• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሚድሮክ ልዑክ ለአባዱላ ያቀረቡት ጥያቄ

February 4, 2013 09:06 am by Editor 1 Comment

የሚድሮክ ኢትዮጵያ የበላይ አመራሮች አባዱላ ገመዳን ለማነጋገር ቀጠሮ አስይዘው የተወሰኑ ባለስልጣናት ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ጠይቀው እንደነበር የጎልጉል ምንጮች አስታወቁ። በኦሮሚያ የሚገኙ የሼኽ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ ንብረት የተባሉ ድርጅቶች ላይ የተደረጉ የሂሳብ ምርመራዎችና ግብር ታሪፍ የተሰራባቸው ሰነዶች ዝርፊያ ምርመራ ተድበስብሶ እንዲታፈን መደረጉ እስካሁን ምላሽ ያላገኘ ጉዳይ እንደሆነ ተጠቆመ።

አባዱላ ገመዳ የኦሮሚያ ፕሬዚዳንት በነበሩበት ወቅት ሚድሮክ የሰየማቸውና በዶ/ር አረጋ የሚመራ ልዑክ ቢሯቸው የተገኘው በወቅቱ የሼክ መሀመድ ድርጅቶች ላይ ክልሉ ግብር እንዲከፍሉ ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ነበር። የክልሉ ካቢኔ ግብር መክፈል የሚገባቸው ባለሃብቶች በሙሉ ሊከፍሉ የሚገባቸውን ውዝፍ እዳ ገቢ እንዲያደርጉ ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ክልሉ ውስጥ የሚገኙትን የንግድ ድርጅቶች መዝገብ መርምሮ ነበር።

በወቅቱ የተላለፈውን ውሳኔና የውሳኔውን ትግበራ በቅርበት የሚያውቁ የጎልጉል የመረጃ ምንጮች እንዳሉት የሚድሮክ ሃላፊዎች አባዱላ ቢሮ በመሄድ ስም በመጥቀስ የተወሰኑ የክልሉ ቢሮ ሃላፊዎች ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ጠይቀዋል። ምንጮቹ እንደሚሉት በሙስና ሰበብ በእስር ላይ የሚገኙትን የገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ቀዳሚው ተጠቃሽ ናቸው።

የሚድሮክ ስምና የባለሃብቱ ስም በሚዲያ እንዲጎድፍ አድርገዋል ያሏቸውን ክልሉን ባለስልጣናት ከሃላፊነታቸው እንዲያነሱላቸው የጠየቁት የሚድሮክ ሃላፊዎች አባዱላ በሰጡት መልስ ተበሳጭተው ነበር። አባዱላ ግብር መክፈል ግዴታ እንደሆነ፣ ይህ አቋም በካቢኔ ታምኖበት እንዲተገበር ከውሳኔ ላይ የተደረሰበት መሆኑንና ባለስልጣኖችን የመሾምና የማንሳት ጉዳይ የሚድሮክ ሳይሆን የክልሉ ስራ መሆኑንን ገልጸው የሚድሮክ ሰዎችን እንዳሰናበቱ ምንጮቹ አስታውቀዋል።

በኦህዴድ አባላት ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት የነበራቸው አባዱላ ከክልሉ ፕሬዚዳንትነታቸው የተነሱበት ዋና ምክንያት በሼኽ መሐመድ ላይ ባላቸው አቋም የተነሳ እንደሆነ የሚጠቁሙት ክፍሎች፣ አባዱላ ለሚድሮክ ሰዎች “የሚያጥወለውል” መልስ ሲመልሱ ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ከተጠየቁት መካከል የተወሰኑት ባለሥልጣኖች በተገኙበት መሆኑ የጀመሩትን የግብር ማስከፈል ስራ አጠናክረው እንዲሰሩ ሞራል ሆኗቸው እንደነበር ይናገራሉ።

ጨለለቅ አልሳም ታወር (ፎቶ:የሰነድ ምዝገባ)

በዚሁ መሰረት አላሙዲ በኢንቨስትመንት ስም አጥረው ባኖሩዋቸው ሰፋፊ መሬቶች፣ በኤልፎራ ዶሮ ርቢ፣ በኤልፎራ ቄራ፣ በተለያዩ የከብት ማደለቢያ ኳራንቲዎችና በመልጌ ወንዶ፣ የሆራ ሃይቅ ወዘተ በወቅቱ ለክልሉ ገቢ ያላደረጉት የአስራ አንድ ዓመት የመሬት ግብር እንዲከፍሉ የሂሳብ ሰነድ ይዘጋጃል። ከሌሎች በክልሉ የመሬት ግብር ካልከፈሉ ባለሃብቶችና ድርጅቶች ጋር ባንድነት ተመርምሮ የተዘጋጀው የግብር ተመን የሂሳብ ሰነድ ሜክሲኮ ጨለለቅ አልሳም (ታወር) ህንጻ በነበረው የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ ዘንድ ለውሳኔ እንደደረሱ ያልተጠበቀ ወሬ ተሰማ።

በወቅቱ የገቢዎች ቢሮ ህግ ክፍል ይሰሩ ከነበሩት መካከል ስማቸው እንዳይጠቀስ በመጠየቅ እንዳሉት “የሃላፊው ቢሮ ሳይሰበር በሩ ተከፍቶ ሰነዶቹ ተዘርፈዋል” ጉዳዩን ህግ ዘንድ እንዴት እንደተያዘ ሲከታተሉ ከነበሩት መካከል አንዱ ለጎልጉል እንደተናገሩት “የበርካታ ባለሃብቶችና ድርጅቶች የሂሳብ ምርመራ ሰነዶች አንድ ላይ ከተቀመጡበት የቢሮው ሃላፊ ውስጥ ተመርጦ የተዘረፈው የሼኽ መሀመድ ንብረት የሆኑት ድርጅቶች የሂሳብ ማህደሮች ብቻ መሆናቸው ነው፡፡”

“ቢሮው በቁልፍ ተከፍቶ ስለመዘረፉ ከበቂ በላይ ምልክቶች ነበሩ” የሚሉት እነዚህ ክፍሎች ሃላፊው ቢሯቸውን ቆልፈው ከወጡ በኋላ ዝርፊያው ሲከናወን ቁልፍ ከየት ተገኝቶ ቢሮው ተከፈተ? የሚል ጥያቄ ተነስቶ ነበር። የመጠባበቂያ ቁልፍ ያለው የህንጻው ባለቤት በሆነው አልሳም ኢንተርናሽናል ዘንድ ብቻ እንደሆነ የሚናገሩት እነዚህ ክፍሎች፣ “ተራ ማምታቻ ተፈጽሞ ስናይ አፈርን” ሲሉ የሚገልጹት ጉዳይም አላቸው።

የቢሮው የኮሪደር መስታወት ሆን ተብሎ እንዲሰበር መደረጉን በአግራሞት ሲገልጹ “የተሰበረው የቢሮው የኮሪዶር ዳር መስታወት ከፍ ያለና እንኳን በር ሰባሪ ማጅራት መቺዎችን የሚጠባ ህጻን የማያስገባ ነው፡፡” ሃፍረት የተሞላበትን የዝርፊያ ድራማ ማመን እያቃታቸው የሚገልጹት ለጉዳዩ የቀረቡት ክፍሎች ምርመራው የተያዘው በፌዴራል፣ በክልሉና በልደታ ፖሊስ ጣቢያ መርማሪ ቢሆንም አንድ ርምጃ ሳይራመድ ተድበስብሶ መቅረቱን ይገልጻሉ።

ለእነዚሁ ክፍሎች ቅርብ የሆኑ የክልሉ ፖሊስ አንድ ሃላፊ የዝርፊያው ድራማ “የመጠባበቂያ ቁልፉን ማግኘት የሚችለው ማን ነው?” በሚል የተጀመረው ምርመራ ቀዳሚ ተጠርጣሪዎችን ቢለይም ጉዳዩ እንዲድበሰበስ በመደረጉ ዝርፊያውን ያካሄዱት ክፍሎች ሳይጋለጡ ቀርተዋል።

ባለሃብቱን በቀጥታ ተጠያቂ ያላደረጉት ክፍሎች፣ በሳቸው ድርጅት ስም እንዲህ ያለ ዝርፊያ ሲከናወን ጉዳዩ እንዲጣራ የወከሉዋቸው “ትልልቅ ሰዎች” ራሳቸው ከፖሊስ ጋር ሊሰሩ ይገባቸው ነበር ሲሉ ተናግረዋል። እንዲህ ያለ ተራና የወረደ የመንደር ዱርዬ ተግባር ሲፈጸም ዝም ማለት ከተባባሪነት ሊያሸሽ እንደማይችል የትዝብት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። በባለሃብቱ ዙሪያ ያሉትን ሰዎች ማንነት ያሳያል የሚል እምነት እንዳላቸው በመጠቆም አስተያየታቸውን የሰጡት የኦህዴድ ሰዎች ድርጅታቸው ኦህዴድ ይህንን ጉዳይ በቸልታ መመልክቱ ሌላው አሳፋሪ ጉዳይ እንደሆነ አመልክተዋል።

የተዘረፉት የሂሳብ ማህደሮች ቅጂ በሚገባ ተቀምጦ ስለነበር ወደ አፈጻጸሙ ለመግባት ምንም እክል እንዳላጋጠማቸው በወቅቱ ስራው አካባቢ የነበሩ ለጎልጉል አስረድተዋል። ዝርፊያው እንዲከናወን ትልቁን ሚና ተጫውቷል የሚባል አንድ “ልማታዊ  ጋዜጠኛ” ስለመኖሩ በቂ መረጃ ስላለ ሁኔታዎች ሲመቻቹ የህግ ጥያቄ እንደሚነሳ አመላክተዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    February 4, 2013 01:08 pm at 1:08 pm

    Woyane ethnic fascists and their collaborators can do whatever they want until the Ethiopian people unite and get rid of these home grown fascists. http://vimeo.com/18242221

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule