• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እነ አላሙዲ በሳዑዲ “ቂሊንጦ”

November 6, 2017 09:44 pm by Editor 9 Comments

ቅዳሜ ማታ በቁጥጥር ሥር የዋሉት የሳዑዲ ልዑላንና ሌሎች ከፍተኛ ባለሥልጣናት እንዲሁም አላሙዲ መሬት ላይ ተኝተው የሚያሳይ ፎቶ ዴይሊ ሜይል በድረገጹ ላይ ለቋል። “ቂሊንጦ” በሚሰኝ ሁኔታ “አገልግሎት” እየተሰጣቸው እንደሆነ ከዴይሊ ሜይል ዘገባ ለመረዳት ይቻላል።

“ከሳዑዲ መንግሥት ምንጮች የተገኘ” በማለት ዴይሊ ሜይል የለቀቀው ይህ ፎቶ እንደሚያሳየው አይነኬዎቹ እነ ልዑል አልዋሊድ (የእኛን ጉድ አላሙዲንን ጨምሮ) በሥሥ ፍራሽ ላይ ሪትዝ ካርልተን ሆቴል መሬት ላይ ተኝተው ይታያል። ጋዜጣው ሲያላግጥም “የሳዑዲ ልዑላን ባለ አምስት ኮከብ እስርቤት ውስጥ” በማለት ለዘገባው ርዕስ ሰጥቶታል። ጋዜጣው ሁኔታውን “የሚያሳፍር” በማለት የጠቀሰው ሲሆን በትንሽ ብርድልብስ ተጠቅልለው ለዚህ ውርደት መብቃታቸው ቢፈቱ እንኳን ውርደቱን ተቀብለው ለመኖር የሚያቅታቸው እንደሆነ አስተያየት ተሰጥቶበታል።

ለምን ያህል ጊዜ እንደሚቆዩ ባይታወቅም ምርመራው እየተካሄደ በዚህ መልኩ ለሳምንታት ሊቆዩ ይችላሉ የሚል ግምት ይሰጣል። (የጋዜጣው ሙሉ መረጃ እዚህ ላይ ይገኛል)

ሰኞ ዕለት የሳዑዲ መንግሥት እንዳስታወቀው የግለሰቦቹ የባንክ ሒሳብ እንዳይንቀሳቀስ ይደረጋል፤ ሃብታቸውም የሳዑዲ መንግሥት ንብረት ይሆናል በማለት መግለጫ ሰጥቷል።

ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ


ደላላው “ባለሃብት” አል-አሙዲ በቁጥጥር ሥር ውሏል!

  • “ማንንም አንፈራም!” ንጉሥ ሳልማን

የሳዑዲ የዙፋን ተስፈኛ አልጋ ወራሽ ሞሐመድ ቢን ሳልማን 11 ልዑላንን እና 38 የመንግሥት ባለሥልጣናትን (የቀድሞውን ጨምሮ) እንዲሁም የንግድ ሰዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ። ደላላ (ተጠሪ ወይም front man) ባለሃብት እንደሆነ የሚነገርለት በግማሽ ኢትዮጵያዊ የሆነው ሞሐመድ አላሙዲ (አል-አሙዲ) በቁጥጥር ሥር ከዋሉት መካከል መሆኑን ጎልጉል አረጋግጧል። ንጉሥ ሳልማን የሕዝብን ንብረት የመዘበረ ማንም ሰው ተጠያቂ ይሆናል፤ “ማንንም አንፈራም” ብለዋል። ዜናው የተወሳሰበ ትስስር ያላቸውን የአላሙዲ “ወዳጆች” ከፍተኛ ሥጋት ላይ ጥሏል።

ልዑል አልዋሊድ ቢን ጣላልና ባለቤታቸው (የፎቶው ባለቤት Jasper Juinen/Getty Images)

ዜናው በመንግሥታዊው የዜና ወኪል አል-አረቢያ ከተዘገበ በኋላ በተለያዩ ምዕራባዊ የሚዲያ ውጤቶች እንደተነገረው ድርጊቱ “ፈጽሞ ያልተጠበቀ” እና በርካታዎችን “ያስደነገጠ” ሆኗል። በሃብታቸው አይነኬነት የሚታወቁት ልዑል አልዋሊድ ቢን ጣላልን (እንደ ፎርብስ ዘገባ የ17ቢሊዮን ዶላር ባለሃብት ናቸው) ጨምሮ ሌሎች 10 ልዑላን በቁጥጥር ሥር መዋላቸው አዲሱ አልጋ ወራሽ ወደ ዙፋን የሚደርጉትን ጉዞ የተቃና ለማድረግ የተወሰደ ነው ተብሏል። ከተያዙት መካከል የደኅንነቱ ኃላፊ ሚጤብ ቢን አብደላም እንደሚገኙ ታውቋል።

በሳውዲ አረቢያ ለውጥ መካሄድ እንደሚያስፈልግ እና ለዚህም ገጣሚ ናቸው በሚል የሳዑዲው ንጉሥ ሳልማን ቢን አብዱልአዚዝ አል ሳውድ ቁጥራቸው ከማይታወቀው ሚስቶቻቸው ከተወለዷቸው ልጆች መካከል የ32ዓመቱን ልዑል ሞሐመድ ቢን ሳልማንን አልጋወራሽ አድርገው ከሾሙ በኋላ በሳውዲ ለውጦች እየተካሄዱ ነው። የሳዑዲ ሃብት ከነዳጅ ወደሌሎች የኢኮኖሚ ውጤቶች ማደግ አለበት በሚል ራዕይ 2030ን አንግበው የተነሱት አልጋ ወራሹ ወደ ዙፋን በሚደርጉት ጉዞ መንገዳቸው ላይ “ዕንቅፋት” የሚሆኑትን ማስወገድ ይዘዋል።

ልዑል ሞሐመድ ቢን ሳልማን

የለውጡና የተሃድሶው ዋነኛ ደጋፊ የሆኑት ንጉሥ ሳልማን በቅርቡ ባቋቋሙት የጸረሙስና ኮሚቴ አልጋወራሽ ሳልማንን ኃላፊ አድርገው ከሾሙ ከጥቂት ጊዜያት በኋላ ነበር በቁጥጥር የማዋል ዘመቻው ተግባራዊ የተደረገው። እንደ አል-አረቢያ ዘገባ ከሆነ፤ ይህ በንጉሡ የተቋቋመው “የጸረሙስና ኮሚቴ ሞሳኝ ነው ብሎ ያመነበትን የማንንም ንብረት የመመርመር፣ የመያዝ (በቁጥጥር ሥር የማዋል)፣ የጉዞ ዕገዳ የማድረግ፣ ወይም ንብረቱ እንዳይንቀሳቀስ የማድረግ” ሙሉ ሥልጣን ተሰጥቶታል።

ይህ “ኃያላንን” በቁጥጥር ሥር የማዋል ዘመቻ በተወሰነ መልኩ ከአሜሪካ የውስጥ ፖለቲካ ጋር የተገናኘ እንደሆነ ጎልጉል ያገኘው መረጃ ያስረዳል። ይህንኑ የሚያረጋግጥ ሆኖ የተዘገበው መረጃ እንደሚያመለክተው በቅርቡ የዶናልድ ትራምፕ ሴት ልጅ ባለቤት ያሬድ ኩሽነር ከዕድሜ አቻው አልጋወራሽ ልዑል ሳልማን ጋር በሳዑዲ ያካሄደው ውይይት እንደ አስረጅነት ይጠቀሳል። ኩሽነር የፕሬዚዳንቱ አማካሪ እንደመሆኑ ጉብኝቱ በምሥጢር መያዙና ከስድስት ቀናት በፊት ይፋ መሆኑ በርካታ መላምት እንዲሰጥበት አድርጓል።

ከዚህ ሌላ ዶናልድ ትራምፕ ለምርጫ በሚወዳደሩበት ወቅት ከይነኬው ባለሃብት ልዑል አልዋሊድ ቢን ጣላል (በሲቲግሩፕ፣ ኧፕል፣ ትዊተር፣ ሊፍት ወዘተ ውስጥ ከፍተኛ የባለቤትነት ድርሻ አላቸው) ጋር የነበራቸውን ቁርሾ የሚያነሱ አሉ። በምርጫው ውድድር ወቅት ልዑሉ ዶናልድ ትራምፕን “ለሪፓብሊካን ፓርቲ ብቻ ሳይሆን ለመላው አሜሪካ ኃፍረት (ውርደት) ነህና በጭራሽ ስለማታሸንፍ ከአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ራስህን አግልል” በማለት የትዊተር መልዕክት አስተላልፈው ነበር።

ትራምፕ ሲመልሱም፤ “ደንቆሮው (በዕጽ የደነዘዘው) ልዑል አልዋሊድ ጣላል በአባቱ ገንዘብ የአሜሪካንን ፖለቲከኞች ለመቆጣጠር ይፈልጋል። እኔ ስመረጥ ይህንን ማድረግ አይችልም” ብለው ነበር። በበቀለኝነታቸውና ጠላቶቻቸውን ጊዜ ጠብቀው በማዋረድ፣ ድባቅ በመምታት የሚታወቁት ትራምፕ ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም ያለፈውን ቁርሾ አሁን በተግባር ፈጽመውታል የሚሉ አሉ።

ወደፊት ሊመጣ የሚችለውን አስቀድመው የተመለከቱት ልዑል አልዋሊድ የትራምፕ መመረጥ ይፋ እንደሆነ ወዲያውኑ ለተመራጩ ፕሬዚዳንት እንዲህ የሚል የአጸፋ ምላሽ ሰጥተው ነበር፤ “ያለፈው ልዩነታችን ምንም ይሁን የአሜሪካ ሕዝብ ተናግሯል፤ እንኳን ደስ አለዎት፤ በፕሬዚዳንታዊ ዘመንዎ መልካሙን ሁሉ እመኛለሁ።”

“በሳዑዲ አረቢያ ታሪክ ተፈጽሞ አያውቅም” በማለት የሚናገሩ፤ ይህ የማጽዳት ዘመቻ ንጉሡ ቅዳሜ ዕለት የጸረሙስና ኮሚቴ መቋቋሙን በተናገሩበት ወቅት ጉዳዩ “የራሳቸውን የግል ጥቅም ከሕዝቡ ጥቅም በማስበለጥ በሚበዘብዙ አንዳንድ ደካማ ሰዎች” ዋንኛው ትኩረቱ እንደሚሆን መናገራቸውን ይጠቅሳሉ። ኮሚቴው እኤአ በ2009ዓም ለመቶ ያህል ሰዎች ሞት ምክንያት የሆነውን የመካከለኛው ምስራቅ የመተንፈሻ በሽታ (MERS) አስመልክቶ የመንግሥት ኃላፊነትና በቫይረሱ መከሰት የተፈጸመውን ደካማ እርምጃ ይመረምራል። በኃላፊነት የሚጠየቁትንም በቁጥጥር ሥር ያውላል። ከዚህ ሌላ ከመቶ በላይ ሰዎች ሞት ምክንያት የሆነውን በ2009 በሳዑዲ (ጂዳ) የደረሰውን የጎርፍ አደጋ በተመለከተ ከመንግሥት የተሰጠውን የአጸፋ እርምጃ ደካማነት በመመርመር ተጠያቂዎችን ለፍርድ ያቀርባል።

ማንኛውንም የማሰር፣ የመያዝ፣ ወዘተ ሥልጣን የተሰጠውን ኮሚቴ አስመልክተው ንጉሥ ሳልማን በሳዑዲ ቲቪ ላይ እንደተናገሩት፤ “የሕዝብን ገንዘብ በነካ፣ በመዘበረ፣ ወይም እንዳይሰረቅ ባልተከላከለ ወይም ሥልጣኑን ተጠቅሞ (ይህንን ዓይነት ተግባር በፈጸመ) በማንኛውም ግለሰብ ላይ ሕጉ በጽናት ተግባራዊ ይደረጋል። ይህ የሚፈጸመው በትልልቆቹም ሆነ በትንንሾቹም ላይ ይሆናል፤ ማንንም አንፈራም” ብለዋል።

የንጉሡን ንግግር ተከትለው አልጋወራሹ ልዑል “ማንም በሙስና ውስጥ የሚገኝ ሚኒስትርም ይሁን ልዑል ማንም ከሕግ በላይ እንደማይሆን ላረጋግጥ እወዳለሁ” በማለት መናገራቸውን አልአረቢያ ዘግቧል።

ተጠርጣሪዎቹ ባለ አምስት ኮከቡ ሪትዝ ካርልተን (Ritz Carlton) ሆቴል በቁጥጥር ሥር እንደሚገኙና ሆቴሉ እስከ ዲሴምበር 1፤ 2017 ድረስ ምንም ዓይነት ክፍት ቦታ እንደሌለው፤ ክፍሎቹ በሙሉ የተያዙ መሆናቸውን አሶሺየትድ ፕሬስ ዘግቧል። እንደ ዜና ዘገባው ከሆነ ይህ የሚያሳየው ይህንን ባከለ ከፍተኛ ደረጃ የሚካሄድ ምርመራ ለሳምንታት ያህል እንደሚወስድ አመላካች ነው ብሏል። ግለሰቦቹ ከሳምንታት ወይም ከቀናት በኋላ የመፈታት ዕድል ቢገጥማቸው እንኳን ባሁኑ የገጠማቸው ኃፍረት ሊሸከሙት የማይችሉት እንደሆነ ይነገራል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የልዑል አልዋሊድ በቁጥጥር ከመዋል ተያይዞ ከሃብታቸው 750 ሚሊዮን ዶላር መጠረጉን ሲኤንኤን ዘግቧል።

እነ ልዑል አልዋሊድ ካላቸው ዓለምአቀፋዊ ተጽዕኖ ፈጣሪነትና ሃብት ጋር ሲነጻጸር የሽልንግ ያህል እንደሆነ የሚቆጠረው የአላሙዲ ስም በቁጥጥር ሥር ከዋሉት መካከል “ሞሐመድ አል-አሙዲ፣ ነጋዴ” በሚል የመጨረሻው መስመር ላይ በሮይተርስ ተጠቅሷል። ዜናው ይፋ እንደሆነ በርካታዎችን ያስደነገጠ ከመሆኑ አኳያ ወዳጅና ደጋፊዎቹ እንዲሁም “ከእጃቸው የበላን” ያሉትን ጨምሮ ማስተባበያ ለመስጠት የተሞከረበት ቢሆንም ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የዲፕሎማቲክ ምንጭ በተለምዶ ሼክ መሐመድ አላሙዲን እየተባለ የሚጠራው በቁጥጥር ሥር መዋሉን አስረድተዋል።

ልዑል አልዋሊድ

እንደ መረጃ አቀባያችን (ጉዳዩ ጥንቃቄ የሚጠይቅ በመሆኑ ስማቸው እንዳይገለጽ አሳስበዋል) ከሆነ በቁጥጥር የማዋል ዘመቻው በዕቅድ የተከናወነ ነው የሚሉት። ንጉሡ ኮሚቴውን ማቋቋማቸው ከተሰማ በኋላ ነበር ብዙም ሳይቆይ ሁሉም ሰዎች የተያዙት። ይህም የሆነው የሚፈለጉት ግለሰቦች አገር ውስጥ መሆናቸው ከተረጋገጠ በኋላ ነው ይላሉ። ይህ ደግሞ እነ ልዑል አልዋሊድን ብቻ ሳይሆን አላሙዲንን የሚጨምር እንደሆነ ያስረዳሉ። ይህ በሳዑዲ የተወሰደው ተግባር በሙስና ሽፋን ስም የተደረገ ቢሆንም ዋናው አጀንዳ ግን የፖለቲካ እንደሆነ የመረጃው ሰው ይናገራሉ። ምክንያቱም የሙስና ቢሆን ኖሮ እነዚህ ሰዎች ካላቸው ሃብት አኳያ የሚጠየቀውን ገንዘብ ከፍለው በዋስ ይለቀቁ ነበር። ቢለቀቁ እንኳን አገር ውስጥ እስኪገቡ መጠበቁ ኮሚቴው ካለው የጉዞ ዕገዳ የማድረግ ሥልጣን አኳያ ከአገር እንዳወጡ አፍኖ ለመያዝ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ ነው ይላሉ።

በኢትዮጵያና በዳያስፖራ በተቃዋሚውም ሆነ በወያኔ ደጋፊው ዘንድ ከተራ ግለሰብ ጀምሮ እስከ ራሳቸውን “ጋዜጠኛ፣ ተንታኝ …” ብለው በሚጠሩ ሁሉ አንዳች ልዩነት ሳያደርጉ “የደሃ አባት፣ ሥራ ፈጣሪ፣ የሕዝብ ደራሽ፣ ከእጃቸው በልቻለሁ፣ ወዘተ” እየተባለ በተለያዩ ቁልምጫዎች የሚጠራው የአላሙዲ መያዝ ከተራዎቹ “ፍርፋሪ ለቃሚዎች” በተለየ ህወሓትን በእጅጉ እንደሚጎዳው ጎልጉል ያገኘው መረጃ ይጠቁማል። በተለይ ለዘመናት ግብር ሳይከፍል የኢትዮጵያን ሃብት በመመዝበር ድርጅቶቹን ሲያንቀሳቅስ መኖሩ አሁን እነዚህ ሁሉ ድርጅቶች በማን ቁጥጥር ሥር እንደሚሆኑና የዕዝ ሠንሠለቱስ እንዴት ተያይዞ እንደሚቀጥል አወዛጋቢ ይሆናል ተብሏል።

ለአስር ሰዎች ሥራ “ለመፍጠር” የሺዎችን የመኖር ኅልውና በመንፈግ ከዓለም የሃብታሞች ተርታ ለመሰለፍ የበቃው አላሙዲን ሥራ ፈጣሪ ተብሎ በተቃዋሚውም ሆነ በህወሓት ደጋፊ መሞካሸቱ የፖለቲካችንን መክሸፍ የሚያመለክት መሆኑን ሲናገሩ የቆዩ ይህ ሥራ መፍጠር ሳይሆን የኔ ከተሳካልኝ ስለሌላው አያገባኝም ዓይነት ሆዳምነት ነው ይላሉ። በድለላ በሚባል ዓይነት የፊትለፊት ሰው በመሆን ሃብት ካካበተው አላሙዲን፤ “ከእጃቸው በልተናል” የሚሉት ህወሓትንና ኤፈርትን ያለመታከት በሚወቅሱበት “ብዕራቸው” አላሙዲንን ዝም ማለታቸው የሚዲያውን መደዴነት፣ አድርባይነትና ጥቅመኝነት የሚያሳይ ነው ይላሉ።

ራሱን “ጋዜጠኛ” ብሎ በመጥራት ከሚዘግብለት ሠንደቅ ጋዜጣ ጎን ለጎን (Honorable Dr Sheik Mohammed Hussien Ali Al-Amoudi) የሚል የፌስቡክ ገጽ የሚያስተዳድረው ፍሬው አበበ በአላሙዲ ስም በከፈተው ገጽ ላይ “የሼህ ሙሐመድ እስር አልተረጋገጠም” በማለት ሲጽፍ በራሱ የፌስቡክ ገጽ ደግሞ “ሼህ አልአሙዲ አልታሠሩም!” በማለት ገልብጦ መጻፉ “ለሆዱ ያደረ ኅሊናቢስነቱን ብቻ ሳይሆን የአላሙዲ በቁጥጥር ሥር መዋል ምን ያህል መደናገጥ መፍጠሩን የሚሳብቅ ነው” በማለት መረጃውን የላኩልን የጎልጉል የፌስቡክ ወዳጅ ተናግረዋል።

ሌላው የአላሙዲ ተጧሪ የEthiopiaFirst.com ቢኒያም ከበደ ዜናውን ለማመን ከከበዳቸው በቀዳሚነት የሚጠቀስ ሆኗል። ቢኒያም በፌስቡክ ገጹ “… አዲሱ መጤው ልዑል ተፎካካሪ ልዑላልን ሪያድ ወደሚገኘው Ritz Carlton Hotel አሰልፎ በመውሰድ ቃላቸውን እንዲሰጡ ማድረጉ ነው። በዚህ መሀከልም የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ የሆኑት ሼህ ሙሓመድ አል-አሙዲም ቃላቸውን እንዲሰጡ ወደ ግዙፉ ሆቴል መወሰዳቸውን ሰምተናል፤” “… እግዚአብሔር ይጠብቃቸው” በማለት ታማኝነቱን አስመስክሯል። አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ለቢኒያም መልዕክት በሌሎች የፌስቡክ ገጾች ላይ “የጣናን እምቦጭ እነቅላለሁ ያለው ትልቁ እምቦጭ አላሙዲ እምቦጭ አለ” በማለት አላግጠዋል።

በአላሙዲን ቀኝ የሚታየው አብነት ነው

በርካታዎች እየሞቱና መብታቸው ተገፍፎ በእስር እየማቀቁ በነበሩበት ወቅት የንብ ካኔተራ በመልበስ የህወሓት ደጋፊነቱን በገሃድ ያስመሰከረው አላሙዲንን ከህወሓት ለይቶ “የሕዝብ ሰው” አድርጎ ማቅረብ ለህወሓት ያለን “ጥላቻ” ከአላሙዲ “ትግሬ” አለመሆን ጋር የተገናኘ ይመስላል የሚሉ ጥቂቶች አይደሉም። ከዚህም አልፎ የዛሬ ሃያ ስድስት ዓመት አካባቢ በኢህአዴግ ሰዎች ሎንዶን ላይ በአብዮታዊ ዲሞክራሲ መጠመቁን የሚናገረውን አላሙዲንን እና ድርጅቶቹን ከኤፈርት ለይቶ ኢትዮጵያዊ አድርጎ ማቅረብ ጭፍንነት ብቻ ሳይሆን ህወሓትን የመቃወሚያው መሠረት አልባነትን የሚያሳይ እንደሆነ ድምጻቸው የታፈነ ጥቂቶች ሲናገሩት የቆዩት ጉዳይ ነው። አላሙዲንና ሚድሮክን የምናሞግስ ከሆነ ስብሃት ነጋንና ኤፈርትን ልንቃወም የምንችልበት መሥፈርት የለንም በማለት እነዚሁ ወገኖች መከራከሪያቸውን ያቀርባሉ።

ሳውዲ በወሰደችው በዚህ ያልተጠበቀ እርምጃ አፈ-አላሙዲን በመሆን ሥራውን የሚያስፈጽመው አብነት ገብረመስቀልና ከእርሱ ጋር ያስተሳሰራቸው የህወሓትና ሌሎች የጥቅም ተካፋዮች ጉዳይ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መውደቁ የማይቀር እንደሚሆን ይታመናል። “አላሙዲን ኢትዮጵያ ውስጥ መታሰር አይችልም ነበር፤ ምክንያቱም እርሱ አገሪቷን አስሯታል፤ አትበቃውም። እርሱን በቁጥጥር ሥር ማዋል የሚችለው ሌላ ኃይል ነበር፤ አሁን አይተነዋል፤ ከዚህ በኋላ ድርጅቶቹን እንደ እርሱ ሆኖ መምራት የሚችል ግለሰብ መኖሩ በጣም አጠራጣሪ ነው፤ ይህ ደግሞ ለድርጅቶቹ ብቻ ሳይሆን ለህወሓትም ትልቅ ዱብዕዳ ነው፤ አገር ውስጥ ካለው እንቅስቃሴ አኳያ ሁኔታዎች በዚሁ አይቀጥሉም፤ በቅርብ በርካታ ያልተጠበቁ የሚመስሉ ለውጦችን ማየት እንጀምራለን” በማለት የጎልጉል መረጃ አቀባይ አስረድተዋል።

ማስታወሻ፤ አላሙዲንን “አንተ” ብለን መጥራታችን ለሚያሳስባችሁ ይህንን እንድታነቡ ይሁን።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    November 7, 2017 10:44 pm at 10:44 pm

    ማልኮስኮስ ልማድህ ሆኖ
    የፊደል ቆጠራው ተራ መክኖ
    ዛሬ ባሰና ይታወቅ ገባ ተመጥኖ??

    አበጀህ ፊደል! ጎሽ!
    ለብራና ፋቂው ፈጥነህ ደራሽ!
    አሳር ሆኖበት ላያመሻሽ
    ቋንቋው ቸግሮት ሆኖ ደበሽ
    ዛሬ አየናችሁ ሲያመሻሽ!
    ሼክም ይጠመጥል ሻሽ!
    ሻሽ በሻሽ! ብቻ ሻሽ በሻሽ!!

    መሪጌታ! ኣፈ ጠበብት! ሆኖ ግዕዝ
    እንደ በርበሬ ሊደለዝ
    ዋ! አማርኛ! እንዲህ ትቀዝቅዝ??
    ገዝግዝ! ተገዛገዝ! በርታ አግዝ

    ደህና ሁኝ አማርኛ!
    የቢናምር ውልድ መጤኛ!
    ደርሶ ግዕዝ ተብሎን ነበር ለኛ!

    Reply
  2. cute-ehapa says

    November 8, 2017 01:10 am at 1:10 am

    Much better re. credits and photo labels. Thats what I was ‘nagging, you about editor man. Please carry on – seriously. Also, if you haven’t already, read the piece by the Guardian, posted by ECAD Forum regarding naming observers – you might learn a thing or two. Honestly you are doing a great job but there is room for improvement. Please listen to your readers, OK? Don’t concern yourselves about the names of feedback writers – what matters is the message!

    Reply
    • Editor says

      November 8, 2017 07:58 am at 7:58 am

      We NEVER said we do not listen. We do! In fact we appreciate any comment from our readers. We strongly believe that is how we grow for we never claimed perfection.

      Your comment was informative and we accepted it and we also replied to that long time ago. We will repeat that here just for the record:

      1. giving credit for photos … we have been doing that for we do believe in professional journalism that is accountable to its ethics as well. However, pictures and photos are found and shared on internet without proper credit (especially on facebook). We cannot give credit to a website that posted the picture just because we got it there. It is not fair nor appropriate. To your satisfaction we can just say just “public domain” or “downloaded from internet”. However, we have found this redundant – it is quite obvious, where-else do we get it? Of course it is from internet! We don’t get it by snail mail. Just an FYI, we have given credits even for ENA, EBC, Tigray Online, Reporter, Addis Fortune, … We do not have any problem with it – no matter who the source is, we believe that it must be respected. If anyone comes with a source for the photos we publish we will recognize that as well – we have stated this in our reply to you more than one time.

      2. as far as adding caption … we do that when it is needed. We have done it in the past and we will continue to do it. Your comment in this regard is acceptable. However, it is a no brainier, if not redundant, to caption, for eg, a photo by saying “this is Meles” or you don’t publish a photo of Trump and caption it as “This is President Trump”. But if the photo was taken somewhere and when Trump is doing something or attending some meeting, it is alright to caption it – and we have tried to do that in the past. The problem is most of the pictures (regarding Ethiopia and its politics) are just shared on internet without telling who is doing what. Thus the problem we stated in #1 spills over here as well – no owner – no caption!

      Another FYI, take a look at this report – look how the pictures are credited and captioned. There are other reports to mention as well.

      Your problem is you are trying to “order” us – not in this comment but in your previous ones. And just for the record no one orders us! We are not anybody’s subjects or loyals! But we seriously listen and give due attention to our readers’ comments and suggestions. In fact we appreciate that because readers are commenting to us because they care – because they want us to improve (like you said above). Besides, do not expect this website to fulfill everything by comparing us to other for profit websites or media outlets. We are volunteers who are running a website that 100% ad free! consider that as well! We earn NO monetary benefit from what we are doing here!

      The other issue about our sources for news tips … we are NOT going to name them or publicize their identities. This is not a western media. Don’t forget that we are dealing with Ethiopian politics. You should know its intricacies and even backlashes.

      We have not read “the piece by the Guardian, posted by ECAD Forum regarding naming observers”. If you have the link, please send us.

      Let’s settle this matter here. We have heard your concern and we will try our best to improve within the boundaries and restrictions we are in.

      Thanks

      Editor

      Reply
  3. ye-tintu-ehapa says

    November 8, 2017 07:51 pm at 7:51 pm

    That’s fine – let us settle here. Just a parting shot I am not the one with the problem or intend to order you around. Just for the record.
    Am I allowed to disguise myself under a different name and nag you? Only joking.

    Reply
    • Editor says

      November 10, 2017 06:36 am at 6:36 am

      Feel free to go as far as “nagging” but not insulting. We understand what you’re doing shows the extent you care. Please do not feel unwanted here. You can come back in any name you want and pick on us. But be more constructive than judgmental. It is all about how you say it than what you are saying.

      Hope that makes sense to you.
      Editor

      Reply
  4. Mulugeta Andargie says

    November 10, 2017 03:22 am at 3:22 am

    Guys!!! I said what I should have said, but you are galloping as if which the horse was worried to go to the race

    Reply
  5. Mulugeta Andargie says

    November 13, 2017 12:07 am at 12:07 am

    ይሀ ነገር እስካሁን ኣላበቃም እንዴ!!???

    Reply
  6. Mezgebu Liben says

    November 15, 2017 08:35 am at 8:35 am

    Hello there,
    I read those comments above & can’t see the heart of your discussion; although I can guess that one of the participants above seems criticizing Golgul. Golgul staff should be happy and proud about the comments. The good thing about this comments suggests that “No one kicks a dead dog”, as the cliche goes, Golgul is alive! Hurray!

    There are bunch of so called “journalists” who never have written any editorial in decades of there media “profession”, and they call themselves “journalists”, but shamefully, they do not even write proper grammar of the very language they only know best! By any standards, whether journalistic ethics or literary qualities like language usage (what always surprises me most is that golgul’s articles and news are almost typos free) and this alone speaks volumes about journalistic professionalism of Golgul. Golgul guys, would you please consider starting radio and/or tv media, too?

    Reply
    • Editor says

      November 17, 2017 04:29 am at 4:29 am

      Dear Mezgebu Liben

      Many thanks for your comments.

      As far as your suggestion to start a radio/tv media, we’d love to do it but the problem is budgetary and staffing issues. However, the plan is not out of agenda – in due times we will make it happen.

      We also like to remind you about your media criticism – we want you to resume that sooner.

      Regards,
      Editor

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule