• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለህወሃትና አገልጋዮቹ “አንቱታን” ነፈግን

October 5, 2016 10:52 pm by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ልዩ መጠሪያዎች ከሚባሉት መካከል “ሰው አክባሪነት” አንዱ ነው፡፡ በበርካታው የአገራችን ባህል ሰዎች በዕድሜያቸው የአንቱነትን ማዕረግ ይጎናጸፋሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ በሥራቸው፣ በሙያቸው፣ በሕዝብ ዘንድ ባላቸው ከበሬታ ይህ የአንቱነት ማዕረግ ይሰጣቸዋል፡፡ በዕድሜያቸው በጣም ልጆች የሆኑ እንኳን ባላቸው መንፈሣዊ አገልግሎት ወይም ልዕልና በታላላቆቻቸው ሳይቀር አንቱ ይባላሉ፡፡

የመንግሥት ባለሥልጣናትን አንቱ ብሎ መጥራት ለኢትዮጵያዊ የሚነገረው ወይም የሚማረው ግብረገብ አይደለም፡፡ እንደ ህወሃት ዓይነቱን ግን “መንግሥት”፣ “አስተዳደር” ብሎ መጥራት በሕዝብ መቀለድ ነው፡፡ የሕዝብ ይሁንታ የሌለው፤ ሕዝብ አንቅሮ የተፋው፣ በግድ መቶ በመቶ እወደዳለሁ ብሎ ሥልጣን በአፈሙዝ የነጠቀ ወንበዴና የወንበዴዎች ስብስብ “አገዛዝ” መባል ሲበዛበት ነው፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ለሕዝብ አገልግሎት መሥጠት ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ህወሃት/ኢህአዴግን “መንግሥት” ብሎ ጠርቶ አያውቅም፡፡ እስካሁን ባወጣናቸው የዜና ዘገባዎች ላይ “የህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ” ከማለት ያለፍንበት ጊዜ የለም – በእኛ ዕምነት ተገቢው መጠሪያ ይኸው ነው፡፡ ወደፊትም በዚሁ እንቀጥላለን፡፡

“በቃ፤ አልፈልግህም፤ ውረድ” የተባለን አንድ የወንበዴ ቡድን አባላት እንደ ባለሥልጣን እስካሁን “አንቱ” እያልን ስንጠራ ቆይተናል፡፡ ሆኖም በእሁዱ የኢሬቻ በዓል ላይ የወንበዴው ቡድን አባላት በሕዝብ ላይ በፈጸሙት በቃላት ለመግለጽ የሚያዳግት ግፍ ታሪካቸውን በሕዝብ ደም ጽፈዋል፡፡ እያንዳንዳቸውም “ነፍሰ ገዳይ ወንበዴ እንጂ አንቱ መባል የሚገባኝ የመንግሥት ባለሥልጣን አይደለሁም” የሚል እንድምታ ያለው ተግባራቸውን ለኢትዮጵያ ሕዝብ አሳይተዋል፡፡

ይህ ብቻ አይደለም፤ በብሔራዊ ሚዲያ “በስብሰናል፣ ገምተናል፣ …” እና ሌሎች እዚህ ላይ መጥቀስ የማንችላቸውን ጸያፍ ንግግሮች በማድረግ ወጣቱን ትውልድ ብልግና፣ ውሸት፣ ስድብ፣ … በተደጋጋሚ ያስተማሩ በመሆናቸው፤ ዕድሜ ሊለውጣቸው የማይችል እንኳን አገርን መምራት ራሳቸውን ለመምራት የማይችሉ ብልሹዎች በመሆናቸው፣ የሰውነት ስነምግባር የሌላቸው፣ እንደ ሰው የማያዝኑ፣ የሰው ስቃይ የማይሰማቸው፣ ሰው መሆን ከውስጣቸው ተመጥጦ የወጣና በራሳቸው አምሳያ ሌሎችን እየቀረጹ የመጡ ለርኩሰታቸው ወደር የሌላቸው ውርደትና ፍጹም ራስወዳድነት ጠፍንጎ የያዛቸው መሆናቸውን በድርጊታቸው ያለ አንዳች ጥርጣሬ የመሰከሩ ሆነዋል፡፡

በመሆኑም ከህወሃት አገዛዝ በይፋ ተላቅቀው ከወጡት በስተቀር ከአሁን ጀምሮ የህወሃት/ኢህአዴግ ወንበዴ ሹመኞችን “አንቱ” የሚለውን የኢትዮጵያዊነት የከበሬታ ስያሜ የነፈግን መሆኑ የተከበራችሁ አንባቢዎቻችን እንድታውቁልን እንወዳለን፡፡ ይህንን አሠራር ከእሁድ መስከረም 22፤ 2009ዓም ጀምሮ ተግባራዊ አድርገናል፡፡

ለመከበር “ሰከን በሉ”!

“የዜጎችህን እምነት ካጣህ በኋላ አክብሮታቸውንም መቼም ቢሆን መልሰህ ማግኘት አትችልም፡፡” አብርሃም ሊንከን

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial, Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule