሁኔታ አስረድቷል፡፡ በአማርኛ ያደረገውን ሙሉውን ቃለምልልስ እዚህ ላይ መመልከት ይቻላል፡፡ በአፋን ኦሮሞ ያደረገው ቃለምልልስ እዚህ ላይ … [Read more...] about “ሕዝቡ እኔን አይቶ መታረቅ አለበት” ፈይሣ ሌሊሣ
መልዕክት ለመምህራን
እንደሚታወቀው ከቅርብ ቀናት በፊት ከመስከረም 4 ጀምሮ የሚሰጠውን የመምህራን ስልጠና በምን መልኩ ወደ ተቃውሞ መድረክ መቀየር እንደምንችል መምህራኖችን መጠየቃችን ይታወሳል። መምህራኖችም ግልፅ በሆነ ቋንቋ ሀሳባቸውን ገልፀውልናል። ለዚህም ልናመሰግናቸው እንወዳለን። እኛም ሀሳባቸውን ጨምቀን አቅርበናል። ከዛ በፊት ግን ይህንን ስብሰባ መቃወም ለምን እንደሚያስፈልግ መግለፁ ተገቢ ነው። 1) ይህ ስብሰባ መምህራን ሙያቸውን የሚያሻሽሉበት ሳይሆን ገዥው ፖርቲ የራሱን ፕሮፖጋንዳ የሚነዛበት የፖለቲካ መድረክ ነው። ይህንን ደግሞ ከዚህ በፊት ከነበረው ልምድና ለስልጠናው ከተዘጋጁት ማኑዋሎች መረዳት ይቻላል። ስለዚህ ከዚህ ስልጠና ለመማር ማስተማሩ ሂደት የሚጠቅም አንዳች ነገር አይኖርም። 2) ወያኔ የሀገሪቱን የፖለቲካ ቀዉስ በውይይት ሳይሆን በመሳሪያ ለመፍታት ወስኗል። ይህንን ምርጫም … [Read more...] about መልዕክት ለመምህራን
የሰማዕታት ዝርዝር በከፊል
Partial list of Oromos that have been killed as a result of Excessive force by Ethiopian Government (TPLF's regime) armed forces during Peaceful demonstration on August 6,2016, Oromia, Ethiopia. (updated 4 September 2016) Nr Name Sex Age Zone Locality Killed by 1 Abbuu Muummee M 17 Arsii Ticho Agazi 2 Abdallaa Mohammed M - East Harageh Qobo Agazi 3 Abda Jiloo M 24 West Arsii Asasa Agazi 4 Abdaa Hasanoo M 31 West … [Read more...] about የሰማዕታት ዝርዝር በከፊል
#ተቃውሞ #እምቢተኝነት #ተጋድሎ
እንባ እንባ ይለኛል ይተናነቀኛል እንባ ከየት አባቱ ደርቋል ከረጢቱ: ሳቅ ሳቅም ይለኛል ስቆ ላይስቅ ጥርሴ ስቃ እያለቀሰች መከረኛ ነብሴ:: (በአሉ ግርማ “ኦሮማይ”) ምነው! ፈጣሪ አምላክ! አላለቅስም ያልኩት ... እንባ የፈሪ ነው ብዬ ዋጥ ያ’ረኩት፣ አይቻል ተችሎኝ ይዤው የከረምኩት፣ ገንፍሎ ወጣና እንባዬ ፈሰሰ ጉንጮቼን ሰንጥቆ ፌቴን አዳረሰ በዛ እንባዬ መሀል አንገቴን አቅንቼ ለፈጣሪ ጮኽኩኝ! እጆቼን ዘርግቼ ምነው? ፈጣሪ አምላክ ምነው! ረሳኸን ምነው! ይሄን በደል አላይልን አልከን ምነው? የኛን ጩኸት ሰምተህ ጨከንክብን ብዬ ወተውትኩት አልኩበት እዬዬ አሁንም ይፈሳል አልቆመም እንባዬ ምነው! ፈጣሪ አምላክ! ... ወለላዬ የዛሬ 25 ዓመት ህወሃት የጀመረው በዚህ ነበር - … [Read more...] about #ተቃውሞ #እምቢተኝነት #ተጋድሎ










