• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሓት ወደ ስልጣን ለመመለስ የሎቢ ሥራውን ዳግም ጀምሯል

May 30, 2019 12:25 am by Editor Leave a Comment

የተከበራችሁ የጎልጉል አንባቢያን፤ ለወራት ጠፍተን በመቆየታችን ታላቅ ይቅርታ እንጠይቃለን። አንዱና ዋንኛው ምክንያት ድረገጻችን በማደስና የምናትማቸውን ጽሁፎች ባዲስ መልክ ለማድረስ እየሠራን ስለነበር ነው። ሥራው በፈቃደኝነት የሚሠራ በመሆኑ ካሰብነው ጊዜ በላይ ቢወስድብንም ባሁኑ ጊዜ በመጠናቀቅ ይገኛል። በቅርቡ አዲሱን ድረገጻችንን እናስተዋውቃለን። እስከዚያው ግን እዚሁ ላይ እንደተለመደው መረጃዎችን ማተማችንን እንቀጥላለን። በተደጋጋሚ ለጠየቃችሁንና መልዕክቶች ለላካችሁልን ምስጋናችን የላቀ ነው። ከልብ እናመሰግናለን። ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ።


በኢትዮጵያ ከፖለቲካው ቀውስ በማያንስ መጠን የኢኮኖሚው መላሸቅ፣ የሥራአጥነትና ድህነት የሚያስከትሉት አደጋ አሳሳቢና አደገኛ ሊሆን እንደሚችል ተጠቆመ። የለውጡ ኃይሎች ለውጡን በሚያደናቅፉ ላይ ፈጥነው እርምጃ አለመውሰዳቸው ስህተት መሆኑ ተነገረ።

የጎልጉል ታማኝ የአሜሪካ ዲፕሎማቲክ ምንጭ እንዳሉት ኢትዮጵያን ከለውጡ በኋላ አላላውስ ያላት ችግር የኢኮኖሚው ጣጣ ነው። ላለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት ሲቀነቀን የነበረው የኢኮኖሚ መርህ የተነሳ ዜጎች ለሥራአጥነት ተዳርገዋል፤ የሥራአጡ ቁጥርም ከሚገመተውና በይፋ ከሚነገረው እጅግ የበለጠ ነው። በአሁን ወቅት የመንጋ፣ ቡድን፣ ጥርቅም የሚባሉት አካሎች ይኸው ድህነቱ የፈጠራቸው ክፍሎች እንጂ ሌላ እንዳልሆኑ የኢትዮጵያን ጉዳይ በቅርበት የሚከታተሉት ዲፕሎማት አመልክተዋል። የመንደርና የጎጥ ፖለቲካውም የራሱን ጫና ማሳደሩን ዲፕሎማቱ አይክዱም።

ችግሩን ይባስ ያወሳሰበው ደግሞ ይህንን ኃይል ገንዘብ ያላቸው ክፍሎች እንዳሻቸው መጠቀም መቻላቸው ነው። የለውጡ ኃይሎች ወደ ሥልጣን እንደመጡ ወዲያውኑ ሊወስዱ የሚገባቸውን እርምጃዎች ባለመውሰዳቸው “ፌዴራል መንግሥት አይነካንም፤ አያዘንም” የሚሉ ጡንቸኛ አካላት እንዲፈጠሩ አድርጓል።

ባለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት አገሪቱን ሲመሩ የነበሩ አካላት በቁጥጥር ሥር ወዲያውኑ አለመዋላቸው በሽሽት ከተደበቁበት ሆነው የቀድሞውን ሰንሰለታቸውን በተዋረድ እንዲጠቀሙበትና ተመልሰው ጡንቻቸውን እንዲያፈረጥሙ እንዳደረጋቸው ዲፕሎማቱ አስረድተዋል። የሚገርመው ይህንን አካሄድ የሚረዱ ዜጎች አገራቸውን ለመታደግ አሁን ድረስ ምን ማድረግ እንዳለባቸው በውል ያወቁ አይመስሉም። ከዚያ ይልቅ የለውጡ ነቃፊዎችና ተቃዋሚዎች በስልትና በረቀቀ ጥበብ የሚነዛውን የሃሰት ፕሮፓጋንዳ እንደ እውነተኛ መረጃ በመቁጠር በመንግሥት ላይ የማያቋርጥ ነቀፋ በየሚዲያው ሲሰጡ መታየታቸው ሕዝቡን ክፉኛ እያደናገረው ይገኛል።

ከለውጡ በፊት በተደጋጋሚ በእነ ዲ.ኤል.ኤ. ፓይፐር ዓይነት በሎቢ አድራጊዎቻቸው (ወትዋቾቻቸው) አማካይነት ዕድሜ ለማራዘም በተደጋጋሚ አሜሪካንን ሲወተውቱ የነበሩት የህወሓት ሰዎች አሁንም እስከ ሶስት ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ክፍያ በመመደብ ዘመቻ ላይ መሠማራታቸውን ዲፕሎማቱን የጠቀሰው የመረጃው ባለቤት አስታውቋል። በተቃራኒው “ሌሎች እርስ በርስ ይተራመሳሉ፤ አገር በማተራመስም የጥፋት ተልዕኳቸውን ይወጣሉ፤ ብዙዎችም መንግሥትንና የለውጡን ኃይል በጭፍን በመተቸት አገር ያፈርሳሉ” ሲልም የዲፕሎማቱን ንግግር ቃል በቃል በመጥቀስ ያክላል።

የፌደራሉ መንግሥት ትርምሱንና በየቀኑ በረቀቀ ስልት የሚነዙትን የሃሰትና የጥላቻ መረጃዎችን ተከትሎ በሚፈጠሩ አደጋዎች ተወጥሮ ሌሎች ሥራዎችን እንዳይሰራ ጤና መንሳትን ዋናው ዓላማው ያደረገ በበጀት የተደገፈ እንቅስቃሴ እንደሚደረግ ለጎልጉል የደረሰው መረጃ ይጠቁማል።

ለውጡ እየመሩ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር አገሪቱን አንድ አድርጎ መምራት እንደተሳናቸው ተደርጎ በረቀቀ ስልት ከሚፈጠሩ ቀውሶች ጋር በማቀነባበርና ኢትዮጵያ በቀውስ ውስጥ ነች በማለት የምዕራቡን ዓለም በተለይም አሜሪካንን ለማሳመን መጣር የውትወታው (የሎቢው ሥራ) ቀዳሚ አጀንዳ መሆኑን ዲፕሎማቱ ይናገራሉ። ይህንንም በማሳየት ዳግም ወደቀድሞው የአገሪቱ አመራር ለመመለስ ህወሓት እየሠራ መሆኑንን ያመለከቱት እኚሁ ከፍተኛ ዲፕሎማት “ሌሎች ወገኖች እንዲህ ያለውን አካሄድ ተረድተው እርምጃቸውን አለማስተካከላቸው በግል ያስገርመኛል” ሲሉ ተችተዋል።

በኤርትራ መፈንቅለ መንግሥት እንዲሆን ወይም በማንኛውም መልኩ በኤርትራ ለውጥ እንዲደረግ ሌት ተቀን የሚሰራው ህወሓት፣ የቅርብ ጊዜ ሙከራው ቢከሽፍም አሁንም በኢትዮጵያ የተከሰተው ዓይነት አፋጣኝ የፖለቲካ ለውጥ በኤርትራ ካልታየ ህወሓት ወደ ቀድሞ ስፍራው ለመለስ ያሉትን አማራጮች ሁሉ እየተጠቀመ መሆኑን ያመከቱት እኚሁ አንጋፋ ዲፕሎማት፣ “ጆሮ ያለው ይስማ” ሲሉ ምክር መሰንዘራቸውን ምንጩ አስረድቷል።

የዋጋ ንረት፣ ሥራአጥነትና ድህነቱ ከሚደረጉት ሽረባዎች ጋር ተዳምሮ ከቁጥጥር ሥር ሊወጣ ይችላል በሚል ስጋት መኖሩን ዲፕሎማቱ አልሸሸጉም። በዚህ መልኩ የሚፈጠረው ቀውስ ደግሞ መያዣና መጨበጫ ስለማይኖረው አሁን አንዳንድ ቦታዎች ላይ የሚሰሙት የወሮበላነት አዝማሚያ ያላቸው እንቅስቃሴዎች ይስፋፋሉ። እናም ዜጎች አገራቸውን ለማዳን ለውጡን እንዴት መጠበቅ እንዳለባቸው መረዳትና ለውጡ መደገፍ ይኖርባቸዋል። ይህን ማድረግ ካልቻሉ የችግሩ ፈጣሪዎች አጋዥና ረዳት ከመሆን እንደማያልፉም አመልክተዋል።

ለጎልጉል መረጃ የሰጡት ክፍሎች እንዳሉት አንጋፋው ዲፕሎማት ባላቸው መስመር አማካይነት ምን መደረግ እንዳለበትና ለውጡ አሁን የተጋረጡበትን ችግሮች በአሸናፊነት እንዲወታ በምን መልኩ መደገፍ እንዳለበት ለሚመለከታቸው ሃላፊዎች ምክር እንደሰጡና ወደፊትም እንደሚሰጡ ገልጸዋል።

ነጻነት የሚመኙ ዜጎች ነጻነታቸውን በሰላም ማጣጣም ካልቻሉ፣ ሥጋት ላይ ይወድቃሉ። ሥጋት ሲበዛ ዜጎች ከነጻነት ይቅል ቅድሚያ ሰላማቸው እንዲጠበቅ ይመኛሉ። ይህንን ሃቅ አምባገነኖች ስለሚረዱ ሕዝብ ሰላም እንዳይሰማው ሁሉንም ዓይነት ጉድጓድ ይቆፍራሉ። ዜጎች ሥጋት እንዲሰማቸው ሃብታቸውን ያፈሳሉ። እናም ሰላም ከሌለው ነጻነት ይልቅ፣ ሰላም ያለውን አፈና እንዲመርጡ ይገደዳሉ። በዚህ ስሌት ለውጡ ከመጣ ጀምሮ ሰፊ ዘመቻ ሲካሄድ እንደነበር፣ ከለውጡ እውን ሊሆን ባለበት ጊዜም ቢሆን ለውጡ ከተካሄደና “እነርሱ” ከሥልጣን ከተነሱ አገሪቱ እንደምትፈርስ በማስጠንቀቅ በተደጋጋሚ የህወሓት ቁንጮዎች ዘመቻ ሲያካሂዱ እንደንነበር ጎልጉል መዘገቡ አይዘነጋም።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: abiy, eprdf, Eritrea, Full Width Top, Middle Column, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule