በተነሳው ተቃውሞና ግጭት ጉዳት የደረሰባቸው አሉ የሲዳማን የክልልነት ጥያቄ ለዛሬ ለማወጅ መቀጠሩን ተከትሎ በሐዋሳ እና አካባቢዋ ግጭት ተቃውሞ መከሰቱ ተገለፀ ። ከዚህ ጋር ተያይዞ ከተማዋ የጦርነት አውድማ እንደሆነች ተደርጎ በማኅበራዊ ሚዲያ የሚወራው ሐሰት መሆኑ ተነገረ ። የጥያቄ አራማጆች ለአዣንስ ፍራንስ ፕረስ እንደገለፁት የሲዳማ ሽማግሌዎች እና ወጣት የጉዳዩ አቀንቃኞች ዛሬ ጠዋት ሊያካሂዱት ያቀዱት ስብሰባ አካባቢውን በዘጉት በፀጥታ ኃይሎች ተደናቅፏል። ባለሥልጣናት ወደዚያ ባለመምጣታቸው፤ እና ወደ መሰብሰቢያው ስፍራም እንዳያልፉ ያገዷቸው የፀጥታ ኃይሎች ላይ ወጣቶቹ ድንጋይ መወርወራቸውንም ዘገባው አመልክቷል። ሐዋሳ ከተማ ላይ በቁጣ ወደ ጎዳና የወጡት ዜጎች ጎማ በማቃጠል ከፀጥታ ኃይሎች ጋር በተፈጠረው ግጭትም ቢያንስ የአንድ ሰው ሕይወት መጥፋቱን … [Read more...] about ሀዋሳ የጦርነት አውድማ አልሆነችም
Full Width Top
አዴፓ ህወሓትን በልኩ በሚገባው ስም በመጥራት አዋርዶ ቀበረው
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ ላለፉት ሰባት ዓመታት የኢትዮጵያ ብቸኛ ጠላት የሆነውን ህወሓት በሚገባው ስም መጠራት አለበት በማለት በተደጋጋሚ ሲወተውት ለመኖሩ ያለፉትን ጽሁፎች መመልከቱ በቂ ግንዛቤ ይሰጣል። በመሆኑም ህወሓት (የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር) በሚለው የተገንጣይ ስሙ አገር በግፍ እየገዛ ያለ የወንበዴዎች ስብስብ ነው በማለት በዚሁ ስሙ እንዲጠራ ብዙ ብለናል። ይህ የአሸባሪዎችና በሞራል ዝቅጠት የመጨረሻው ደረጃ ላይ ባሉ ርካሾች የሚመራ የወሮበሎች ድርጅት በነጻ አውጪ ስም ኢትዮጵያን ያከለ ታላቅ አገር በንቀት እየገዛ ያለ ነው በማለት አትተናል። በመሆኑም ይህ በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች ቋት ውስጥ እስካሁን ድረስ ተመዝግቦ የሚገኝ ድርጅት መታደስ ሳይሆን መታገድና መክሰም ያለበት መሆኑንም አበክረን አሳስበናል። ይህ የእኛ ብቻ ሳይሆን የበርካቶች … [Read more...] about አዴፓ ህወሓትን በልኩ በሚገባው ስም በመጥራት አዋርዶ ቀበረው
የጄ/ል አበባው “ከፈለገ ይፈንዳ” ንግግር በትግራይ ሌላ ችግር እያፈነዳ ነው
ትግራይን የተቆጣጠሩ የቀድሞ አገዛዝ ርዝራዦች አሁንም ለዐቢይ ችግር ናቸው በባህርዳርና አዲስ አበባ በተቀናጀ መልኩ በተካሄደው የመፈንቅለ መስተዳድር/መንግሥት ህይወታቸውን ባጡት ጄ/ል ሰዓረ መኮንን አስከሬን ሽኝት ላይ በጄ/ል አበባው ታደሰ የተነገረው በትግራይ ሌላ ችግር እያፈነዳ መሆኑ ተሰማ። በአዲስ አበባ በቅድስት ሥላሴ ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው የጄ/ል ሰዓረ ቀብር ትግራይ መደረጉ ይህንኑ ተከትሎ ለተነሳው “እሣት” ማዳፈኛ ይሆን ዘንድ ለፖለቲካ ፍጆታ የዋለ መሆኑ ተገለፀ። በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር መ/ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ኃላፊው ቲቦር ኒጌይ ትግራይ የመሸጉ የህወሓት ርዝራዦች አሁንም ለጠ/ሚ/ር ዐቢይ ችግር ፈጣሪዎች እንደሆኑ ተናገሩ። ህወሓትን በአደባባይ እንደሚያገለግል እየተናገረ መከላከያውን በኤታማዦር ሥልጣን ለረጅም ዓመታት ሲመራ የነበረው ሳሞራ የኑስን … [Read more...] about የጄ/ል አበባው “ከፈለገ ይፈንዳ” ንግግር በትግራይ ሌላ ችግር እያፈነዳ ነው
ህወሓት ወደ ስልጣን ለመመለስ የሎቢ ሥራውን ዳግም ጀምሯል
የተከበራችሁ የጎልጉል አንባቢያን፤ ለወራት ጠፍተን በመቆየታችን ታላቅ ይቅርታ እንጠይቃለን። አንዱና ዋንኛው ምክንያት ድረገጻችን በማደስና የምናትማቸውን ጽሁፎች ባዲስ መልክ ለማድረስ እየሠራን ስለነበር ነው። ሥራው በፈቃደኝነት የሚሠራ በመሆኑ ካሰብነው ጊዜ በላይ ቢወስድብንም ባሁኑ ጊዜ በመጠናቀቅ ይገኛል። በቅርቡ አዲሱን ድረገጻችንን እናስተዋውቃለን። እስከዚያው ግን እዚሁ ላይ እንደተለመደው መረጃዎችን ማተማችንን እንቀጥላለን። በተደጋጋሚ ለጠየቃችሁንና መልዕክቶች ለላካችሁልን ምስጋናችን የላቀ ነው። ከልብ እናመሰግናለን። ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ። በኢትዮጵያ ከፖለቲካው ቀውስ በማያንስ መጠን የኢኮኖሚው መላሸቅ፣ የሥራአጥነትና ድህነት የሚያስከትሉት አደጋ አሳሳቢና አደገኛ ሊሆን እንደሚችል ተጠቆመ። የለውጡ ኃይሎች ለውጡን በሚያደናቅፉ ላይ ፈጥነው እርምጃ አለመውሰዳቸው … [Read more...] about ህወሓት ወደ ስልጣን ለመመለስ የሎቢ ሥራውን ዳግም ጀምሯል
ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ኢትዮጵያ 20 ቢሊዮን ዶላር ተዘርፋለች!
ህወሓት/ኢህአዴግ በግፍ ሲገዛት በነበረችው ኢትዮጵያ፣ አንድ ዓመት ያልሞላው የለውጥ ሒደት ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ባሉት ዘጠኝ ዓመታት (እኤአ 2003 – 2012) ባሉት ዓመታት ውስጥ 20ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ በሕገወጥ መንገድ ከአገር ወጥቷል፤ ተዘርፏል። የሪፖርተሩ ብርሃኑ ፈቃደ ያቀናበረው እንዲህ ይነበባል፤ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ሥር የሚገኘው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ይፋ ያደረገው የአፍሪካ የጤና ክብካቤና የኢኮኖሚ ዕድገት ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ውስጥ 20 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ወደ ውጭ በሕገወጥ መንገድ እንደሸሸባት አስታውቆ፣ ይህ ገንዘብ ለጤናው ዘርፍ የምታውለውን 87 በመቶ በጀት እንደሚሸፍን አመለከተ። ማክሰኞ የካቲት 5 ቀን 2011 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ይፋ የተደረገው የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ … [Read more...] about ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ኢትዮጵያ 20 ቢሊዮን ዶላር ተዘርፋለች!
በእስር ቤቱ ውስጥ ኢንተርኔት የለም፤ ኮምፒውተር እንፈልጋለን – በረከት ስምዖን
በሌብነት የተጠረጠሩት በረከት ስምኦንና ታደሰ ካሣ አርብ በባህር ዳርና አካባቢዋ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። በዕለቱ ሁለቱም ግለሰቦች ያሉባቸውን ችግሮች ያስረዱ ሲሆን በተለይ በረከት ስምዖን በእስርቤቱ ውስጥ ኢንተርኔት የለም ሲል ማማረሩን ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል። ኮምፒውተር ያስፈልገናልም ብለዋል። በዕለቱ የአማራ ክልል ፀረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪ ባለፈው በተሰጠው የጊዜ ቀጠሮ ማስረጃዎችን ማየቱንና የምስክሮችን ቃል መቀበሉን አሳውቋል። ሆኖም ጉዳዩ ከባድ፣ ውስብስብና ድንበር ተሻጋሪ ከመሆኑም በላይ ምስክሮች እና ሰነዶች በሃገር ውስጥ እና ከሃገር ውጪ መገኘታቸውን አስታውሶ ምርመራውን ባለማጠናቀቁ ተጨማሪ የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል። በወቅቱ የቀረበውን ማራዘሚያ ቀን በረከት የተቃወመ ሲሆን ያቀረበው ምክንያትም የሕግ ሥልጣን በሌለው አካል መከሰሰሱን ነው። ይህ ሕጋዊነት … [Read more...] about በእስር ቤቱ ውስጥ ኢንተርኔት የለም፤ ኮምፒውተር እንፈልጋለን – በረከት ስምዖን
የአል አሙዲ ሃብት በ9.7 ቢሊዮን ዶላር ወደረ!
የኢትዮጵያን ሃብት ከህወሓት ጋር በጥቅም በመመሳጠር ሲበዘብዝ የነበረው መሐመድ አለ አሙዲ (አላሙዲ) እጅግ በርካታ ገንዘብ ከፍሎ በሌብነት ከታሰረበት ሳዑዲ አረቢያ መለቀቁ ተሰምቷል። ከዚህ ጋር በተያያዘ ሲታሰር 10.9 ቢሊዮን ዶላር የነበረው ሃብቱ ሲፈታ 1.2 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል። በፎርብስ ደረጃ አሠጣጥ መሠረት ከእስር በኋላ የ159ኛ ደረጃ ሰጥቶታል። ሆኖም ፎርብስ የአላሙዲ ሃብት በእርግጥ የእርሱ መሆኑን ማረጋገጥ ስላልቻለ በ2018 ከዓለም ቢሊየነሮች ዝርዝር ውስጥ አውጥቶታል። በርካታዎች እየሞቱና መብታቸው ተገፍፎ በእስር እየማቀቁ በነበሩበት ወቅት የንብ ካኔተራ በመልበስ የህወሓት ደጋፊነቱን በገሃድ ያስመሰከረው አላሙዲንን ከህወሓት ለይቶ “የሕዝብ ሰው” አድርጎ ማቅረብ ለህወሓት ያለን “ጥላቻ” ከአላሙዲ “ትግሬ” አለመሆን ጋር የተገናኘ ይመስላል የሚሉ ጥቂቶች … [Read more...] about የአል አሙዲ ሃብት በ9.7 ቢሊዮን ዶላር ወደረ!
ህወሓት በክህደት አከርካሪው ተመታ
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) በማለት ራሱን የሚጠራው የበረሓ ወንበዴዎች ስብስብ አባል የነበረው ዛዲግ አብርሃ ከድርጅቱ አባልነት ለቋል። በህወሓት ታሪክ ዓይነተኛ ቦታ የሚሰጠው ይህ ክህደት ድርጅቱን ክፉና ጎድቶታል። ዛዲግን የሚከተሉ ይኖራሉ ተብሎ ይጠበቃል ተብሏል። በጠ/ሚ/ር ዐቢይ አሕመድ ግንቦት 2፤ 2010 በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማዕከል ኃላፊ ሆኖ የተሾመው ዛዲግ አብርሃ የካቲት 5፤2011ዓም ከድርጅቱ መልቀቁን በጻፈው አምስት ገጽ ደብዳቤ ገልጾዋል። ከዚህኛው ሹመቱ በፊት ዛዲግ፤ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ጦር እንዲዘምት ትዕዛዝ በሰጠው የጦር ወንጀለኛ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ዘመን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ኃላፊ የነበረው ነገሪ ሌንጮ ምክትል በመሆን ሠርቷል። ከዚያም በፊት “የሕዳሴ ግድብ” አስተባባሪ ኃላፊ ሆኖ መሥራቱ … [Read more...] about ህወሓት በክህደት አከርካሪው ተመታ
አወዛጋቢውና ባለጉዳዮች ያልመከሩበት የስደተኞች ሕግ ጉዳይ
የሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት ባለፈው ሳምንት ያፀደቀው “የስደተኞች አዋጅ” ከሚመለከታቸው ባለጉዳዮች ከፍተኛ ተቃውሞ እየደረሰበት ነው። በተለይ የስደተኛ ቁጥር በብዛት በሚገኝባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ የኅልውና ጥያቄ እንዳለባቸው ይናገራሉ። የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችም ስጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ። በፀደቀው አዋጅ መሠረት ማንኛውም ዕውቅና የተሰጠው ስደተኛ ወይም ጥገኝነት ጠያቂ፤ በመረጠው የአገሪቷ አካባቢ የመዘዋወር፣ የመኖሪያ ቤት የመመሥረት፣ መንጃ ፈቃድ የማውጣት፣ የመታወቂያና የውጪ ቪዛ (የጉዞ ሰነድ) የማግኘት፣ የባንክ ሂሳብ የመክፈትና ገንዘብ የማንቀሳቀስ፣ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ዜጎች ጋር ተዋህደው የመኖርና የኢትዮጵያን ዜግነት የመጠየቅ መብት ተሰጥቷቸዋል። አዋጁ ወደ ሥራ የመጣው Road map for the implementation of the Federal Democratic … [Read more...] about አወዛጋቢውና ባለጉዳዮች ያልመከሩበት የስደተኞች ሕግ ጉዳይ
“በማረፊያ ቤት ሰብዓዊ መብታች ተጥሷል”፤ በጥንቃቄ የተዘጋጀ ምግብ በአግባቡና በሰዓቱ አይቀርብልንም – በረከትና ታደሰ
በሌብነት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የዋሉት በረከት ስምዖንና ታደሰ ካሣ “በማረፊያ ቤት ቆይታችን ሰብዓዊ መብታችንን እና ክብራችንን የሚነካ ድርጊት ተፈጽሞብናል” በማለት ለፍርድቤት ቅሬታ አቀረቡ። ጉዳያቸው በአዲስ አበባ እንዲታይ ለፍርድቤቱ ያቀረቡት ጥያቄ ውድቅ ተደርጎ የአስራ አራት ቀን ቀጠሮ ሰጥቷል። በረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ በተጠረጠሩበት የጥረት ኮርፖሬት የሀብት ብክነት ጉዳይ ዛሬ ጥር 17 ቀን 2011 ዓ.ም. በባሕር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። ተጠርጣሪዎቹ ካለባቸው የጤና ችግር አንጻር በጥንቃቄ የተዘጋጀ ምግብ እንደሚመገቡ ገልጸው፤ ይሁንና በማረፊያ ቤቱ ምግብ በአግባቡ እና በሰዓቱ እንደማይቀርብላቸው ተናግረዋል። ለአብነትም ትናንት ምሳ በ10፡00 እንደቀረበላቸው ለችሎቱ አስረድተዋል። የኢኮኖሚ ችግር እንዳለባቸው እና ጡረታ በአግባቡ … [Read more...] about “በማረፊያ ቤት ሰብዓዊ መብታች ተጥሷል”፤ በጥንቃቄ የተዘጋጀ ምግብ በአግባቡና በሰዓቱ አይቀርብልንም – በረከትና ታደሰ










