• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለህወሃትና አገልጋዮቹ “አንቱታን” ነፈግን

October 5, 2016 10:52 pm by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ልዩ መጠሪያዎች ከሚባሉት መካከል “ሰው አክባሪነት” አንዱ ነው፡፡ በበርካታው የአገራችን ባህል ሰዎች በዕድሜያቸው የአንቱነትን ማዕረግ ይጎናጸፋሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ በሥራቸው፣ በሙያቸው፣ በሕዝብ ዘንድ ባላቸው ከበሬታ ይህ የአንቱነት ማዕረግ ይሰጣቸዋል፡፡ በዕድሜያቸው በጣም ልጆች የሆኑ እንኳን ባላቸው መንፈሣዊ አገልግሎት ወይም ልዕልና በታላላቆቻቸው ሳይቀር አንቱ ይባላሉ፡፡

የመንግሥት ባለሥልጣናትን አንቱ ብሎ መጥራት ለኢትዮጵያዊ የሚነገረው ወይም የሚማረው ግብረገብ አይደለም፡፡ እንደ ህወሃት ዓይነቱን ግን “መንግሥት”፣ “አስተዳደር” ብሎ መጥራት በሕዝብ መቀለድ ነው፡፡ የሕዝብ ይሁንታ የሌለው፤ ሕዝብ አንቅሮ የተፋው፣ በግድ መቶ በመቶ እወደዳለሁ ብሎ ሥልጣን በአፈሙዝ የነጠቀ ወንበዴና የወንበዴዎች ስብስብ “አገዛዝ” መባል ሲበዛበት ነው፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ለሕዝብ አገልግሎት መሥጠት ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ህወሃት/ኢህአዴግን “መንግሥት” ብሎ ጠርቶ አያውቅም፡፡ እስካሁን ባወጣናቸው የዜና ዘገባዎች ላይ “የህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ” ከማለት ያለፍንበት ጊዜ የለም – በእኛ ዕምነት ተገቢው መጠሪያ ይኸው ነው፡፡ ወደፊትም በዚሁ እንቀጥላለን፡፡

“በቃ፤ አልፈልግህም፤ ውረድ” የተባለን አንድ የወንበዴ ቡድን አባላት እንደ ባለሥልጣን እስካሁን “አንቱ” እያልን ስንጠራ ቆይተናል፡፡ ሆኖም በእሁዱ የኢሬቻ በዓል ላይ የወንበዴው ቡድን አባላት በሕዝብ ላይ በፈጸሙት በቃላት ለመግለጽ የሚያዳግት ግፍ ታሪካቸውን በሕዝብ ደም ጽፈዋል፡፡ እያንዳንዳቸውም “ነፍሰ ገዳይ ወንበዴ እንጂ አንቱ መባል የሚገባኝ የመንግሥት ባለሥልጣን አይደለሁም” የሚል እንድምታ ያለው ተግባራቸውን ለኢትዮጵያ ሕዝብ አሳይተዋል፡፡

ይህ ብቻ አይደለም፤ በብሔራዊ ሚዲያ “በስብሰናል፣ ገምተናል፣ …” እና ሌሎች እዚህ ላይ መጥቀስ የማንችላቸውን ጸያፍ ንግግሮች በማድረግ ወጣቱን ትውልድ ብልግና፣ ውሸት፣ ስድብ፣ … በተደጋጋሚ ያስተማሩ በመሆናቸው፤ ዕድሜ ሊለውጣቸው የማይችል እንኳን አገርን መምራት ራሳቸውን ለመምራት የማይችሉ ብልሹዎች በመሆናቸው፣ የሰውነት ስነምግባር የሌላቸው፣ እንደ ሰው የማያዝኑ፣ የሰው ስቃይ የማይሰማቸው፣ ሰው መሆን ከውስጣቸው ተመጥጦ የወጣና በራሳቸው አምሳያ ሌሎችን እየቀረጹ የመጡ ለርኩሰታቸው ወደር የሌላቸው ውርደትና ፍጹም ራስወዳድነት ጠፍንጎ የያዛቸው መሆናቸውን በድርጊታቸው ያለ አንዳች ጥርጣሬ የመሰከሩ ሆነዋል፡፡

በመሆኑም ከህወሃት አገዛዝ በይፋ ተላቅቀው ከወጡት በስተቀር ከአሁን ጀምሮ የህወሃት/ኢህአዴግ ወንበዴ ሹመኞችን “አንቱ” የሚለውን የኢትዮጵያዊነት የከበሬታ ስያሜ የነፈግን መሆኑ የተከበራችሁ አንባቢዎቻችን እንድታውቁልን እንወዳለን፡፡ ይህንን አሠራር ከእሁድ መስከረም 22፤ 2009ዓም ጀምሮ ተግባራዊ አድርገናል፡፡

ለመከበር “ሰከን በሉ”!

“የዜጎችህን እምነት ካጣህ በኋላ አክብሮታቸውንም መቼም ቢሆን መልሰህ ማግኘት አትችልም፡፡” አብርሃም ሊንከን

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial, Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule