• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሕዝቡ እኔን አይቶ መታረቅ አለበት” ፈይሣ ሌሊሣ

September 15, 2016 11:01 pm by Editor Leave a Comment

አትሌት ፈይሣ ሌሊሣ ዛሬ በፌሰቡክ ከጋቢና ቪኦኤ ጋር የቀጥታ ውይይት አካሂዷል፡፡ ስላሳ ደቂቃ አካባቢ በፈጀው ቆይታው ከፕሮግራሙ ተከታታዮች ለቀረበለት ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ሕወሃት ደንቁሯል እንጂ ከዚህ በላይ መልዕክት አያስፈልገውም ነበር፡፡

ዜግነቱን ለመቀየር ሃሳብ እንደሌለውና ራሱን ጀግና ብሎ እንደማይቆጥር የተናገረው ፈይሣ ለትግራይ ተወላጆች፣ ትግራዮችን በትግሬነታቸው ለሚጠሉ፣ ለትግራይ ወጣቶች፣ በሥልጣን ለሚገኙት ግፈኛ የህወሃት ባለሥልጣናት፣ ለነ ኃይሌ ገ/ሥላሴና መሰል አንጋፋ አትሌቶች፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ለወጣቶች፣ … እስኪበቃው ተናግሯል፡፡ የሰላም ታጋይና ዕርቅ ወዳድ የሆነው ፈይሣ ስለ ዕርቅም በሚገባው ሁኔታ አስረድቷል፡፡

በአማርኛ ያደረገውን ሙሉውን ቃለምልልስ እዚህ ላይ መመልከት ይቻላል፡፡

በአፋን ኦሮሞ ያደረገው ቃለምልልስ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡

ከተናገራቸው በጥቂቱ፤

“ሰው በጅምላ እየተገደለ፣ እየታሰረ ነው፤ ይህንን አይቼ ነው የተቃወምኩት”

“ለሕዝብ ብዬ ነው ተቃውሞ ሰማሁት፤ ለራሴ ጥቅም አይደለም፤ ጥሩ ኑሮ አለኝ፤ …”fayissa

“ሕዝብ የሥልጣን ባለቤት እንዲሆን ነው ምኞቴ”

“ይህ ሥርዓት ተቀይሮ ለአገራችን ብሮጥ ደስ ይለኛል እንጂ ለየትም አገር መሮጥ አልፈልግም፤ ዜግነቴን አልቀይርም”

“አንድ ቀን ወደ ኢትዮጵያ ተመልሼ እንደምሮጥ ነው ተስፋ የማደርገው”

“ሕዝቡ እኔን አይቶ መታረቅ አለበት”

“ጀግንነት አይሰማኝም፤ ጀግና አይደለሁም፤ የዜግነት ግዴታዬን ነው የተወጣሁት”

ለነኃይሌ ገ/ሥላሴ፤

“እነኃይሌ … ስለ ሪዮ ሲነጋገሩ ነበር፤ … አሁን የምንነጋገረውና የምናስበው ስለሜዳሊያ አይደለም፤ … ስለ አገራችን ስለ ህዝባችን ለምን አይሰማንም”

“ሕዝብ እየተገደለ፣ እየሞተ እንዴት ስለ ሕዝብ አናስብም”

“እናንተ (አንጋፋ አትሌቶች) ሕዝብንና መንግሥትን ማገናኘት ትችላላችሁ”

ለህወሃት ኃላፊዎች፤

“ብዙ ሃብታም መሆን ይጎዳል፤ ለህዝባችሁ አስቡ፤ ለራሳችሁ ጥቅም ብላችሁ አገራችንን ከማፍረስ ብትቆጠቡ ደስ ይለኛል”

ለትግራይ ተወላጆች፤

“ከኦሮሞ፣ ከአማራ፣ ከጋምቤላ ሕዝብ ጋር ሆነው ይህንን ሥርዓት መቃወም አለባቸው፤ ሕዝቡን መደገፍ አለባቸው”

በአጠቃላይ፤

“የአንድ ብሔር የበላይነት (የትግራይ) አለ፤ግን ብዙም አይደለም፤ የተወሰኑ ሰዎች ናቸው፤ ትግሬ ሆኖ ደሃ አለ – የሚለምኑ ትግሬዎች አይቻለሁ”

“የኢትዮጵያ ሕዝብ በትግሬ ቅር ብሎታል”

“እኔ ትግሬ አልጠላም፤ … ጓደኞቼም አሉ፤ … ትግሬዎችን ግን የሚጠሉ አሉ፤ የሚሳደቡ አሉ፤ (ይህንን) ከማድረግ እንዲቆጠቡ ልንግራቸው እፈልጋለሁ”

“እኛ አንድነት ነው የምንፈልገው፤ ይህ መንግሥት ይወድቃል፤ ስለዚህ እነርሱ ሰዉን እንዳያስከፉ”

“(ወጣቶች) በሰላማዊ መንገድ ትግል መቀጠል አለባቸው፤ ሞትም ቢሆን ለትውልድ ነጻነት ሰጥቶ መሞት ነው፡፡”


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule