• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለህወሃትና አገልጋዮቹ “አንቱታን” ነፈግን

October 5, 2016 10:52 pm by Editor Leave a Comment

የኢትዮጵያ ልዩ መጠሪያዎች ከሚባሉት መካከል “ሰው አክባሪነት” አንዱ ነው፡፡ በበርካታው የአገራችን ባህል ሰዎች በዕድሜያቸው የአንቱነትን ማዕረግ ይጎናጸፋሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ በሥራቸው፣ በሙያቸው፣ በሕዝብ ዘንድ ባላቸው ከበሬታ ይህ የአንቱነት ማዕረግ ይሰጣቸዋል፡፡ በዕድሜያቸው በጣም ልጆች የሆኑ እንኳን ባላቸው መንፈሣዊ አገልግሎት ወይም ልዕልና በታላላቆቻቸው ሳይቀር አንቱ ይባላሉ፡፡

የመንግሥት ባለሥልጣናትን አንቱ ብሎ መጥራት ለኢትዮጵያዊ የሚነገረው ወይም የሚማረው ግብረገብ አይደለም፡፡ እንደ ህወሃት ዓይነቱን ግን “መንግሥት”፣ “አስተዳደር” ብሎ መጥራት በሕዝብ መቀለድ ነው፡፡ የሕዝብ ይሁንታ የሌለው፤ ሕዝብ አንቅሮ የተፋው፣ በግድ መቶ በመቶ እወደዳለሁ ብሎ ሥልጣን በአፈሙዝ የነጠቀ ወንበዴና የወንበዴዎች ስብስብ “አገዛዝ” መባል ሲበዛበት ነው፡፡

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ለሕዝብ አገልግሎት መሥጠት ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ህወሃት/ኢህአዴግን “መንግሥት” ብሎ ጠርቶ አያውቅም፡፡ እስካሁን ባወጣናቸው የዜና ዘገባዎች ላይ “የህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ” ከማለት ያለፍንበት ጊዜ የለም – በእኛ ዕምነት ተገቢው መጠሪያ ይኸው ነው፡፡ ወደፊትም በዚሁ እንቀጥላለን፡፡

“በቃ፤ አልፈልግህም፤ ውረድ” የተባለን አንድ የወንበዴ ቡድን አባላት እንደ ባለሥልጣን እስካሁን “አንቱ” እያልን ስንጠራ ቆይተናል፡፡ ሆኖም በእሁዱ የኢሬቻ በዓል ላይ የወንበዴው ቡድን አባላት በሕዝብ ላይ በፈጸሙት በቃላት ለመግለጽ የሚያዳግት ግፍ ታሪካቸውን በሕዝብ ደም ጽፈዋል፡፡ እያንዳንዳቸውም “ነፍሰ ገዳይ ወንበዴ እንጂ አንቱ መባል የሚገባኝ የመንግሥት ባለሥልጣን አይደለሁም” የሚል እንድምታ ያለው ተግባራቸውን ለኢትዮጵያ ሕዝብ አሳይተዋል፡፡

ይህ ብቻ አይደለም፤ በብሔራዊ ሚዲያ “በስብሰናል፣ ገምተናል፣ …” እና ሌሎች እዚህ ላይ መጥቀስ የማንችላቸውን ጸያፍ ንግግሮች በማድረግ ወጣቱን ትውልድ ብልግና፣ ውሸት፣ ስድብ፣ … በተደጋጋሚ ያስተማሩ በመሆናቸው፤ ዕድሜ ሊለውጣቸው የማይችል እንኳን አገርን መምራት ራሳቸውን ለመምራት የማይችሉ ብልሹዎች በመሆናቸው፣ የሰውነት ስነምግባር የሌላቸው፣ እንደ ሰው የማያዝኑ፣ የሰው ስቃይ የማይሰማቸው፣ ሰው መሆን ከውስጣቸው ተመጥጦ የወጣና በራሳቸው አምሳያ ሌሎችን እየቀረጹ የመጡ ለርኩሰታቸው ወደር የሌላቸው ውርደትና ፍጹም ራስወዳድነት ጠፍንጎ የያዛቸው መሆናቸውን በድርጊታቸው ያለ አንዳች ጥርጣሬ የመሰከሩ ሆነዋል፡፡

በመሆኑም ከህወሃት አገዛዝ በይፋ ተላቅቀው ከወጡት በስተቀር ከአሁን ጀምሮ የህወሃት/ኢህአዴግ ወንበዴ ሹመኞችን “አንቱ” የሚለውን የኢትዮጵያዊነት የከበሬታ ስያሜ የነፈግን መሆኑ የተከበራችሁ አንባቢዎቻችን እንድታውቁልን እንወዳለን፡፡ ይህንን አሠራር ከእሁድ መስከረም 22፤ 2009ዓም ጀምሮ ተግባራዊ አድርገናል፡፡

ለመከበር “ሰከን በሉ”!

“የዜጎችህን እምነት ካጣህ በኋላ አክብሮታቸውንም መቼም ቢሆን መልሰህ ማግኘት አትችልም፡፡” አብርሃም ሊንከን

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial, Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule