• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሀዋሳ የጦርነት አውድማ አልሆነችም

July 19, 2019 10:09 am by Editor 2 Comments

በተነሳው ተቃውሞና ግጭት ጉዳት የደረሰባቸው አሉ

የሲዳማን የክልልነት ጥያቄ ለዛሬ ለማወጅ መቀጠሩን ተከትሎ በሐዋሳ እና አካባቢዋ ግጭት ተቃውሞ መከሰቱ ተገለፀ ። ከዚህ ጋር ተያይዞ ከተማዋ የጦርነት አውድማ እንደሆነች ተደርጎ በማኅበራዊ ሚዲያ የሚወራው ሐሰት መሆኑ ተነገረ ።

የጥያቄ አራማጆች ለአዣንስ ፍራንስ ፕረስ እንደገለፁት የሲዳማ ሽማግሌዎች እና ወጣት የጉዳዩ አቀንቃኞች ዛሬ ጠዋት ሊያካሂዱት ያቀዱት ስብሰባ አካባቢውን በዘጉት በፀጥታ ኃይሎች ተደናቅፏል። ባለሥልጣናት ወደዚያ ባለመምጣታቸው፤ እና ወደ መሰብሰቢያው ስፍራም እንዳያልፉ ያገዷቸው የፀጥታ ኃይሎች ላይ ወጣቶቹ ድንጋይ መወርወራቸውንም ዘገባው አመልክቷል።

ሐዋሳ ከተማ ላይ በቁጣ ወደ ጎዳና የወጡት ዜጎች ጎማ በማቃጠል ከፀጥታ ኃይሎች ጋር በተፈጠረው ግጭትም ቢያንስ የአንድ ሰው ሕይወት መጥፋቱን ሌሎች ደግሞ መጎዳታቸውን የሆስፒታል ምንጮች ለዶይቼ ቬለ «DW» ገልጸዋል።

የሐዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዝናው ሳርሚሶ ጭንቅላቱን በጥይት መመታቱ የተገለፀው ተጎጂ ወደ ሐኪም ቤት ከሄደ በኋላ ሕይወቱን ማጣቱን ለሐዋሳው ዘጋቢያችን ሸዋንግዛው ወጋየሁ ገልጸዋል።

«መጀመሪያ ላይ ትንሽ ጭንቅላቱ ላይ የቆሰለ ሰው ገብቷል። እሱ የመጀመሪያ ርዳታ ሰጥተን ወደ ቤቱ ሄዷል። ከዚያ ቀጥሎም ደግሞ አንድ ሴት ነበረች የመጣችው። ባጠቃላይ አራት ወንድ እና አንድ ሴት ነበር የመጡት። አንደኛው ከአዳሬ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የመጣ ከዚያ ሪፈር የተደረገ ሰው ነበረ ጭንቅላቱ ላይ ነበር ቆስሎ የነበረው፤ ቁስሉ አሁን ሀኪሞች እንዳረጋገጡት በጥይት የተመታ ይመስላል። ከፍተኛ የሆነ ቁስል ነው። እሱ አዳሬም ወደ እኛ እንደላከ እኛ ጋርም ብዙ ሳይቆይ ሊያርፍ ችሏል።»

ሌሎቹ ተጎጂዎችን በተመለከተ የሚታየው እስካሁን ለከፋ አደጋ የሚያደርስ እንዳልሆነም አክለው ገልጸዋል። ግጭት ተቃውሞው በሐዋሳ ከተማ የተወሰነ እንዳልሆነ ከአካባቢው የሚወጡ መረጃዎች ያመለክታሉ። ከሚመለከተው የመንግሥት አካል ተገቢውን ምላሽ ካላገኙ ዛሬ ማለትም ሐምሌ 11 ቀን 2011ዓ,ም የሲዳማን ክልልነት ለማወጅ መዘጋጀታቸውን የጉዳዩ ጠያቂዎች ሲያሳስቡ መሰንበታቸው ይታወቃል።

ሐዋሳ ከተማ ሐሙስ ዕለት

ሐሙስ ከቀትር በፊት የሲዳማ አርነት ንቅናቄ ሲአን የሲዳማ ተወላጆች እንዲረጋጉ አሳስቦ ነበር። የሲአን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ደስላኝ ሜሳ የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ጥያቄውን ተቀብሎ ሕዝበ ውሳኔ ለማድረግ እንዲቻል ቅድመ ዝግጅት በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ ለዶቼ ቨለ «DW» አረጋግጠዋል። እንዲያም ሆኖ እስካሁን አካባቢው ስለመረጋጋቱ የተሰማ ነገር የለም።

በሌላ በኩል ሀዋሳ ከተማ የጦርነት_አውድማ እንደሆነች ተደርጎ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሠራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ ነው። በዚህ ፈታኝ ወቅት ሀገሪቱን ወደማያባራ ግጭት ውስጥ እድትገባ ፅኑ ፍላጎት ያላቸው የፌስቡክ አርበኞች በመኖራቸው የምንሰማቸውን መረጃዎች በደንብ ልናጣራ እና ልንመረምራቸው ይገባል በማለት ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያና ተናግረዋል። ግጭቱ ከተነሳ ጀምሮ እስካሁን በሲዳማ ዞን እና ዙሪያው በሚገኙ ከተሞች የኢንተርኔት አገልግሎት እንደተቋረጠ ነው።

©DW

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. አለም says

    July 19, 2019 10:37 pm at 10:37 pm

    ህወሓት 24 ሰኣት በጀሌዎቹ አገር ውስጥና ከአገር ውጭ የጥፋት ወሬ እያሠራጨ ነው። እነርሱ በፈጸሙት ደባና ሌብነት ዶ/ር ዐቢይን እየወነጀሉት ነው። በአዋሳ፣ በአሦሳ፣ በአማራ በሚካሄደው ሁሉ እጃቸው አለበት፡፡ የሌባ ዐይነ ደረቅ መልሶ ልብ ያድርቅ ነው! በምን ተኣምር ነው ዶ/ር ዐቢይ በ1ኣመት ተኩል እነርሱ 27 ኣመት ሲመዘብሩ ዜጋ ላይ ግፍ ሲፈጽሙ የኖሩትን ማቃናት የሚችለው? ይገርማል እኮ! አገር ሁሉ ህወሓትን አይቀበልም አይፈልግም። የሚነዙትን ውሸት ማጋለጥ የያንዳንዳችን ሓላፊነት ነው። ለነገሩ ውዥንብር ይንዙ እንጂ አይሳካላቸውም!! ይህን እነርሱም አውቀውታል! ትልቁ የህወሓት ችግር የትግራይን ሕዝብ እንዴት አፍኖ እንደሚይዝ ነው። አንደኛው ብልሃት በዜና ማሠራጫቸው 24 ሰኣት ወሬ መንዛት ነው። ሌላኛው የጋራ ጠላት መጠፍጠፍ ነው። ሳያስቡ ያደረጉት አንድ መውደቂያቸው ጄኔራል ሰዐረን ትግራይ ወስዶ መቅበር ነው። የሰዐረ ቀብር ፈንጂ ሆኖ ይበትናቸዋል!

    Reply
  2. Segel gazeta says

    July 20, 2019 10:51 am at 10:51 am

    ህወሃት ራሱ ገድሎ፡ «ገደሉት…» ብሎ አስወርቶ፡ አብሮህ ሃዘን የሚቀመጥ ቡድን ነው፡፡ እንዲያም ቢሂን ግን አብይም ቢሆን በርካታና አብዛኛውን ኢትዮጵያዊ ድጋፍ የሚያስገኝለትን እርምጃ መውሰድ አልቻለም፡፡ አንድ አመት ቀላል አይደለም፡፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሤራ አክሻፊው ጎንደር ለሦስተኛ ጊዜ ታሪክ ሠራ May 10, 2023 09:25 am
  • ማር በከፍተኛ ደረጃ የኮንትሮባንድ ሰለባ ሆኗል May 9, 2023 09:24 am
  • ኦነግ በኦሮሚያ ሪፈረንደም እንዲካሄድ መጠየቁ ለሰላም ንግግሩ ዕንቅፋት ሆነ May 4, 2023 01:12 am
  • መረጃ ቲቪ ያጋራው አሳሳች መረጃ May 2, 2023 12:37 pm
  • “ከፈጣሪ በታች መከላከያ የሁላችን ዋስ ጠበቃ ነው፤ ትልቅ ይቅርታ እንጠይቃለን” April 13, 2023 10:19 am
  • በትግራይ የ”ልጆቻችን የት ናቸው?” ጥያቄ እየተሰማ ነው April 13, 2023 08:56 am
  • በትህነግ የፈረሰው የአክሱም ኤርፖርት ያስከተለው ዘርፈብዙ ኪሣራ April 13, 2023 03:21 am
  • “የከተማው ነዋሪ በመሰላቸቱ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ ችግር” ገጥሟቸዋል April 12, 2023 09:23 am
  • ከዕድሜ ልክ እስከ 20 ዓመት ቅጣት ተበይኖባቸዋል April 11, 2023 02:58 pm
  • የኡጋንዳ የክልሎች ሚኒስትር በቆርቆሮ ሌብነት ተጠርጥረው ታሰሩ April 10, 2023 03:59 pm
  • ታከለ ከተነሳ በኋላ የመዐድን ሌቦች እየተያዙ ነው April 6, 2023 02:53 pm
  • አገር ለማተራመስ ያለመ የምሁራን፣ የሚዲያ ባለቤቶችና አክቲቪስቶች ህቡዕ ቡድን ተያዘ April 4, 2023 10:07 am
  • በ10 ዓመት ውስጥ ከ44 ቢሊየን ዶላር በላይ ሸሽቷል April 4, 2023 09:26 am
  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule