• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአል አሙዲ ሃብት በ9.7 ቢሊዮን ዶላር ወደረ!

February 7, 2019 11:18 am by Editor 1 Comment

የኢትዮጵያን ሃብት ከህወሓት ጋር በጥቅም በመመሳጠር ሲበዘብዝ የነበረው መሐመድ አለ አሙዲ (አላሙዲ) እጅግ በርካታ ገንዘብ ከፍሎ በሌብነት ከታሰረበት ሳዑዲ አረቢያ መለቀቁ ተሰምቷል። ከዚህ ጋር በተያያዘ ሲታሰር 10.9 ቢሊዮን ዶላር የነበረው ሃብቱ ሲፈታ 1.2 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል። በፎርብስ ደረጃ አሠጣጥ መሠረት ከእስር በኋላ የ159ኛ ደረጃ ሰጥቶታል። ሆኖም ፎርብስ የአላሙዲ ሃብት በእርግጥ የእርሱ መሆኑን ማረጋገጥ ስላልቻለ በ2018 ከዓለም ቢሊየነሮች ዝርዝር ውስጥ አውጥቶታል።

በአላሙዲን ቀኝ የሚታየው አብነት ነው

በርካታዎች እየሞቱና መብታቸው ተገፍፎ በእስር እየማቀቁ በነበሩበት ወቅት የንብ ካኔተራ በመልበስ የህወሓት ደጋፊነቱን በገሃድ ያስመሰከረው አላሙዲንን ከህወሓት ለይቶ “የሕዝብ ሰው” አድርጎ ማቅረብ ለህወሓት ያለን “ጥላቻ” ከአላሙዲ “ትግሬ” አለመሆን ጋር የተገናኘ ይመስላል የሚሉ ጥቂቶች አይደሉም። ከዚህም አልፎ የዛሬ ሃያ ሰባት ዓመት አካባቢ በኢህአዴግ ሰዎች ሎንዶን ላይ በአብዮታዊ ዲሞክራሲ መጠመቁን የሚናገረውን አላሙዲንን እና ድርጅቶቹን ከኤፈርት ለይቶ ኢትዮጵያዊ አድርጎ ማቅረብ ጭፍንነት ብቻ ሳይሆን ህወሓትን የመቃወሚያው መሠረት አልባነትን የሚያሳይ እንደሆነ ድምጻቸው የታፈነ ጥቂቶች ሲናገሩት የቆዩት ጉዳይ ነው። አላሙዲንና ሚድሮክን የምናሞግስ ከሆነ ስብሃት ነጋንና ኤፈርትን ልንቃወም የምንችልበት መሥፈርት የለንም በማለት እነዚሁ ወገኖች መከራከሪያቸውን ያቀርባሉ።

ከዚህ አንጻር ግለሰቡ የሳዑዲውን የሌብነት ወንጀል ያደረሰበትን የሞራል ዝቅጠት ተቋቁሞ ወደ ኢትዮጵያ የሚመለስ ከሆነ በበርካታ ወንጀሎች ሊጠየቅ ይገባዋል የሚሉ ጥቂቶች አይደሉም። በሸራተን ሆቴል ይሠራል ከሚባለው እጅግ የዘቀጡ ኢሞራላዊ ተግባራት ጀምሮ የኢትዮጵያ ሃብት እስከ መዝረፍ እንዲሁም ከመሬት ነጠቃ ጋር በማያያዝ በበርካታ ወንጀሎች ክስ ሊመሰረትበት ይገባል የሚሉት ወገኖች አላሙዲ ከህወሓት ጋር በመሆን ከፍተኛ የኢኮኖሚ በደል ያደረሰ ሰው ነው ይላሉ።

ፎርብስ መጽሔትን በመጥቀስ ሪፖርተር ያቀናበረው ዘገባ እንዲህ ይነበባል።

እሑድ ጥር 19 ቀን 2011 ዓ.ም. ከአንድ ዓመት ከሁለት ወራት በላይ ታስረው የተለቀቁት ሼክ መሐመድ ሁሴን ዓሊ አል አሙዲ፣ ከእስር ነፃ ለመውጣት ከፍተኛ ገንዘብ መክፈላቸው ተሰማ። ባለፈው ዓመት 10.9 ቢሊዮን ዶላር ሀብት የነበራቸው ሼክ አል አሙዲ፣ በአሁኑ ወቅት በፎርብስ የቢሊየነሮች ዝርዝር ላይ በ1.2 ቢሊዮን ዶላር ሀብት 159ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል። ፎርብስ እ.ኤ.አ. በ2018 ሼክ አል አሙዲ ከቢሊየነሮች ዝርዝር ውስጥ ማስወጣቱ ይታወሳል። በሰጠው ምክንያትም የትኛው ሀብት የእሳቸው እንደሆነ ግልጽነት ባለመኖሩ ነው ብሏል።

የሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት ባካሄደው የፀረ ሙስና ዘመቻ በቁጥጥር ሥር ከዋሉ ባለሀብቶች አንዱ የሆኑት ሼክ አል አሙዲ፣ ምን ያህል ገንዘብ ለሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት ግን እንደከፈሉ ማወቅ አልተቻለም። ለሀብታቸው በከፍተኛ መጠን ማሽቆልቆል ምክንያት ግን ምናልባት ለነፃነታቸው ከፍተኛ ገንዘብ መክፈላቸው ሳይሆን እንዳልቀረ ውስጥ አዋቂዎች ይናገራሉ። የሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥት በፀረ ሙስና ዘመቻው ከ100 ቢሊዮን ዶላር በላይ ሳያገኝ እንዳልቀረ ይገመታል።

ሼክ አል አሙዲ በእስር በነበሩባቸው ጊዜያት ከሁለት ቢሊዮን ዶላር በላይ ኢንቨስት ባደረጉባት ኢትዮጵያ መጠነ ሰፊ የፖለቲካ አመራር ለውጥ ተካሂዷል። በፖለቲካ ለውጡ ሒደት በነበረው ሕዝባዊ አመፅ የሼክ አሊ አሙዲ የተወሰኑ ንብረቶች ሰለባ ሆነዋል። የፖለቲካ አመራር ለውጥ ከተደረገ በኋላም ለአገሪቱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ የሚያስገኘው የሚድሮክ ጎልድ የለገደንቢ ወርቅ ማምረቻ በአካባቢና በሰዎች ላይ አድርሷል በተባለ ተፅዕኖ ምክንያት ሲታገድ፣ በአዲስ አበባ ከተማ ለዓመታት ታጥረው የቆዩ 11 ቦታዎች ደግሞ ካርታቸው መክኗል።

የሼክ አል አሙዲ የቅርብ ሰው የሆኑት አቶ አብነት ገብረ መስቀል ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በአሁኑ ወቅት ሼኩ ጂዳ በሚገኘው መኖርያ ቤታቸው ከቤተሰቦቻቸው ጋር ጊዜያቸውን እያሳለፉ ነው።

“ጤናቸው በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል፣ ሞራላቸውም እንደዚያው። ፕሮግራማቸውን አሁን መናገር ባይቻልም ከተወሰኑ ቀናት በኋላ ወደ አገራቸው ይመጣሉ፤” በማለት የገለጹት አቶ አብነት፣ “ሼክ አል አሙዲ አገራቸው ከመጡ በኋላ በአገሪቱ የመጣውን ለውጥ ተከትለው ሥራቸውን ማካሄድ ይጀምራሉ፤” ብለዋል። ምንም እንኳን አቶ አብነት ሼክ አል አሙዲ ወደ ኢትዮጵያ ይመለሳሉ ይበሉ እንጂ፣ በሳዑዲ መንግሥት የፀረ ሙስና ዘመቻ ከታሰሩት መካከል አብዛኛዎቹ እስካሁን ከሳዑዲ ዓረቢያ መውጣት አይችሉም። በተመሳሳይም ሼክ አል አሙዲ ከሳዑዲ እንዳይወጡ ዕገዳ ሊደረግባቸው ይችላል የሚሉ ግምቶች አሉ።

“የቆሙ ሥራዎችና የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች በሙሉ በተካሄደው አገራዊ ለውጥ መሠረት ሥራቸው ይጀመራል፤” በማለት የገለጹት አቶ አብነት፣ “ሼክ አል አሙዲ ባልነበሩባቸው ጊዜያት በኢትዮጵያ የሚገኙት ድርጅቶቻቸው ሥራቸውን በአግባቡ በመሥራት አትራፊ ሆነው ቀጥለዋል፤” ሲሉ አብራርተዋል።

ሼክ አል አሙዲ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ደርግ ሥልጣን ላይ በነበረበት ጊዜ ቢሆንም፣ ሙሉ ለሙሉ ወደ ኢንቨስትመንት ከገቡ 25 ዓመታት ተቆጥረዋል። ባለሀብቱ 105 የሚጠጉ ኩባንያዎችን በአራት ግሩፖች አዋቅረዋል። በእነዚህ ኩባንያዎች ከ50 ሺሕ በላይ ሠራተኞች የሚተዳደሩ ሲሆን፣ ከመንግሥት ቀጥሎ በኢትዮጵያ ትልቁ ቀጣሪ አድርጓቸዋል። (ሪፖርተር)

አብነት ይህንን ቢልም በገሃድ የሚታየው ሁኔታ ግን ይህ አይደለም በማለት የሚሞግቱ ጥቂቶች አይደሉም። ከለገደንቢ ጋር ተያይዞ በወርቅ ላይ ይደረግ ነበር የሚባልለት የወርቅ ዘረፋ አላሙዲንን በከፍተኛ ሁኔታ አክስሮታል። አብረውት በሃብት ዘረፋው ላይ የበላይነትን ተቀዳጅተው የነበሩት የህወሓት ሰዎች ትግራይ ራሳቸውን በፈቃዳቸው አስረው ለራሳቸውም “አዳኝ” እየተመኙ ነው። ሲታመም “አንጠልጥሎ ደቡብ አፍሪካ” ያሳከመው በረከት ስምዖንም “ንጽህናው አልተጠበቀም” ያለውን ምግብ እየበላ በሌብነት የተከሰሰበትን ጉዳይ እየተከታተለ ይገኛል። ከፒያሳ ጀምሮ እስከ ተለያዩ የኢትዮጵያ ቦታዎች ላይሠራ ለዓመታት አጥሮ ያስቀመጣቸው ባዶ ቦታዎች ተወርሰዋል። እንደ ዱሮው በአንድ ቀጭን ስልክ ማስመለስ አለመቻል ብቻ ሳይሆን የማይታሰብ ሃቅ ሆኗል።

በእነዚህና በሌሎች እጅግ በርካታ ምክንቶች የሳዑዲ መንግሥት ከአገር የመውጣት መብቱን ባይከለክለው እንኳን አላሙዲ ወደ ኢትዮጵያ አይመለስም የሚሉ ጥቂቶች አይደሉም። በሌብነት ተከስሶ ከተወነጀለበት ሞራል የሚነካ ክስ ጀምሮ እስከ ህወሓት መክሰም ድረስ በአላሙዲን ላይ የደረሰው ይህ ነው የማይባል ናዳ ማንም ከሚገምተው በላይ ሁኔታውን ውስብስብ አድርጎታል። በመሆኑን ኢትዮጵያ መንግሥት ተገቢውን ክስ በመመሥረት በተወካ እንዲከራከር አድርጎ ሃብቱን ለሕዝብ ጥቅም ቢያውለው ተገቢና መደረግ ያለበት ተግባር ነው በማለት የፖለቲካም የሕግም አስተያየት እየተሰጠ ይገኛል።

ማስታወሻ፤ አላሙዲንን “አንተ” ብለን መጥራታችን ለሚያሳስባችሁ ይህንን እንድታነቡ ይሁን።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

 

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: azeb al amoudi, effort, Full Width Top, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. gi Haile says

    February 7, 2019 07:15 pm at 7:15 pm

    ሌባ ሌባ ነው። የተዘረፈው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሐብት ነው ወርቁን ከወለጋ ወሰዶ የወለጋን ሕዝብ አስርቦና አስገድሎ በለቤት ያልሆነውን እንደከብሩ መድረግ ከወንጀልም የከፋ ወንጀል ነው። ይህ ወንጀል ደግሞ ከአገራችን አልፎ በአለም አቀፍ ደረጃ የተደረገ በመሆኑ ነገሮችን ውስብስብ አድርጓታል። የአገር ሐብት አዘርፎ ሐብታም ከሆኑ በኃላ ገንዘብን አንደ አሸዋ በየቦታው በመበተን ለዝሙትና ታወቂ ሰዎችን ለማሳከም፣ ቆንጆ ሴት ፈልጎ በገንዘብ አጥምዶ መድፈር፣ ለልማት ሳይውል ተዘግቶ ለኣመታት የቆየ መሬቶች ተክስ ገቢ አለመደረጉ። ከዘረፋ ድርጅቶች ሕገሠዊ መስሎ ለመታየት መሞከር የእስልምና እምነት ተከታይ ነኝ የሚልን ሰው በሕሪይ አይወክልም። ኣሳፋሪ ተግባር ነው ከዚህም በላይ የመንጸስና የሞራል ውድቀት በላይ ኪሳራ የለም። አብታችንን ለሰውዲ ኣረቢያ ኣሸፈሳልፎ መስጠቱ ደግሞ ሌላው ኸንጀል ነው። ሰለዚህ 9 ቢሊዮን ዶላር የኢትዮጵያ ሐብት ሊሆን ይችላል።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule