• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሚድሮክ ልዑክ ለአባዱላ ያቀረቡት ጥያቄ

February 4, 2013 09:06 am by Editor 1 Comment

የሚድሮክ ኢትዮጵያ የበላይ አመራሮች አባዱላ ገመዳን ለማነጋገር ቀጠሮ አስይዘው የተወሰኑ ባለስልጣናት ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ጠይቀው እንደነበር የጎልጉል ምንጮች አስታወቁ። በኦሮሚያ የሚገኙ የሼኽ መሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲ ንብረት የተባሉ ድርጅቶች ላይ የተደረጉ የሂሳብ ምርመራዎችና ግብር ታሪፍ የተሰራባቸው ሰነዶች ዝርፊያ ምርመራ ተድበስብሶ እንዲታፈን መደረጉ እስካሁን ምላሽ ያላገኘ ጉዳይ እንደሆነ ተጠቆመ።

አባዱላ ገመዳ የኦሮሚያ ፕሬዚዳንት በነበሩበት ወቅት ሚድሮክ የሰየማቸውና በዶ/ር አረጋ የሚመራ ልዑክ ቢሯቸው የተገኘው በወቅቱ የሼክ መሀመድ ድርጅቶች ላይ ክልሉ ግብር እንዲከፍሉ ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ነበር። የክልሉ ካቢኔ ግብር መክፈል የሚገባቸው ባለሃብቶች በሙሉ ሊከፍሉ የሚገባቸውን ውዝፍ እዳ ገቢ እንዲያደርጉ ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ክልሉ ውስጥ የሚገኙትን የንግድ ድርጅቶች መዝገብ መርምሮ ነበር።

በወቅቱ የተላለፈውን ውሳኔና የውሳኔውን ትግበራ በቅርበት የሚያውቁ የጎልጉል የመረጃ ምንጮች እንዳሉት የሚድሮክ ሃላፊዎች አባዱላ ቢሮ በመሄድ ስም በመጥቀስ የተወሰኑ የክልሉ ቢሮ ሃላፊዎች ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ጠይቀዋል። ምንጮቹ እንደሚሉት በሙስና ሰበብ በእስር ላይ የሚገኙትን የገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ቀዳሚው ተጠቃሽ ናቸው።

የሚድሮክ ስምና የባለሃብቱ ስም በሚዲያ እንዲጎድፍ አድርገዋል ያሏቸውን ክልሉን ባለስልጣናት ከሃላፊነታቸው እንዲያነሱላቸው የጠየቁት የሚድሮክ ሃላፊዎች አባዱላ በሰጡት መልስ ተበሳጭተው ነበር። አባዱላ ግብር መክፈል ግዴታ እንደሆነ፣ ይህ አቋም በካቢኔ ታምኖበት እንዲተገበር ከውሳኔ ላይ የተደረሰበት መሆኑንና ባለስልጣኖችን የመሾምና የማንሳት ጉዳይ የሚድሮክ ሳይሆን የክልሉ ስራ መሆኑንን ገልጸው የሚድሮክ ሰዎችን እንዳሰናበቱ ምንጮቹ አስታውቀዋል።

በኦህዴድ አባላት ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት የነበራቸው አባዱላ ከክልሉ ፕሬዚዳንትነታቸው የተነሱበት ዋና ምክንያት በሼኽ መሐመድ ላይ ባላቸው አቋም የተነሳ እንደሆነ የሚጠቁሙት ክፍሎች፣ አባዱላ ለሚድሮክ ሰዎች “የሚያጥወለውል” መልስ ሲመልሱ ከሃላፊነታቸው እንዲነሱ ከተጠየቁት መካከል የተወሰኑት ባለሥልጣኖች በተገኙበት መሆኑ የጀመሩትን የግብር ማስከፈል ስራ አጠናክረው እንዲሰሩ ሞራል ሆኗቸው እንደነበር ይናገራሉ።

ጨለለቅ አልሳም ታወር (ፎቶ:የሰነድ ምዝገባ)

በዚሁ መሰረት አላሙዲ በኢንቨስትመንት ስም አጥረው ባኖሩዋቸው ሰፋፊ መሬቶች፣ በኤልፎራ ዶሮ ርቢ፣ በኤልፎራ ቄራ፣ በተለያዩ የከብት ማደለቢያ ኳራንቲዎችና በመልጌ ወንዶ፣ የሆራ ሃይቅ ወዘተ በወቅቱ ለክልሉ ገቢ ያላደረጉት የአስራ አንድ ዓመት የመሬት ግብር እንዲከፍሉ የሂሳብ ሰነድ ይዘጋጃል። ከሌሎች በክልሉ የመሬት ግብር ካልከፈሉ ባለሃብቶችና ድርጅቶች ጋር ባንድነት ተመርምሮ የተዘጋጀው የግብር ተመን የሂሳብ ሰነድ ሜክሲኮ ጨለለቅ አልሳም (ታወር) ህንጻ በነበረው የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ ዘንድ ለውሳኔ እንደደረሱ ያልተጠበቀ ወሬ ተሰማ።

በወቅቱ የገቢዎች ቢሮ ህግ ክፍል ይሰሩ ከነበሩት መካከል ስማቸው እንዳይጠቀስ በመጠየቅ እንዳሉት “የሃላፊው ቢሮ ሳይሰበር በሩ ተከፍቶ ሰነዶቹ ተዘርፈዋል” ጉዳዩን ህግ ዘንድ እንዴት እንደተያዘ ሲከታተሉ ከነበሩት መካከል አንዱ ለጎልጉል እንደተናገሩት “የበርካታ ባለሃብቶችና ድርጅቶች የሂሳብ ምርመራ ሰነዶች አንድ ላይ ከተቀመጡበት የቢሮው ሃላፊ ውስጥ ተመርጦ የተዘረፈው የሼኽ መሀመድ ንብረት የሆኑት ድርጅቶች የሂሳብ ማህደሮች ብቻ መሆናቸው ነው፡፡”

“ቢሮው በቁልፍ ተከፍቶ ስለመዘረፉ ከበቂ በላይ ምልክቶች ነበሩ” የሚሉት እነዚህ ክፍሎች ሃላፊው ቢሯቸውን ቆልፈው ከወጡ በኋላ ዝርፊያው ሲከናወን ቁልፍ ከየት ተገኝቶ ቢሮው ተከፈተ? የሚል ጥያቄ ተነስቶ ነበር። የመጠባበቂያ ቁልፍ ያለው የህንጻው ባለቤት በሆነው አልሳም ኢንተርናሽናል ዘንድ ብቻ እንደሆነ የሚናገሩት እነዚህ ክፍሎች፣ “ተራ ማምታቻ ተፈጽሞ ስናይ አፈርን” ሲሉ የሚገልጹት ጉዳይም አላቸው።

የቢሮው የኮሪደር መስታወት ሆን ተብሎ እንዲሰበር መደረጉን በአግራሞት ሲገልጹ “የተሰበረው የቢሮው የኮሪዶር ዳር መስታወት ከፍ ያለና እንኳን በር ሰባሪ ማጅራት መቺዎችን የሚጠባ ህጻን የማያስገባ ነው፡፡” ሃፍረት የተሞላበትን የዝርፊያ ድራማ ማመን እያቃታቸው የሚገልጹት ለጉዳዩ የቀረቡት ክፍሎች ምርመራው የተያዘው በፌዴራል፣ በክልሉና በልደታ ፖሊስ ጣቢያ መርማሪ ቢሆንም አንድ ርምጃ ሳይራመድ ተድበስብሶ መቅረቱን ይገልጻሉ።

ለእነዚሁ ክፍሎች ቅርብ የሆኑ የክልሉ ፖሊስ አንድ ሃላፊ የዝርፊያው ድራማ “የመጠባበቂያ ቁልፉን ማግኘት የሚችለው ማን ነው?” በሚል የተጀመረው ምርመራ ቀዳሚ ተጠርጣሪዎችን ቢለይም ጉዳዩ እንዲድበሰበስ በመደረጉ ዝርፊያውን ያካሄዱት ክፍሎች ሳይጋለጡ ቀርተዋል።

ባለሃብቱን በቀጥታ ተጠያቂ ያላደረጉት ክፍሎች፣ በሳቸው ድርጅት ስም እንዲህ ያለ ዝርፊያ ሲከናወን ጉዳዩ እንዲጣራ የወከሉዋቸው “ትልልቅ ሰዎች” ራሳቸው ከፖሊስ ጋር ሊሰሩ ይገባቸው ነበር ሲሉ ተናግረዋል። እንዲህ ያለ ተራና የወረደ የመንደር ዱርዬ ተግባር ሲፈጸም ዝም ማለት ከተባባሪነት ሊያሸሽ እንደማይችል የትዝብት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል። በባለሃብቱ ዙሪያ ያሉትን ሰዎች ማንነት ያሳያል የሚል እምነት እንዳላቸው በመጠቆም አስተያየታቸውን የሰጡት የኦህዴድ ሰዎች ድርጅታቸው ኦህዴድ ይህንን ጉዳይ በቸልታ መመልክቱ ሌላው አሳፋሪ ጉዳይ እንደሆነ አመልክተዋል።

የተዘረፉት የሂሳብ ማህደሮች ቅጂ በሚገባ ተቀምጦ ስለነበር ወደ አፈጻጸሙ ለመግባት ምንም እክል እንዳላጋጠማቸው በወቅቱ ስራው አካባቢ የነበሩ ለጎልጉል አስረድተዋል። ዝርፊያው እንዲከናወን ትልቁን ሚና ተጫውቷል የሚባል አንድ “ልማታዊ  ጋዜጠኛ” ስለመኖሩ በቂ መረጃ ስላለ ሁኔታዎች ሲመቻቹ የህግ ጥያቄ እንደሚነሳ አመላክተዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    February 4, 2013 01:08 pm at 1:08 pm

    Woyane ethnic fascists and their collaborators can do whatever they want until the Ethiopian people unite and get rid of these home grown fascists. http://vimeo.com/18242221

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule