ከሕገወጥ ፍልሰት ጋር በተያያዘ የአውሮጳ ኅብረት የአስቸኳይ ጊዜ መተማመኛ ድጎማ (Emergency Trust Fund - ETF) በማለት ለኢትዮጵያ የመደበው ገንዘብ ወደ ህወሃት ኮሮጆ እንደማይገባ ተነገረ፡፡ በኢትዮጵያ እየተባባሰ የመጣው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰትን እንደምክንያት በማድረግ ድጎማው እንዲከለስ ወይም እንዲሰረዝ ዩሮአክቲቭ ያቀረበው ጥያቄ ለመረጃው ይፋ መሆን ምክንያት ሆኗል፡፡ አንድ ጊዜ በቃል በሌላ ጊዜ ደግሞ በኢሜይል ከኅብረቱ በኩል የተሰጠው መረጃ የኅብረቱን የድጎማ አከፋፈል በተመለከተ የጠራ አቋም የማያሳይ ድንግዝግዝ መረጃ ሆኗል፡፡ በህገወጥ መንገድ ከአፍሪካ የሚፈልሱት ዜጎች የአውሮጳውያን መንግሥታት ራስምታት ከሆኑ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የፍልሰት መጠኑ መጨመሩና ከዚያ ጋር ተያይዞ የሚጠፋው የሰው ህይወት አውሮጳውያኑን በስፋት ያነታረከ ነው፡፡ … [Read more...] about የአውሮጳ ኅብረት ድጎማ ህወሃት ኮሮጆ አይገባም
Middle Column
ቂሊንጦ – “የተረሸኑት” እነማን ናቸው?!
“ወይኔ ልጄ፣ እጅ እግሬ ልጄ፣ ወይኔ ልጄ፣ ወዴት ነህ ልጄ፣ የት ላግኝህ ልጄ? እምኑ ጋር ነህ? ልጄ … ልጄ … ልጄ … ልጄ …” ጥቁር ቦርሳቸውን በወገባቸው ተሸክመው፣ ቂሊንጦ እስር ቤት ደጅ የሚያነቡ እናት ለቅሶ!! ሁሉም ያነባሉ። ሁሉም ያለቀሳሉ፣ የሚሰማ ግን የለም። እንደውም “ዘወር በሉ” እየተባሉ ይደገንባቸዋል። “ሊታረሙ በህግ ከለላ ስር ሆነዋል” የተባሉ ወገኖች “ተረሽነዋል” የሚለው አስተሳሰብ እየጠነከረ መጥቷል። ለቤተሰቦቻቸው እንደምን ተቆጥረው ይሁን? ይህ ሁሉ የጭካኔ ግፍ ወዴት ይመራን ይሆን? የብዙዎች ጥያቄና ስጋት ነው። በየሰዓቱ የሚወጡት መረጃዎች ደግሞ ስጋቱን የሚያግሉና ቁጣን የሚቀሰቅሱ ሆነዋል። የህወሃት ሹሞችም “የሆነው ነገር ሁሉ የተከሰተው በዕቅድ አይደለም” ይላሉ፡፡ በአልሞት ባይ ተጋዳነት የሚውተረተረው ህወሃት አሁንም አለሁ ቢልም የቂሊንጦ ጉዳይ … [Read more...] about ቂሊንጦ – “የተረሸኑት” እነማን ናቸው?!
“የገደሉት ልጄ አስከሬን ላይ ቁጭ በይ ብለው ደበደቡኝ” ደምቢ ዶሎ የተገደለ ወጣት እናት
በቄለም ወለጋ ዞን ደምቢዶሎ ከተማ ውስጥ ትናንት ማክሰኞ ማምሻው ላይ ከመንግሥት ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉን የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ። የአንደኛው ወጣት ወላጅ እናት እኔንም የልጄ አስከሬን ላይ ጥለው ደበደቡኝ ብለዋል። በመንግሥት ታጣቂ ጥይት ህይወታቸው ያለፈው ሁለቱ ሃይሉ ኤፍሬም እና ኢብሳ ሩንዴ የሚባሉ ሲሆኑ የ16 ዓመቱ ወጣት ሃይሉ ኤፍሬም ከተማዋ ውስጥ ተኩስ በመከፈቱ ከሌሎች ጓደኞቹ ጋር ከተኩሱ ለማምለጥ ሲሮጥ መትተው ገደሉት ሲሉ የከተማዋ ነዋሪዎች ገልጸዋል። “ደሞቢ ዶሎ መሃል ከተማ ነበር ተኩስ የተጀመረው። ወደ ቀበሌ ዜሮ አምስት አካባቢም ተኩስ ነበር ። ልጆቹን እያባረሩዋቸው ሲመጡ ወጣት ሃይሉ ኤፍሬም በቅጽል ስሙ ቦጌ ነው የሚባለው ቀበሌ ዜሮ ሰባት በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ አቅራቢያ ነው የተገደለው” ብለዋል የአሜሪካ ድምፅ … [Read more...] about “የገደሉት ልጄ አስከሬን ላይ ቁጭ በይ ብለው ደበደቡኝ” ደምቢ ዶሎ የተገደለ ወጣት እናት
የኢኮኖሚ አድማ!
በ#OromoProtests አስተባባሪዎች በተሰጠው ማሳሰቢያ መሠረት በኢኮኖሚ ላይ ያተኮረው የገበያ ማቆም አድማ እየተካሄደ ነው፡፡ በፎቶዎቹ ላይ እንደሚታዩት ከንጋት ጀምሮ የአምቦ አካባቢ ከተማ፣ ሻሸመኔ አዋሾ ክፍለ ከተማ፤ አሳሳ፣ ጉደርና ከተሞች ከነገበያቸው ባዶ ሆነዋል፡፡ ዓድማው በሌሎችም ከተሞች ላይ ሲካህይድ የዋለ ሲሆን በውጤቱም የህወሃትን የገቢ ኮሮጆ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚጎዳው ይገመታል፡፡ ከአስተባባሪዎቹ የተሰጠውና እስከ መስከረም 2 የሚዘልቀው ማሳሰቢያ እንዲህ ይነበባል፤ ማሳሰቢያ: የገበያ ማቆም አድማ በመላው ኦሮሚያ ነገ ጳግሜን 1 እንደሚጀምር አስቀድመን መግለጻችን ይታወቃል፡፡ ይህ አድማ እስከ መስከረም ሁለት ይቀጥላል። በዚህ አድማ ጊዜ ውስጥ ከሌሎች ክልሎች ለሽያጭ እቃዎችን ወደ አዲስ አበባ እና ሌሎች የኦሮሚያ ከተሞች ማስገባት ክልክል ነው። እቃዎችን ጭነው … [Read more...] about የኢኮኖሚ አድማ!
“… መብከት፣ መበስበስ ከአንዴ በላይ ይደብራል …” ሕዝብ
ከመተካካት አልፈው ራሳቸውን "recycle" ያደረጉትን የህወሃት/ኢህአዴግ ሹሞች ያካሄዱትን ውይይትና የሕዝቡን አስተያየት የጀርመን ድምጽ ሬዲዮ ዘግቧል - "የኢህአዴግ ከፍተኛ ባለስልጣናትና የኢትዮጵያ ሁኔታ" በሚል ርዕስ የታተመው ዘገባ እንዲህ ይነበባል:- ኢትዮጵያን የሚመራዉ የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) በቅርቡ ካካሔደው ግምገማ በኋላ በሥራ አስፈጻሚዎቹ ዘንድ ሹም ሽር ሊያካሂድ መሆኑን እየተናገረ ነው። የገዢው ግንባር ሹም ሽርም ይሁን ግምገማ ግን ለውጥ ለማምጣቱ በርካቶች ጥያቄ አላቸው። ከሩብ ምዕተ-ዓመት በላይ በስልጣን ላይ የቆየው የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ከገባበት አጣብቂኝ ለመውጣት ተሿሚዎቹን ሊገመግም እንደሆነ አስታውቋል። ከጠቅላይ ሚንስትር ሐይለ ማርያም ደሳለኝ አማካሪዎች መካከል አቶ አባይ ፀኃዬ … [Read more...] about “… መብከት፣ መበስበስ ከአንዴ በላይ ይደብራል …” ሕዝብ
የቂሊንጦ እስር ቤት ቃጠሎ ለህወሃት ፈተና ተጨማሪ ነዳጅ ሆነ!!
የኢትዮጵያ ፖለቲካ ቀውስ ከቀን ወደቀን እየጋመ ነው። ህወሃት ችግሮችን በሰከነ መንፈስ ከመፍታት ይልቅ ክተት አውጆና ንጹሃንን እየፈጀ ይገኛል። ሥልጣን ከያዙ ጀምሮ የረባ ትዕዛዝ ሰጥተው የማያውቁት ሃይለማርያም “አዝዣለሁ" ሲሉ በወገኖቻቸው ላይ ሞት አውጀው ቀውሱን አግመውታል። አፍቃሪ ህወሃቶችም የ“ቅምጡን ባሪያ ጠቅላይ ሚኒስትር” “ትዕዛዝ” ተከትለው “ትዕግስትም ገደብ አለው” እያሉ በየሚዲያውና በማህበራዊ ገጾች እያሽካኩ ነው። ሕዝብ “መሳሪያ አጣን” እያለ ጥሪ እያቀረበ ነው። ያም ሆኖ ምሬት የገፋቸው ሁሉ አመጹን ገፍተውበታል። በከፋፍለህ ግዛ የፖለቲካ ቁማር ህዝብ እያናከሰ ላለፉት 25 ዓመታት አገር ሲገዛ የኖረው ህወሃት ዛሬ አደረጃጀቱና “አጋሬ” የሚላቸው የተለዩት ይመስላሉ። ኦህዴድ ከተናጋና ከከዳ ሰንብቷል። ብአዴንም መመኪያ ሊሆን የማይችልበት ደረጃ ደርሷል። ለዚህም … [Read more...] about የቂሊንጦ እስር ቤት ቃጠሎ ለህወሃት ፈተና ተጨማሪ ነዳጅ ሆነ!!
“የባንኮች የመተርከክ (hack የመደረግ) ሽብር” አገሪቷን እንዳያናውጥ ተሰግቷል
ህወሃት/ኢህአዴግን በየቦታው እየናጠው ያለው ተቃውሞ በኢትዮጵያ የገንዘብ ቀውስ ሊያስከትል ይችላል የሚል ግምት ተሰጥቶታል፡፡ ችግሩ ባንኮች ላይ የገንዘብ እጥረት እንደሚያስከትልና ባንኮችን ሽብር ውስጥ ሊከታቸው እንደሚችል በስፋት እየተነገረ ነው፤ ደምበኞች ስለገንዘባቸው የሚጠነቀቁበት ጊዜ አሁን ነው፡፡ ህዝባዊ ቁጣ ያሰጋቸው የአገዛዙ ተጠቃሚዎች የውጭ ምንዛሬ እየሰበሰቡ ሲሆን በፍርሃቻ ንብረት በማስያዝ ከባንክ የሚበደሩት ክፍሎች ቁጥርም በርካታ ሆኗል። ከ10 ወራት በላይ ያስቆጠረውና ለተጨማሪ የኢኮኖሚ ማዕቀብ ቀን የቆረጠው የኦሮሞ ህዝባዊ እምቢተኛነት (#OromoProtests) ያስከተለውን መንኮታኮት ህወሃት በይፋ ባያሳውቅም በግብር አሰባሰብ፣ በውጭ ምንዛሬ፣ በጠቅላላ የውጭና የውስጥ ንግድ የገቢ ስርዓቱን እንዳናጋው ከፋይናንስ ተቋማት የተገኙ መረጃዎች ያመለክታሉ። ይህ እንግዲህ … [Read more...] about “የባንኮች የመተርከክ (hack የመደረግ) ሽብር” አገሪቷን እንዳያናውጥ ተሰግቷል
ህወሃት/ኢህአዴግ በአማራው ሕዝብ ላይ የዘር ዕልቂት (genocide) አወጀ
በአማራ ክልል እየተቀጣጠለ የመጣውን ሕዝባዊ እምቢተኝነት (#AmharaResistance) ፖለቲካዊ መፍትሔ ከመፈለግ ይልቅ የመከላከያ ኃይል እርምጃ እንዲወስድ ሃይለማርም ደሳለኝ በኦፊሴል አዟል፡፡ በትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) ሙሉ ቁጥጥር ሥር ያለው የሃይለማርያም የጠቅላይ ሚኒስትርነት ሥልጣን በየቦታው “በቃን፤ አንፈልግም” የተባለውን የህወሃት የበላይነትን እንደገና ለማስፈን የጦርነት አዋጅ አውጇል፡፡ በኦሮሚያ (#OromoProtests) ለ10 ወራት የዘለቀው የኦሮሞን ሕዝብ የመፍጀት ሥልታዊ ጥቃት አሁንም የበርካታዎችን ደም እያፈሰሰ ባለበት ባሁኑ ወቅት በአንድ ክልል ሕዝብ ላይ የተነጣጠረው ይህ በሃይለማርያም ትዕዛዝ የተሰጠው የህወሃት እርምጃ ታሪክ የማይረሳው፣ ሰላም ሊያመጣ የማይችል፣ የዕድሜ ልክ ቁርሾ የሚያስከትል የዘር ማጥፋት (genocide) ወንጀል … [Read more...] about ህወሃት/ኢህአዴግ በአማራው ሕዝብ ላይ የዘር ዕልቂት (genocide) አወጀ
አሜሪካ፡ “ህወሃት አብቅቶለታል”
በኢትዮጵያ የስርዓት ለውጥ እንዲካሄድ የማይፈልጉት የአሜሪካ ባለስልጣናት ህወሃት አገር መምራት የማይችልበት ደረጃ ደርሷል የሚል ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል። የሚያደርጉትን ቢያውቁም ለመፍትሄ በተናጠል ተቀናቃኝ ፓርቲዎችንና የሲቪክ ማህበራትን “ምክር” እየጠየቁ ነው። አሁን ያለው ህዝባዊ ተቃውሞ በዚህ ከቀጠለ ኢትዮጵያን ላለማጣት ድንገተኛ የሚመስል ግን የታቀደ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ሊደረግ እንደሚችልም ፍንጭ እየተሰጠ ነው። የጎልጉል ታማኝ መረጃ ሰዎች እንዳሉት የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) እንዳበቃለት የገመገሙት የአሜሪካ ባለስልጣናት “ከወዲሁ አንድ ነገር ማድረግ አለብን” የሚል አቋም ከያዙ ሰነባብተዋል። ለዚሁም መነሻቸው ህወሃት መልሶ እንዲያገግም ሊረዱት አለመቻላቸውና ለራሳቸው ጥቅም ሲሉ የኢትዮጵያን መክሰር አለመፈለጋቸው ነው። “ህወሃት አገር መምራት … [Read more...] about አሜሪካ፡ “ህወሃት አብቅቶለታል”
ከ25 ዓመት በኋላ!
የዛሬ 25 ዓመት ሟቹ "ባለ ራዕይ እንዳይነሣ አድርገን ቀብረነዋል" ያሉት "ጨርቅና አስተሳሰብ" 25 ዓመት እና ከዚያ በታች በሆኑ እንደገና ተውለብልቧል! ምን ይሆን "ትምክህተኛ" ያደረጋቸው? እውነታው ወይስ የህወሃት ዘረኝነትና ጠባብነት?! … [Read more...] about ከ25 ዓመት በኋላ!










