• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሚድሮክ ልዑክ ለአባዱላ ያቀረቡት ጥያቄ

February 4, 2013 09:06 am by Editor 1 Comment

የሚድሮክ ኢትዮጵያ የበላይ አመራሮች አባዱላ ገመዳን ለማነጋገር ቀጠሮ አስይዘው የተወሰኑ ባለስልጣናት ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ጠይቀው እንደነበር የጎልጉል ምንጮች አስታወቁ። በኦሮሚያ የሚገኙ የሼኽ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ ንብረት የተባሉ ድርጅቶች ላይ የተደረጉ የሂሳብ ምርመራዎችና ግብር ታሪፍ የተሰራባቸው ሰነዶች ዝርፊያ ምርመራ ተድበስብሶ እንዲታፈን መደረጉ እስካሁን ምላሽ ያላገኘ ጉዳይ እንደሆነ ተጠቆመ።

አባዱላ ገመዳ የኦሮሚያ ፕሬዚዳንት በነበሩበት ወቅት ሚድሮክ የሰየማቸውና በዶ/ር አረጋ የሚመራ ልዑክ ቢሯቸው የተገኘው በወቅቱ የሼክ መሀመድ ድርጅቶች ላይ ክልሉ ግብር እንዲከፍሉ ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ነበር። የክልሉ ካቢኔ ግብር መክፈል የሚገባቸው ባለሃብቶች በሙሉ ሊከፍሉ የሚገባቸውን ውዝፍ እዳ ገቢ እንዲያደርጉ ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ክልሉ ውስጥ የሚገኙትን የንግድ ድርጅቶች መዝገብ መርምሮ ነበር።

በወቅቱ የተላለፈውን ውሳኔና የውሳኔውን ትግበራ በቅርበት የሚያውቁ የጎልጉል የመረጃ ምንጮች እንዳሉት የሚድሮክ ሃላፊዎች አባዱላ ቢሮ በመሄድ ስም በመጥቀስ የተወሰኑ የክልሉ ቢሮ ሃላፊዎች ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ጠይቀዋል። ምንጮቹ እንደሚሉት በሙስና ሰበብ በእስር ላይ የሚገኙትን የገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ቀዳሚው ተጠቃሽ ናቸው።

የሚድሮክ ስምና የባለሃብቱ ስም በሚዲያ እንዲጎድፍ አድርገዋል ያሏቸውን ክልሉን ባለስልጣናት ከሃላፊነታቸው እንዲያነሱላቸው የጠየቁት የሚድሮክ ሃላፊዎች አባዱላ በሰጡት መልስ ተበሳጭተው ነበር። አባዱላ ግብር መክፈል ግዴታ እንደሆነ፣ ይህ አቋም በካቢኔ ታምኖበት እንዲተገበር ከውሳኔ ላይ የተደረሰበት መሆኑንና ባለስልጣኖችን የመሾምና የማንሳት ጉዳይ የሚድሮክ ሳይሆን የክልሉ ስራ መሆኑንን ገልጸው የሚድሮክ ሰዎችን እንዳሰናበቱ ምንጮቹ አስታውቀዋል።

በኦህዴድ አባላት ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት የነበራቸው አባዱላ ከክልሉ ፕሬዚዳንትነታቸው የተነሱበት ዋና ምክንያት በሼኽ መሐመድ ላይ ባላቸው አቋም የተነሳ እንደሆነ የሚጠቁሙት ክፍሎች፣ አባዱላ ለሚድሮክ ሰዎች “የሚያጥወለውል” መልስ ሲመልሱ ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ከተጠየቁት መካከል የተወሰኑት ባለሥልጣኖች በተገኙበት መሆኑ የጀመሩትን የግብር ማስከፈል ስራ አጠናክረው እንዲሰሩ ሞራል ሆኗቸው እንደነበር ይናገራሉ።

ጨለለቅ አልሳም ታወር (ፎቶ:የሰነድ ምዝገባ)

በዚሁ መሰረት አላሙዲ በኢንቨስትመንት ስም አጥረው ባኖሩዋቸው ሰፋፊ መሬቶች፣ በኤልፎራ ዶሮ ርቢ፣ በኤልፎራ ቄራ፣ በተለያዩ የከብት ማደለቢያ ኳራንቲዎችና በመልጌ ወንዶ፣ የሆራ ሃይቅ ወዘተ በወቅቱ ለክልሉ ገቢ ያላደረጉት የአስራ አንድ ዓመት የመሬት ግብር እንዲከፍሉ የሂሳብ ሰነድ ይዘጋጃል። ከሌሎች በክልሉ የመሬት ግብር ካልከፈሉ ባለሃብቶችና ድርጅቶች ጋር ባንድነት ተመርምሮ የተዘጋጀው የግብር ተመን የሂሳብ ሰነድ ሜክሲኮ ጨለለቅ አልሳም (ታወር) ህንጻ በነበረው የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ ዘንድ ለውሳኔ እንደደረሱ ያልተጠበቀ ወሬ ተሰማ።

በወቅቱ የገቢዎች ቢሮ ህግ ክፍል ይሰሩ ከነበሩት መካከል ስማቸው እንዳይጠቀስ በመጠየቅ እንዳሉት “የሃላፊው ቢሮ ሳይሰበር በሩ ተከፍቶ ሰነዶቹ ተዘርፈዋል” ጉዳዩን ህግ ዘንድ እንዴት እንደተያዘ ሲከታተሉ ከነበሩት መካከል አንዱ ለጎልጉል እንደተናገሩት “የበርካታ ባለሃብቶችና ድርጅቶች የሂሳብ ምርመራ ሰነዶች አንድ ላይ ከተቀመጡበት የቢሮው ሃላፊ ውስጥ ተመርጦ የተዘረፈው የሼኽ መሀመድ ንብረት የሆኑት ድርጅቶች የሂሳብ ማህደሮች ብቻ መሆናቸው ነው፡፡”

“ቢሮው በቁልፍ ተከፍቶ ስለመዘረፉ ከበቂ በላይ ምልክቶች ነበሩ” የሚሉት እነዚህ ክፍሎች ሃላፊው ቢሯቸውን ቆልፈው ከወጡ በኋላ ዝርፊያው ሲከናወን ቁልፍ ከየት ተገኝቶ ቢሮው ተከፈተ? የሚል ጥያቄ ተነስቶ ነበር። የመጠባበቂያ ቁልፍ ያለው የህንጻው ባለቤት በሆነው አልሳም ኢንተርናሽናል ዘንድ ብቻ እንደሆነ የሚናገሩት እነዚህ ክፍሎች፣ “ተራ ማምታቻ ተፈጽሞ ስናይ አፈርን” ሲሉ የሚገልጹት ጉዳይም አላቸው።

የቢሮው የኮሪደር መስታወት ሆን ተብሎ እንዲሰበር መደረጉን በአግራሞት ሲገልጹ “የተሰበረው የቢሮው የኮሪዶር ዳር መስታወት ከፍ ያለና እንኳን በር ሰባሪ ማጅራት መቺዎችን የሚጠባ ህጻን የማያስገባ ነው፡፡” ሃፍረት የተሞላበትን የዝርፊያ ድራማ ማመን እያቃታቸው የሚገልጹት ለጉዳዩ የቀረቡት ክፍሎች ምርመራው የተያዘው በፌዴራል፣ በክልሉና በልደታ ፖሊስ ጣቢያ መርማሪ ቢሆንም አንድ ርምጃ ሳይራመድ ተድበስብሶ መቅረቱን ይገልጻሉ።

ለእነዚሁ ክፍሎች ቅርብ የሆኑ የክልሉ ፖሊስ አንድ ሃላፊ የዝርፊያው ድራማ “የመጠባበቂያ ቁልፉን ማግኘት የሚችለው ማን ነው?” በሚል የተጀመረው ምርመራ ቀዳሚ ተጠርጣሪዎችን ቢለይም ጉዳዩ እንዲድበሰበስ በመደረጉ ዝርፊያውን ያካሄዱት ክፍሎች ሳይጋለጡ ቀርተዋል።

ባለሃብቱን በቀጥታ ተጠያቂ ያላደረጉት ክፍሎች፣ በሳቸው ድርጅት ስም እንዲህ ያለ ዝርፊያ ሲከናወን ጉዳዩ እንዲጣራ የወከሉዋቸው “ትልልቅ ሰዎች” ራሳቸው ከፖሊስ ጋር ሊሰሩ ይገባቸው ነበር ሲሉ ተናግረዋል። እንዲህ ያለ ተራና የወረደ የመንደር ዱርዬ ተግባር ሲፈጸም ዝም ማለት ከተባባሪነት ሊያሸሽ እንደማይችል የትዝብት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። በባለሃብቱ ዙሪያ ያሉትን ሰዎች ማንነት ያሳያል የሚል እምነት እንዳላቸው በመጠቆም አስተያየታቸውን የሰጡት የኦህዴድ ሰዎች ድርጅታቸው ኦህዴድ ይህንን ጉዳይ በቸልታ መመልክቱ ሌላው አሳፋሪ ጉዳይ እንደሆነ አመልክተዋል።

የተዘረፉት የሂሳብ ማህደሮች ቅጂ በሚገባ ተቀምጦ ስለነበር ወደ አፈጻጸሙ ለመግባት ምንም እክል እንዳላጋጠማቸው በወቅቱ ስራው አካባቢ የነበሩ ለጎልጉል አስረድተዋል። ዝርፊያው እንዲከናወን ትልቁን ሚና ተጫውቷል የሚባል አንድ “ልማታዊ  ጋዜጠኛ” ስለመኖሩ በቂ መረጃ ስላለ ሁኔታዎች ሲመቻቹ የህግ ጥያቄ እንደሚነሳ አመላክተዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    February 4, 2013 01:08 pm at 1:08 pm

    Woyane ethnic fascists and their collaborators can do whatever they want until the Ethiopian people unite and get rid of these home grown fascists. http://vimeo.com/18242221

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule