• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለህወሃትና አገልጋዮቹ “አንቱታን” ነፈግን

October 5, 2016 10:52 pm by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ልዩ መጠሪያዎች ከሚባሉት መካከል “ሰው አክባሪነት” አንዱ ነው፡፡ በበርካታው የአገራችን ባህል ሰዎች በዕድሜያቸው የአንቱነትን ማዕረግ ይጎናጸፋሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ በሥራቸው፣ በሙያቸው፣ በሕዝብ ዘንድ ባላቸው ከበሬታ ይህ የአንቱነት ማዕረግ ይሰጣቸዋል፡፡ በዕድሜያቸው በጣም ልጆች የሆኑ እንኳን ባላቸው መንፈሣዊ አገልግሎት ወይም ልዕልና በታላላቆቻቸው ሳይቀር አንቱ ይባላሉ፡፡

የመንግሥት ባለሥልጣናትን አንቱ ብሎ መጥራት ለኢትዮጵያዊ የሚነገረው ወይም የሚማረው ግብረገብ አይደለም፡፡ እንደ ህወሃት ዓይነቱን ግን “መንግሥት”፣ “አስተዳደር” ብሎ መጥራት በሕዝብ መቀለድ ነው፡፡ የሕዝብ ይሁንታ የሌለው፤ ሕዝብ አንቅሮ የተፋው፣ በግድ መቶ በመቶ እወደዳለሁ ብሎ ሥልጣን በአፈሙዝ የነጠቀ ወንበዴና የወንበዴዎች ስብስብ “አገዛዝ” መባል ሲበዛበት ነው፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ለሕዝብ አገልግሎት መሥጠት ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ህወሃት/ኢህአዴግን “መንግሥት” ብሎ ጠርቶ አያውቅም፡፡ እስካሁን ባወጣናቸው የዜና ዘገባዎች ላይ “የህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ” ከማለት ያለፍንበት ጊዜ የለም – በእኛ ዕምነት ተገቢው መጠሪያ ይኸው ነው፡፡ ወደፊትም በዚሁ እንቀጥላለን፡፡

“በቃ፤ አልፈልግህም፤ ውረድ” የተባለን አንድ የወንበዴ ቡድን አባላት እንደ ባለሥልጣን እስካሁን “አንቱ” እያልን ስንጠራ ቆይተናል፡፡ ሆኖም በእሁዱ የኢሬቻ በዓል ላይ የወንበዴው ቡድን አባላት በሕዝብ ላይ በፈጸሙት በቃላት ለመግለጽ የሚያዳግት ግፍ ታሪካቸውን በሕዝብ ደም ጽፈዋል፡፡ እያንዳንዳቸውም “ነፍሰ ገዳይ ወንበዴ እንጂ አንቱ መባል የሚገባኝ የመንግሥት ባለሥልጣን አይደለሁም” የሚል እንድምታ ያለው ተግባራቸውን ለኢትዮጵያ ሕዝብ አሳይተዋል፡፡

ይህ ብቻ አይደለም፤ በብሔራዊ ሚዲያ “በስብሰናል፣ ገምተናል፣ …” እና ሌሎች እዚህ ላይ መጥቀስ የማንችላቸውን ጸያፍ ንግግሮች በማድረግ ወጣቱን ትውልድ ብልግና፣ ውሸት፣ ስድብ፣ … በተደጋጋሚ ያስተማሩ በመሆናቸው፤ ዕድሜ ሊለውጣቸው የማይችል እንኳን አገርን መምራት ራሳቸውን ለመምራት የማይችሉ ብልሹዎች በመሆናቸው፣ የሰውነት ስነምግባር የሌላቸው፣ እንደ ሰው የማያዝኑ፣ የሰው ስቃይ የማይሰማቸው፣ ሰው መሆን ከውስጣቸው ተመጥጦ የወጣና በራሳቸው አምሳያ ሌሎችን እየቀረጹ የመጡ ለርኩሰታቸው ወደር የሌላቸው ውርደትና ፍጹም ራስወዳድነት ጠፍንጎ የያዛቸው መሆናቸውን በድርጊታቸው ያለ አንዳች ጥርጣሬ የመሰከሩ ሆነዋል፡፡

በመሆኑም ከህወሃት አገዛዝ በይፋ ተላቅቀው ከወጡት በስተቀር ከአሁን ጀምሮ የህወሃት/ኢህአዴግ ወንበዴ ሹመኞችን “አንቱ” የሚለውን የኢትዮጵያዊነት የከበሬታ ስያሜ የነፈግን መሆኑ የተከበራችሁ አንባቢዎቻችን እንድታውቁልን እንወዳለን፡፡ ይህንን አሠራር ከእሁድ መስከረም 22፤ 2009ዓም ጀምሮ ተግባራዊ አድርገናል፡፡

ለመከበር “ሰከን በሉ”!

“የዜጎችህን እምነት ካጣህ በኋላ አክብሮታቸውንም መቼም ቢሆን መልሰህ ማግኘት አትችልም፡፡” አብርሃም ሊንከን

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Editorial, Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule