• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የገደሉት ልጄ አስከሬን ላይ ቁጭ በይ ብለው ደበደቡኝ” ደምቢ ዶሎ የተገደለ ወጣት እናት

September 7, 2016 08:18 pm by Editor 1 Comment

በቄለም ወለጋ ዞን ደምቢዶሎ ከተማ ውስጥ ትናንት ማክሰኞ ማምሻው ላይ ከመንግሥት ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉን የከተማዋ ነዋሪዎች ገለጹ። የአንደኛው ወጣት ወላጅ እናት እኔንም የልጄ አስከሬን ላይ ጥለው ደበደቡኝ ብለዋል።

በመንግሥት ታጣቂ ጥይት ህይወታቸው ያለፈው ሁለቱ ሃይሉ ኤፍሬም እና ኢብሳ ሩንዴ የሚባሉ ሲሆኑ የ16 ዓመቱ ወጣት ሃይሉ ኤፍሬም ከተማዋ ውስጥ ተኩስ በመከፈቱ ከሌሎች ጓደኞቹ ጋር ከተኩሱ ለማምለጥ ሲሮጥ መትተው ገደሉት ሲሉ የከተማዋ ነዋሪዎች ገልጸዋል።

“ደሞቢ ዶሎ መሃል ከተማ ነበር ተኩስ የተጀመረው። ወደ ቀበሌ ዜሮ አምስት አካባቢም ተኩስ ነበር ። ልጆቹን እያባረሩዋቸው ሲመጡ ወጣት ሃይሉ ኤፍሬም በቅጽል ስሙ ቦጌ ነው የሚባለው ቀበሌ ዜሮ ሰባት በሚገኘው መኖሪያ ቤቱ አቅራቢያ ነው የተገደለው” ብለዋል የአሜሪካ ድምፅ ያነጋጋራቸው የከተማዋ ነዋሪ።

ሌላው ወጣት ኢብሳ ሩንዴ ደግሞ ግቢው ውስጥ ቆሞ እንዳለ ተኩሰው ገድለውታል ሲሉ የደምቢ ዶሎ ነዋሪ አስታወቀዋል። አስከሬኑን ወደ ሆስፒታል በመውሰድ ላይ እንዳሉ የመንግሥት ታጣቂዎቹ አስቁመው ወደቤት መልሷቸው ሲሉ ነዋሪው አክለው አመልክተዋል።

ከሟቾቹ መካከል የአስራ ስድስት ዓመቱን ወጣት የሃይሉ ኤፍሬም እናንት ወይዘሮ ታደሉ ተማምን በስልክ አግኝተን የልጃቸውን መገደል ሰምተው እንደሆነ ጠየቅናቸው።

“ቤት ውስጥ ነበርኩ። እሱ ደግሞ ከልጆች ጋር ሊጫወት ወጣ ብሎ ነበር። ከተማ ውስጥ ብጥብጥ ተነሳ ሲባል መሯሯጥ ጀመሩ። ከፊት ይሮጥ የነበረውን ልጄን መትተው ጣሉብኝ። ጓደኞቹ መጥተው ሲነግሩኝ ሮጬ ሄድኩ።ስደርስ ልጄ ሜዳ ላይ ተዘርግቷል። አንድ ያለኝ ተስፋ እሱ ነበር። እንደ አባትም ሆኖ በባሌም ምትክ የቀን ሥራ እየሰራ የሚረዳኝን ልጄን ነው ያጣሁት” ብለዋል።

ታጣቂዎቹ ጥለውኝ ሲሂዱ ብጮህ ሰዉ ሁሉ ፈርቶ ሸሽቷል። እኔና ሴቷ ልጄ ሜዳ ላይ ብቻችንን አለቀስን ያሉት የሟቹ ወጣት እናት አንገቱ ላይ መትተው ነው የገደሉብኝ ብለዋል። በኃላም ጎረቤቶች ተሰብሰበው ረድተውኝ ልጄን ሸኙልኝ። የአስከሬን ሳጥን መግዣ እንኳን አልነበረኝም ብለዋል።

ከቂለም ወለጋ የፖሊስ አዛዥ ምላሽ ለማግኘት ደውለን ነበር። ይሁን እንጂ አዛዡ ኮማንደር ቦደና ስልኩን ካነሱ በኃላ ዘግተውታል።

ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል እዚህ ላይ ያድምጡ። (ምንጭ: የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ)

ፎቶ: ከግራ ወደ ቀኝ ኢብሣ ሩንዴ እና ኃይሉ ኤፍሬም (ቦጌ) ከጃዋር ፌስቡክ የተገኘ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Lusif says

    September 9, 2016 09:12 pm at 9:12 pm

    I can’t say it did not happen. I am still troubled by the nature of human beings particularly the so called law enforcers or military personals. They are supposed to protect citizens against criminals and oppressive government.
    It is natural, no matter what,a mother cry for her dead son. Why on earth, however I am cynical, force a mother to sit on her son’s dead body and bit hear down. Those military personnel must be sadistes evil in human appearance. I still doubt it, that a human person do such evil deeds.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule