• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የባንኮች የመተርከክ (hack የመደረግ) ሽብር” አገሪቷን እንዳያናውጥ ተሰግቷል

August 31, 2016 02:19 am by Editor Leave a Comment

ህወሃት/ኢህአዴግን በየቦታው እየናጠው ያለው ተቃውሞ በኢትዮጵያ የገንዘብ ቀውስ ሊያስከትል ይችላል የሚል ግምት ተሰጥቶታል፡፡ ችግሩ ባንኮች ላይ የገንዘብ እጥረት እንደሚያስከትልና ባንኮችን ሽብር ውስጥ ሊከታቸው እንደሚችል በስፋት እየተነገረ ነው፤ ደምበኞች ስለገንዘባቸው የሚጠነቀቁበት ጊዜ አሁን ነው፡፡ ህዝባዊ ቁጣ ያሰጋቸው የአገዛዙ ተጠቃሚዎች የውጭ ምንዛሬ እየሰበሰቡ ሲሆን በፍርሃቻ ንብረት በማስያዝ ከባንክ የሚበደሩት ክፍሎች ቁጥርም በርካታ ሆኗል።

ከ10 ወራት በላይ ያስቆጠረውና ለተጨማሪ የኢኮኖሚ ማዕቀብ ቀን የቆረጠው የኦሮሞ ህዝባዊ እምቢተኛነት (#OromoProtests) ያስከተለውን መንኮታኮት ህወሃት በይፋ ባያሳውቅም በግብር አሰባሰብ፣ በውጭ ምንዛሬ፣ በጠቅላላ የውጭና የውስጥ ንግድ የገቢ ስርዓቱን እንዳናጋው ከፋይናንስ ተቋማት የተገኙ መረጃዎች ያመለክታሉ። ይህ እንግዲህ አሁን እየተሰማ ያለው ባንኮችን የመተርከክ (hack የማድረግ) አደጋ ሳያካትት ነው።

ሕዝባዊ እምቢተኛነቱ አድማሱን አስፍቶ መጓዙ ከክልል እስከ ማዕከላዊው አገዛዝ ድረስ የኢኮኖሚ ጫና ማሳደሩ እየተነገረ ባለበት ባሁኑ ወቅት፣ ተቃውሞውን “ሥርዓቱ በቃን፤ መንግሥት ፈርሷል” በማለት የሚቀላቀሉት የህብረተሰብ ክፍሎች የራሳቸውን የጎበዝ አለቃ አስተዳደር አዋቅረው መተዳደር መጀመራቸው የግብር ገቢውን አሽመድምዶታል፤ አድቅቆታል። ህወሃት አሁን በደረሰበት የቁጣ ማዕበል ደፍቆት ጉዳቱን የሚያጣጥም ስሜት ባይኖረውም ወገቡ ደቅቋል የሚሉ በርካታ ናቸው።

ይህ የራስን አስተዳደር አዋቅሮ የመተዳደር ውሳኔ ቆዳውን እያሰፋ ሲሆን አሁን አገዛዙ የሸፋፈነው የኢኮኖሚ መንኮታኮት፣ በቅርቡ ሊደበቅ በማይችል ሁኔታ ራሱን እንደሚገልጽ ባለሙያዎች ከወዲሁ ተንብየዋል። የመንግስት ግምጃ ቤት መረጃ አቀባዮቹን ጠቅሶ የገለጸው የጎልጉል የአዲስ አበባ መረጃ አቀባይ፣ በከፍተኛ ደረጃ ብር ከባንክ የሚያወጡ መበራከታቸው ተጨማሪ ብር ለማሳተምና ገበያ ውስጥ ለማስገባት ዕቅድ እንዳለ እና አሁን አገሪቱ የምትንከላወሰው በድርቅ ስም ከተገኘ የውጭ ምንዛሬ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።

በየቦታው የተነሱትን ተቃውሞዎች ለመቆጣጠር የሚመደበው በጀት፣ የፖሊስና ወታደር የውሎ አበል፣ ሰልፍ ለመበተን የሚፈሰው ገንዘብ፣ … ከወጪ በስተቀር ምንም ገቢ የማያስገኝ መሆኑ እየደረሰ ካለው የኢኮኖሚ ድቀት ጋር ተዳምሮ ችግሩን አወሳስቦታ፡፡ አገሪቱ ለውጭ ገበያ የምታቀርበው ምርት በአብዛኛው ከኦሮሚያ የሚገኝ ከመሆኑ አኳያ 10 ወራትን ያስቆጠረው የኦሮሞ ተቃውሞ (#OromoProtests) እጅግ ብዙ መስዋዕትነትን ያስከፈለ ቢሆንም የህወሃትን አከርካሪ እየገዘገዘው እንደሆነ ራሳቸው በአገዛዙ ውስጥ ያሉ እያመኑበት የመጡት እውነታ ነው፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ በአማራ የተነሳው ተጋድሎና (#AmharaResistance) የቤት ውስጥ አድማ የንግድ እንቅስቃሴን ከመግታት አኳያ የግብር አሰባሰብን በማዳከም የህወሃትን የገንዘብ ቋት እያደረቀው እንደሆነ ከቀናት በፊት በዘገብነው ዜና ላይ በስፋት ተመልክቷል፡፡

ከእነዚህ ተቃውሞዎች ጋር ተያይዞ በየጊዜው የሚካሄደው የአገሪቱን የኢንተርኔት መረብ የመተርከኩ (hack የማድረጉ) ተግባር ህወሃትን በተደጋጋሚ ለከፍተኛ ወጪ ዳርጎታል፡፡ በተለይ ከወራት በፊት በኦሮሞ ተቃውሞ አመራሮች የተካሄዱት የመተርከክ ሥራዎች ህወሃት በዘርፉ በቂ ባለሙያ የሌለው መሆኑን ያጋለጠ ሆኗል፡፡ የትምህርት ተቋማትና ሌሎች መ/ቤቶች በየቦታው በተተረከኩ ጊዜ ሁኔታውን ለመከላከል ኤሌክትሪክ ከቆጣሪው የማጥፋት ዓይነት ውሳኔ መወሰዱ ህወሃት ኢንሳ፤ የሳይበር ወንጀል መከላከል፤ … እያለ የሚያወራው ሁሉ ባዶ መሆኑን በይፋ ያሳየ ነበር፡፡ በወቅቱ የተከሰተውን ቀዳዳ ለመድፈንም በይፋ ያልተነገረ በርካታ ሚሊዮኖችን ወጪ እንዳስወጣው በተለያዩ ጊዜያት ለኢህአዴግ ምክርቤት (ባለ መቶ በመቶው ፓርላማ) በቀረቡ ሪፖርቶች ላይ ተመልክቷል፡፡

telecomከዚህ ባለፈ ሰሞኑን በቴሌ ላይ የደረሰው የመተርከክ ሥራ በአንዳንዶች በተሰጠው ግምት መሠረት ቢያንስ እስከ100 ሚሊዮን ብር ኪሣራን አስከትሏል ተብሏል፡፡ በተደጋጋሚ የቴሌን ጓዳ የተረከከው ተግባር ሰዎች ያሻቸው አገር የፈለጉትን ያህል ሰዓት ያለአንዳች ክፍያ ስልክ መደወል እንዲችሉ፤ የስልካቸው ባትሪ ያልቃል ብለው ካልተጨነቁ በስተቀር ስልካቸውን ደውለው ከፍተው ቢተዉት አንዳች ኪሣራ በማያስከትል ሁኔታ “የወተት ላም፤ አንሸጥም፤ እናልበዋለን” የሚባለውን “የቀለጠውን ሰፈር” ባዶውን አስቀርተውታል፡፡ ዛሬም (ነሐሴ 24፤2008) እንዲሁ “ግድግዳው ተቀዶ” ስልክ “በነጻ እየተደወለ ነው፤ ወትሮ የማትጠቀሙበትን ሲም በመጠቀም ዘመድ አዝማዳችሁን ጠይቁበት” በማለት “በሩን የበረገዱት ታጋዮች” መልዕክት ማስተላለፋቸው ከ#OromoProtests አመራሮች ተነግሯል፡፡

ከዚሁ ከኢኮኖሚ ጋር በተያያዘ የኦሮሞ ተቃውሞ (#OromoProtests) አስተባባሪዎች “ከጳጉሜ አንድ እስከ መስከረም ሁለት 2009 ዓ.ም የሚቆይ በስርዓቱ ኢኮኖሚ ላይ ያነጣጠረ ዘመቻ ይደረጋል” በማለት ዝርዝር መግለጫ ሰጥተዋል። “ዓላማውም የስርዓቱን ኢኮኖሚ በመምታት የጭቆና አቅሙን ማንኮታኮት ይሆናል” በሚል ዓላማ ላይ የተመሠረተው ይህ እንቅስቃሴ እስካሁን ከተካሄደው ጋር ተዳምሮ በኢኮኖሚው ላይ የሚኖረው ጫና ቀላል እንደማይሆን ከወዲሁ ተገምቷል።

የቴሌን መረብ በመተርከክ ያለገደብ በነጻ ስልክ ለማስደወል የበቁት የተቃውሞው አካሂያጆች ወደ ባንኮች ከዞሩ የሚያስከትሉት ተጽዕኖ እስካሁን ከደረሰው እጅግ የከፋ ይሆናል፡፡ ይህንኑ ዓይነት እንደምታ ያለው ሃሳብ በተቃውሞው አራማጆች ሲሰነዘር ሰሞኑን መሰማቱ በኅብረተሰቡ ላይ ፍርሃት መጫሩን አንዳንድ መረጃዎች እየጠቆሙ ነው፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ይሁን በሌላ፣ ባንኮች ከወትሮው በተለየ ሥራ በዝቶባቸዋል። ከህወሃት የአታላይነትና የሌባ ዓይነደረቅነት አኳያ ደምበኞች የጥንቃቄ እርምጃ መውሰድ መጀመራቸው በተለያዩ ቦታዎች እየታየ ነው፡፡

እንደተባለው የባንኮች መረብ የሚተረከክ ከሆነ ባንኮች ያላቸውን ተቀማጭ ባጭር ጊዜ ውስጥ ስለሚሟጠጥ የሚደርሰውን ኪሣራ ለመከላከል የባንክ ተጠቃሚዎች ገንዘባቸውን በእጃቸው ከማድረግ ጀምሮ ያስቀመጡትን ገንዘብ የሚከላከሉበትን መፍትሔ ካሁኑ ማሰብ ይኖርባቸዋል፡፡ ምክንያቱም ባንኮች ከደንበኞቻቸው የሚሰበስቡትን ሁሉ በእጃቸው ላይ የማያስቀምጡ በመሆናቸው ድንገተኛ የገንዘብ ዕጥረት ውስጥ ስለሚገቡ ይህም ወደ ገንዘብ ቀውስ/ሽብር ውስጥ በቀጥታ ስለሚከታቸው ነው፡፡

የህወሃት አገዛዝ ከየቦታው እየተናጠ ባለበት ባሁኑ ወቅት ራሱ አገዛዙ ያመነው 20.6 ቢሊዮን ዶላር ዕዳ አገሪቱ ላይ ተጭኖባት እያለ የባንኮች መረብ ከተተረከከ (hack ከተደረገ) የገንዘቡ ቋት በየቦታው ይቀደዳል፤ ይህ ደግሞ “የባንክ ሽብር” ይፈጥራል፡፡ ባንኮች በሽብር ውስጥ በሚገቡበት ጊዜ ተቀማጭ ጥሬ ገንዘባቸው ይሟጠጣል፤ ይህንን ቀውስ ለማስተካከል ለቀናት ወይም ለሳምንታት ይዘጋሉ፡፡ ይህ ደግሞ ተጠቃሚውን ኅብረተሰብ ከፍተኛ አደጋ ላይ ይጥላል፡፡ እኤአ በመስከረም 2007ዓም በእንግሊዝ በሚገኝ ባንክ ላይ በደረሰ “የባንክ ሽብር” ምክንያት ደምበኞች ለረጅም ሰልፍ ከመጋለጥ አልፈው በአንድ ቀን ብቻ 1ቢሊዮን ፓውንድ ጥሬ ብር ከባንኩ በማውጣቸው ባንኩ ለመዘጋት ደርሶ ነበር፡፡ በቀጣይም የእንግሊዝ መንግሥት ለደምበኞቹ ማረጋገጫ ዋስትና ቢሰጥም ባንኩ እስኪረጋጋ ለተወሰኑ ቀናት ተዘግቶ ነበር፡፡

ከዚህ አንጻር እንደ ህወሃት/ኢህአዴግ በመዝረፍ ላይ ኅልውናውን የመሠረተ አካል በትርከካው ምክንያት በሚደርሰው ኪሣራ የዜጎችን የባንክ ተቀማጭ ገንዘብ “አላውቅም” ብሎ የማይክድበት ምክንያት እንደማይኖር ከረሃብተኛ ላይ እየቀማ ራሱን ያበለጸገበት ታሪኩ ይመሰክራል፡፡

በመሆኑም በአገር ውስጥ አገዛዙን በሁሉም መስክ እያናወጠ ካለው ተቃውሞና በምዕራባውያን ባንኮች ከደረሰው ልምምድ በመነሳት በአገሪቱ የባንክ አገልግሎት ላይ ቀውስ ከመከሰቱና ባንኮች ሽብር ውስጥ ከመግባታቸው በፊት ዜጎች በየባንኩ ባላቸው ተቀማጭ ገንዘብ ላይ መውሰድ የሚገባቸውን እርምጃ ሳይቀደሙ እንዲቀድሙ ጉዳዩ ያሳሰባቸው ይመክራሉ፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule