• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አሜሪካ፡ “ህወሃት አብቅቶለታል”

August 29, 2016 09:45 am by Editor 4 Comments

በኢትዮጵያ የስርዓት ለውጥ እንዲካሄድ የማይፈልጉት የአሜሪካ ባለስልጣናት ህወሃት አገር መምራት የማይችልበት ደረጃ ደርሷል የሚል ድምዳሜ ላይ ደርሰዋል። የሚያደርጉትን ቢያውቁም ለመፍትሄ በተናጠል ተቀናቃኝ ፓርቲዎችንና የሲቪክ ማህበራትን “ምክር” እየጠየቁ ነው። አሁን ያለው ህዝባዊ ተቃውሞ በዚህ ከቀጠለ ኢትዮጵያን ላለማጣት ድንገተኛ የሚመስል ግን የታቀደ ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ሊደረግ እንደሚችልም ፍንጭ እየተሰጠ ነው።

የጎልጉል ታማኝ መረጃ ሰዎች እንዳሉት የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) እንዳበቃለት የገመገሙት የአሜሪካ ባለስልጣናት “ከወዲሁ አንድ ነገር ማድረግ አለብን” የሚል አቋም ከያዙ ሰነባብተዋል። ለዚሁም መነሻቸው ህወሃት መልሶ እንዲያገግም ሊረዱት አለመቻላቸውና ለራሳቸው ጥቅም ሲሉ የኢትዮጵያን መክሰር አለመፈለጋቸው ነው።

“ህወሃት አገር መምራት ካቃተው፣ ኢትዮጵያን ላለማጣት ምን ማድረግ አለብን” ከሚለው መሰረታዊ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ዝንባሌያቸው በመነሳት አሜሪካኖቹ በየእርከኑ አገር ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የተቀናቃኝ ፓርቲ መሪዎችን፣ ነፍጥ አንስተው ከሚታገሉ፣ በውጭ አገር ከሚገኙ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ እንዲሁም ከሲቪክ ተቋማት ጋር ውይይት እያካሄዱ ነው። ውይይቱ “ምን እናድርግ በሚል ምክር የመጠየቅ አይነት ነው” ሲሉ የመረጃው ባለቤቶች ያስረዳሉ። አሜሪካኖች የሚያድርጉትን እያወቁ ምክር የመጠየቃቸውን ጉዳይ የመረጃ ምንጮቹ ባያጣጥሉትም ምክር ተጠያቂዎቹ ተደራጅተውና ህብረት ፈጥረው ተጽዕኖ መፍጠር የሚችሉበትን ሁኔታ ሊያስቡበት እንደሚገባ ይመክራሉ።

(ከዚህ ዜና ጋር በተያያዘ እነ አባይ ጸሃዬ “አማራና ኦሮሞ ተባበሩብን፤ ሰግተናል” በሚል ርዕስ ጎልጉል በዘገበበት ዜና ላይ አሜሪካ ህወሃትን ለማዳን ጥገናዊ ለውጥ እንዲደረግ መፈለጓን፤ ለዚህም በተናጠል የተቃዋሚ ቡድኖችን እያናገረች መሆኗን ጠቅሰን ነበር)

kerry
ቴድሮስ አድሃኖም የሌሉበትና ህወሃት/ኢህኣዴግ የታገደበት ስብሰባ በጆን ኬሪ ሲመራ – ከጎናቸው የኬንያዋ ውጭ ጉዳይ ሚ/ር አሚና ሞሐመድ ቀጥሎ የኡጋንዳው (ምስላቸው አይታይም) በግራ የመጀመሪያው የድቡብ ሱዳኑ ዴንግ አሎር ቀጥሎ የሶማሊያው አብዲሳላን ኦማር ቀጥሎ የሱዳኑ ኢብራሂም ጋንዱር Photo – PAN SIWEI

በደም የተነከረውና ህዝባዊ ቁጣ የናጠውን ህወሃት አቅፋና ደግፋ ወደ ዙፋን ያመጣችው፣ በጀት ቆጥራ ስንዴ ሰፍራ እየደጎመች ዙፋኑን ያጠበቀችለት፣ ሲገድል ከበሮ የደለቀችለት፣ የሕዝብ ድምጽ ዘርፎ ራሱን ሲሾም “ዴሞክራሲያዊ” ያለችው፣ ከህዝባዊ ማዕበልና ከውስጥ መበላላት ያተረፈችው፣ የዛሬውንም ህዝባዊ ማዕበል በጥገና እንዲሻገር ስትደክምለት የኖረችው አሜሪካ አሁን ተስፋዋ እንደተመናመነ ለማወቅ ተችሏል። ይህንኑ ሃሳብ ለማጠናከር ሰሞኑን ኬንያ የተደረገውን የጸጥታ ጉዳይ ስብሰባ ለአብነት ያነሳሉ።

ባለፈው ረቡዕ ኬንያ የተደረገውና የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ኃላፊ ጆን ኬሪ የመሩት የጸጥታ ጉዳይና የጸረአሸባሪነት ስብሰባ ከአራት ወራት በፊት ሲታቀድ ለጉባኤው የተመረጠችው አገር ኢትዮጵያ ነበረች። ስብሰባው ህወሃት በደረሰበት ህዝባዊ አመጽ አማካይነት ወደ ኬንያ መዛወሩ ብቻ ሳይሆን ስለ አልሻባብና ቦኮ ሃራም ውይይት በተደረገበት ስብሰባ ላይ ኬሪ አንድም ጊዜ የኢትዮጵያን ስም አለማንሳታቸው በይፋ ታይቷል፡፡ “በዲፕሎማሲው ቋንቋ ይህ የሚያሳየው አሜሪካ ለህወሃት ጀርባዋን መስጠት መጀመሯን ነው” በማለት የምስራቅ አፍሪካን ፖለቲካ የሚናገሩ ያስረዳሉ። ሲያክሉም ኬሪ ይህ ሁሉ ደም በሚፈስበትና ህዝብ በጅምላ በሚታሰርበት አገር ተገኝተው ስለ ጸጥታ ጉዳይ ስብሰባ ማድረጋቸው አሜሪካንን የሚያሳፍር ከመሆን ባሻገር አለቃቸው ፕሬዚዳንት ኦባማ “ዴሞክራሲያዊት” ብለው ባሞገሷት አገር ላይ ስለ ህወሃት ደምአፍሳሽነት ከዓለምአቀፍ ጋዜጠኞች ጥያቄ ቢቀርብላቸው የአሜሪካንን ኪሣራ አምኖ ላለመቀበል የተቀነባበረ እንደሆነ ያስረዳሉ፡፡ ስለዚህም ስለ አልሻባብ እና ስለ ደቡብ ሱዳን ደኅንነት በተጠራው ስብሰባ ላይ “የሶማሊያ መሃንዲስ የአልሻባብ ባለገድል” እንዲሁም የደቡብ ሱዳን “አሸማጋይ” የሆነውን ህወሃት እንዳይገባ ተከልክሏል፡፡

መለስ በG-20 ስብሰባ
መለስ በG-20 ስብሰባ

የምዕራብ ተላላኪ የነበሩት ሟቹ “ባለራዕይ” መለስ በአገር ውስጥ ያለው ግፍ እያሳጣቸው በመጣ ጊዜ ጌቶቻቸው ጀርባ ሰጥተዋቸው የዕራት ግብዣ ጠረጴዛ ላይ ሻማ ያዥ አሽከር መስለው የታዩበት ጊዜ የሚታወስ ነው፡፡

በ1983 የሎንዶን ድርድር ኢትዮጵያን በኸርማን ኮኽን አማካይነት ለህወሃት ያስረከበችው አሜሪካ “ህወሃት አብቅቶለታል” ከሚለው ድምዳሜ ላይ ባለችበት ባሁኑ ሰዓት የተቃዋሚው ኃይል በቶሎ አገር ወደማዳን አጀንዳ በኅብረት ተንቀሳቅሶ አንድ ደረጃ ላይ ካልደረሰ አሜሪካ ድንገተኛ የሚመስል ግን አስቀድሞ የታቀደ ወታደራዊ የመፈንቅለ መንግስት ልታካሂድ ትችላለች የሚል ግምት እንዳለ ለማወቅ ተችሏል። የዜናው ሰዎች እንደሚሉት ከሆነ አሜሪካ ይደረጋል ብላ የምትጠብቀው ኩዴታ “በድንገት የሚደረግና የማይታወቅ አይደለም” ሲሉ በየደረጃው ከተቀመጡት አማራጮች መካከል አንዱ ስለመሆኑ ፍንጭ ይሰጣሉ። ሲያብራሩም የቀድሞውን የህወሃት ታጋይ ጻድቃንን እና ሌሎች የቀድሞ የመከላከያ ኃላፊዎችን ከፊት ለፊት ያመጣሉ።

ሰሞኑን ጻድቃን ገ/ትንሣኤ ያቀረቡት “የመፍትሔ ሃሳብ” ውስጥ የመከላከያውና የደህንነቱ መዋቀር እንዳለ ቆይቶ ህገ መንግስቱን መሰረት ያደረገ የስርዓት ማሻሻያ ከማድረግ የተሻለ አማራጭ እንደሌለ የሚያሳስብ ነው። ዜናውን ያቀበሉት ክፍሎች ሲያከሉም “በዚህ እሳቤ ውስጥ ሆኖ መፈንቅለ መንግስቱን ማስላት አግባብ ነው” ባይ ናቸው። እናም አሜሪካ በግል የምታናግራቸውና የኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ ሁሉ በቶሎ ግንዛቤያቸውን ሊያሰፉና የመፍትሄ ሃሳብ ሊያቀርቡ እንደሚገባቸው ያሳስባሉ።

ላለፉት 25 ዓመታት ታማኝ በሆናት ህወሃት አማካኝነት አሜሪካ በኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ የወታደራዊና የደኅንነት መዋዕለ ንዋይ ማፍሰሷ ይታወቃል፡፡ ኢትዮጵያን ላለማጣት የምትፈልገው ካላት ወታደራዊ ኢንቨስትመንትና ሌሎች ጥቅማጥቅሞች አኳያ እንደሆነ በሰፊው ይታመናል፡፡

ከተያዙት የተለያዩ መፍትሔዎች መካከል መፈንቅለ መንግስት አማራጭ ከሆነ “ሥልጣን እስከ ሞት” በሚሉ ህወሃቶችና ተራው የእኛ ነው በሚሉ “ንሰሃ በገቡ የለውጥ አራማጅ” ህወሃቶች መካከል እርስ በእርስ መበላላት ሊኖር እንደሚችል ከግምት በላይ ስጋት አለ። መከላከያውና ደህንነቱ የሚመራው ባንድ አካባቢ ተወላጆች መሆኑ የአቋም ልዩነት ከተነሳና መከዳዳት ከተከሰተ መቀዳደም ሊኖር እንደሚችል የሚገመቱ አሉ። በሌላ በኩል ከስልጣናቸው በላይ ዋስትና አግኝተው ያላቸውን ሃብት ማስተዳደርና መኖር የሚፈልጉ ስለሚበዙ ጉዳዩ እጅግ ቀላል የመሸጋገሪያ መንገድ እንደሆነ የሚያስቡም አሉ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ህዝባዊ ተቃውሞው ስልቱን እየቀያየረ ተጠናከሮ ቀጥሏል። ከየአካባቢው በምስል እየተደገፉ የሚወጡት መረጃዎች እንደሚያሳዩት ህዝብ እምቢተኛነቱን የሚገልጽበት መንገድ ኢኮኖሚውን እያመነዠገው ነው። ይህ በሆንበት ሁኔታ ህዝባዊ እምቢተኛነቱ ትምህርት ቤቶችና ከፍተኛ ተቋማት ሲከፈቱ ዋና ዋና ከተሞችን በሙሉ ያዳርሳል የሚል ፍርሃቻ ነግሷል።

በሌላ ዜና በአማራ ክልል የሚካሄደውን ህዝባዊ እምቢተኛነት አስመልከቶ መረጃ የሚሰጡ የፖለቲካ ድርጅቶች የመናበብና የመረጃ አሰጣጥ ስልት ችግር እንዳለባቸው ተሰምቷል። በብዛት አሜሪካ ራዲዮ የሚያናግራቸው እነዚህ ክፍሎች የሚሰጡትን መረጃ የማደራጀትና በየሰአቱ የማጎልበት ችግር ይስተዋልባቸዋል። እንደውም ጉዳዩን ወደ ህዝብ ወኪሎች ቢገፉት የተሻለ እንደሆነ የሚመከሩም አሉ። በቅንጅት ወቅት ሁሉም የተሳከረ መረጃ እየሰጡ የተፈጠረውን ችግር የሚያስታውሱ ክፍሎች መረጃ ተደራጀቶ የሚሰራጭበት አግባብ ሊፈለግ እንደሚገባ አበክረው ይመክራሉ። ሕዝባዊ ተቃውሞ አስቀድሞ ከጀመረው የኦሮሞ ተቃውሞ ጋር ኃይልን ማስተባበር እንደ አማራጭ ሊታይ ይገባዋል ሲሉ ሃሳብ ይሰጣሉ፡፡

ከበላይ አመራሩ በስተቀር አብዛኛው የብአዴን ካድሬ ከድቷል በሚባልበት ባሁኑ ወቅት “መንግሥት ፈርሷል” እየተባለ መነገሩና ሕዝቡ በጎበዝ አለቃ እየተመራ መምጣቱ ህወሃትን ከፍተኛ ቀውስ ውስጥ ከቶታል፡፡ ሁሉም ድርጅቶች የተናጠል ስብሰባ አካሂደው በመጨረሻም የኢህአዴግን የሚያደርጉበት የተለመደ አሠራር ቀርቶ ህወሃት ብቻ ባደረገው ስብሰባ የኢህአዴግ ምክርቤት መግለጫ አውጥቷል፡፡ ይህም እንደ ኦህዴድ ብአዴንም የከዳና መተማመን በግምባሩ ውስጥ የመነመነ መሆኑን የሚያሳይ ሲሆን በቀጣይ ህወሃት በኦፊሴል ባያውጅም እንደ ኦሮሚያ የአማራን ክልልም በወታደራዊ አገዛዝ ሥር እንደሚያስተዳደር አመልካች ሆኗል፡፡

ይህ አካሄድ ለህወሃት የኅልውና ጉዳይ ስለሆነ የተከፈለው መስዋዕትነት ተከፍሎ “አገር በማዳን” ስም በበርካታ አካባቢዎች የከረረ ወታደራዊ እርምጃ ሊወስድ ይችላል የሚለው በስፋት የሚታመንበት ሆኗል፡፡ በአሜሪካ ድጋፍ ሲቪል መሰል ወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከተከሰተም አገር ማረጋጋት በሚል ተመሳሳይ እርምጃ የማይወሰድበት ምክንያት እንደሌለ አስተያየት ይሰጣል፡፡ በመሆኑም “ህወሃት አብቅቶለታል” በሚባልበት በአሁኑ ሰዓት የተቃዋሚው ኃይል ሁሉን አቀፍ አንድ ወጥ ቻርተር ወይም አጀንዳ መቅረጹ በቶሎ ሊሰራበት የሚገባ እንደሆነ ጉዳዩ የሚያሳስባቸው አበክረው ይናገራሉ፡፡ (ቀዳሚ ፎቶ አጋዚ በአዲስ አበባ ፎቶ ምንጭ AP)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tadesse says

    August 29, 2016 01:13 pm at 1:13 pm

    If the for united states have a future for its people and the world,it must try to help the Ethiopian according to what is written here/America can’t exist with out helping create democratic governments in Israel and Ethiopia.

    Reply
  2. Tamirat says

    August 30, 2016 12:40 am at 12:40 am

    We dont have to expect anything from outside. TPLF will soon resort to an allout mascer and we have to prepare to defend our people and beet the invader. That is what we should talk about now, not blowing baseless conspiracy theory.

    Reply
    • Sammy T says

      September 10, 2016 04:45 pm at 4:45 pm

      I agree with you. People are using their enslaved mentality. They want their destiny be decided by their masters. People, even if your masters gave you a solution, it would be what works for them, not you.

      Reply
  3. Takele says

    August 30, 2016 10:15 pm at 10:15 pm

    This is a call for Ethiopian people to stand up together and avert the catastrophic situation that our country is facing . Community leaders , religious leaders , Ethiopian people who are living all over the world , organizations who are working on conflict resolution , mediation etc , this is the time to collaborate and come together to make a conducive atmosphere for reconciliation . say bygones be bygones . The situation in Amhare and Oromia regions is getting bad from day to day , this is because the security personals especially Agazi resorted to the use of ammunition and left with a number of people died and wounded . The religious leaders ,influential persons , elderlies have to preach forgiveness in order to heal the emotions and wounds of hatred or anger that had been created by the Ethiopian government.
    I am hopeful that Peace and Justice for Africa( PJA) is going to do an outstanding job by creating methods how to solve African’s problem using different means and techniques . I personally encourage Peace and Justice for Africa, to do the best by caring intuitive dedication and look for ways and means to resolve crisis looming In Ethiopia before the bloodshed spreading and change to civil war . The only thing that can be break Is making possible a new beginning is forgiveness . Those Ethiopian’s who have suffered grievously in EPRDF regime will engage in the most fearful orgy of revenge before this happen in our beloved country every organization or concerned individual has to put maximum effort to avert. PJA consistently needs out supporting feedback to enable improve negotiation and mediation skill which can give impressive quality for the organization to startup mediation and negotiations which has to be followed by Reconciliation . PJA can sale its objectives , missions , activities and relentlessly teach the benefit of tolerance , the habit of openness to and empathy for the opinions feelings and perspective to the concerned groups .
    Due to the strong work of PJA I feel confident and cordially invite the organization to African countries and donors to collaborate with the organization to implement its objectives . At the same time PJA will show the affected part of Africa especially Ethiopia excellent organizational and management abilities with the ability to solve or at least minimize the crucial problem created in Ethiopia quickly . From the organization’s website I understand PJA is eager to complete tasks effectively which ultimately serves as proof of PJA’s dedicated ambition to succeed .
    PJA is managed by well experienced people who acquired considerable experience for a long time . I believe that the experience in particular give the organization a great advantage in pursuing the current situation we are facing in our country Ethiopia .
    Takele

    Sent from my iPad

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule