• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“… መብከት፣ መበስበስ ከአንዴ በላይ ይደብራል …” ሕዝብ

September 6, 2016 08:41 pm by Editor 2 Comments

ከመተካካት አልፈው ራሳቸውን “recycle” ያደረጉትን የህወሃት/ኢህአዴግ ሹሞች ያካሄዱትን ውይይትና የሕዝቡን አስተያየት የጀርመን ድምጽ ሬዲዮ ዘግቧል – “የኢህአዴግ ከፍተኛ ባለስልጣናትና የኢትዮጵያ ሁኔታ” በሚል ርዕስ የታተመው ዘገባ እንዲህ ይነበባል:-

ኢትዮጵያን የሚመራዉ የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) በቅርቡ ካካሔደው ግምገማ በኋላ በሥራ አስፈጻሚዎቹ ዘንድ ሹም ሽር ሊያካሂድ መሆኑን እየተናገረ ነው። የገዢው ግንባር ሹም ሽርም ይሁን ግምገማ ግን ለውጥ ለማምጣቱ በርካቶች ጥያቄ አላቸው።

ከሩብ ምዕተ-ዓመት በላይ በስልጣን ላይ የቆየው የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ከገባበት አጣብቂኝ ለመውጣት ተሿሚዎቹን ሊገመግም እንደሆነ አስታውቋል። ከጠቅላይ ሚንስትር ሐይለ ማርያም ደሳለኝ አማካሪዎች መካከል አቶ አባይ ፀኃዬ ግንባሩ የመንግስት ተሿሚዎችን «አመኔታ በሰራተኛ፤ በሕዝብ በፓርቲ ዘንድ አለው ወይስ የለውም? ውጤታማ ነው? ውጤታማ አይደለም?» ብሎ ሊገመግም እንደሆነ ጠቁመዋል። ሌላዉ የጠቅላይ ሚንስትሩ አማካሪ አቶ በረከት ስምዖን በበኩላቸው «የመንግስት አስፈጻሚ አካላትን በአዲስ መልክ እናደራጃለን» ሲሉ ተደምጠዋል።

የዶይቼ ቬለ የፌስቡክ ገፅ ተከታታዮች ግን የኢህአዴግ ሹም ሽር ለውጥ ማምጣቱን ይጠራጠራሉ። አስተያየት ከሰጡት አንዱ፤ ጌትነት በላይ «ኢህአዴግ እኮ በ1993 በክቶ እንደገና ታደስኩ ብሎ መቅረቡ ይታወሳል። መብከት፣ መበስበስ ከአንዴ በላይ ይደብራል። አሁን እኮ በህዝብ ላይ ጦርነት በይፋ ታውጇል። ማንን ለማስተዳደር ነው መታደስ የሚያስፈልገው?» ሲሉ ይጠይቃሉ። «አንድን ጥያቄ መፍታት ጥያቄውን በቅጡ ከመረዳት ይጀምራል» የሚሉት ዮሐንስ አያሌው «ገዢው ፓርቲ የሚያልመው ለውጥ ከሕዝብ መሰረታዊ የለውጥ ጥያቄ» ጋር እንደማይጣጣም ፅፈዋል። ቹቹ ደግሞ «ላይኛውን ማን ያደራጀው? ሁሌ ታችኛው አመራር ጥፋተኛ ከተባለ የሱ አለቃስ ላይኛው ጤነኛ ይሆን?» ብለዋል።

ኢህአዴግ ‘ተሐድሶ’ ያስፈልገኛል ያለው የአስራ አምስት አመታት የስራ ክንውኑን በአራት ቀናት ከገመገመ በኋላ ነው። ግንባሩ ከዚህ ቀደም የገጠሙትን ፖለቲካዊ ቀውሶች በግምገማ ለመፍታት ቢሞክርም መሰረታዊ ለውጥ ማምጣት ግን የቻለ አይመስልም። የፖለቲካ ተንታኝ አቶ ቻላቸው ታደሰ ኢህአዴግ የሚከተለውን የዴሞክራሲ ማዕከላዊነት መርሕ «ያልተቀደሰ ጋብቻ» ይሉታል።

ይህ የዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት መርሕ በአባል ድርጅቶች እና በግንባሩ መካከል ያለውን ግንኙነት ሚዛን አዛብቶት ቆይቷል። አራት ፓርቲዎችን የያዘው ኢህአዴግ በሥራ አስፈጻሚነት የሚያካሂዳቸው ሹም ሽሮች ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ ናቸው እየተባሉ ይተቻሉ። ሰሞኑን ከከተማ ልማትና ቤቶች ሚኒስትርነታቸው የተነሱት አቶ መኩሪያ ኃይሌ መልሰው የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ አማካሪ ሆነዋል። ኢህአዴግ አባል ያልሆኑ ግን ደግሞ በሙያቸው ብቁ ግለሰቦችን በሥራ አስፈጻሚነት ለመሾምም ዝግጁ አይመስልም።

ባለፈው ዓመት የተካሔደውን አገር አቀፍ ምርጫ በየክልሎቻቸው መቶ በመቶ ድምፅ በማግኘት ያሸነፉት ብአዴን እና ኦህዴድ ዘንድሮ የተቀሰቀሰባቸውን ጥያቄዎች መመለስ የሕግ የበላይነትን ማስጠበቅ እና ሕዝባቸውን ማረጋጋት ተስኗቸዋል። ሁለቱ ፓርቲዎች በሕዝብ ዘንድ ያላቸው ተዓማኒነትም ጥያቄ ውስጥ የወደቀ ይመስላል። በዶይቼ ቬለ የፌስ ቡክ ገፅ አስተያየታቸውን ያሰፈሩት አባ ጨብሳ «ሁለቱም ዱቄት ናቸው።» ይላሉ። ጃክ ካሬስ በበኩላቸው «ሁለቱም እኮ አቅም የላቸውም በራሳቸው በራሳቸው ምንም ነገር መወሰን አይችለም ስለዚህ በህዝቡም ዘንድ ተቀባይነታቸው አይታየኝም» ብለዋል። ሳዴን ሳዶ ሳዴን ፓርቲዎቹን «የህወሃት ጉዳይ አስፈፃሚዎች» ይሏቸዋል። ይነጋል በሚል ሥም አስተያየት ያሰፈሩ ሌላ ግለሰብ «የሞግዚት አስተዳደር እንዴት ተቀባይነት ይኖረዋል?» ብለው ጠይቀዋል። አቶ ቻላቸው ታደሰ የኦሮሚያ እና የአማራ ክልሎችን የሚያስተዳድሩት ኦሕዴድ እና ብአዴን እና በግንባሩ መካከል ያለው የስልጫን ክፍፍል ፍትኃዊ እንዳልሆነ ይናገራሉ።

እሸቴ በቀለ

ነጋሽ መሐመድ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Ayu asfaw says

    September 7, 2016 06:07 am at 6:07 am

    Gulcha bikeyayer Wot Ayataftem !!!

    Reply
  2. Lusif says

    September 9, 2016 10:57 pm at 10:57 pm

    What they do not understand is that they are products of the sixties communist conflict ideologists who strongly believe domination of a group over the masses. The strategic means to this domination is political and economic power through violence and animosity They only feel they are only responsible to their close relatives and group. That is why they call themselves a dominante group/ party.
    Such mentality has overlived it’s time and became morbid. The new generation has already acquired a new different political, economic and social order. Unity with mutual respect and equality, economic self interest with equal opportunity, compassionate individual with social responsibility.There is a clear generational gap.
    These two understandings are mutually exclusive. The group mentality can only survive by suppressing and undermining the new mutual social responsibility. The new social responsibility paradigm can only grow upon the grave of group mentality. So the struggle is between the old dieing status quo and the new embryo of freedom, equality, justice and democracy. The old relays on relative peace managed by force, the new one on enduring peace managed by consensus and democracy.
    It is a historical fact and inevitable the ruling party with its old garbage, must go unless it makes informed and wise decision and make a U turn.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule