በረከት ስምኦንና አቶ ታደሰ ካሳ ከጥረት ኮርፖሬት ጋር በተያያዘ በሌብነት ወንጀል ተጠርጥረው ነው በቁጥጥር ሥር የዋሉት። ዜናው በአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት የተዘገበ ሲሆን ከመኖሪያ ቤታቸው እንደተያዙ መረጃው ጨምሮ ገልጾዋል። ታደሰ ካሳ ጥረት ኮርፖሬትን በዋና ስራ አስፈፃሚነት ለበርካታ ዓመታት የመራ ሲሆን በረከት ስምኦን ደግሞ ከበርካታ የመንግሥት የሥራ ኃላፊነት ቦታዎች ባሻገር የጥረት ኮርፖሬት የቦርድ ኃላፊ ሆኖ ሲመዘብር የነበረ ለመሆኑ ብዙዎች ይናገራሉ። ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about በረከት ስምኦንና ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) በቁጥጥር ሥር ውለዋል
Full Width Top
አንድ ሚሊዮን ብር የሚገመት ለጥቁር ገበያ ሽያጭ ሊቀርብ የነበረ ነዳጅ ተያዘ
ለጥቁር ገበያ ለሽያጭ ሊቀርብ የነበረ ነዳጅ እና ግምቱ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ልዩ ልዩ ቁሳቁስ ከኅብረተሰብ በደረሰ ጥቆማ መያዙን አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ “ትዕግስት ብሩክ ቶታል ማደያ” ውስጥ ጥር 12 ቀን 2011 ዓ/ም በ44 ጀሪካን 995 ሊትር ቤንዚን ከማደያው በመቅዳት ላይ እንዳሉ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል። የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የተቀዳውን ከአስራአንድ ሺ ብር በላይ ዋጋ የሚያወጣ ቤንዚን እና ሌላ ሊቀዳበት የነበረ አርባ አራት ባዶ ጀሪካን የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 አ/አ 29642 ከሆነ አይሱዙ ተሽከርካሪ ጋር በቁጥጥር ሥር አውሏል። ድርጊቱን ፈፅመዋል ተብለው የተጠረጠሩ 5 ግለሰቦችም ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን አስታውቋል። የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የወንጀልና ትራፊክ አደጋ … [Read more...] about አንድ ሚሊዮን ብር የሚገመት ለጥቁር ገበያ ሽያጭ ሊቀርብ የነበረ ነዳጅ ተያዘ
በኢትዮጵያ 36 ሚሊዮን የሚጠጉ ህጻናት በድህነት ደረጃ ላይ ናቸው
በድርብ አኻዝ በከፍተኛ ፍጥነት ዕድገት ላይ ነች እየተባለ ሲደሰኮርባት በነበረችው አገር በቅርቡ ይፋ የተደረገ ጥናት እንደጠቆመው ሰላሣ ስድስት ሚሊየን የሚጠጉ ህፃናቶቿ ዘርፈብዙ በሆነ መልኩ ድሃ መሆናቸው ተነገረ። ይህም ማለት ህፃናቱ ለመኖር የሚያስፈልጓቸው መሠረታዊ አገልግሎቶችን እንኳን ማግኘት ብርቅ ሆኖባቸዋል ነው ጥናቱ ያለው። በኢትዮጵያ ከ18 አመት በታች ከሆኑት ከ41 ሚሊየን ውስጥ 36 ሚሊዮኑ በድህነት ውስጥ እንዳሉ የስታቲስቲክ ኤጀንሲ እና ዩኒሴፍ ጥናት አስረድቷል። ጥናቱ በተለያዩ ዘጠኝ ክፍሎች ተለይቷል። ድህነቱ በዕድገት፣ በምግብ፣ በጤና፣ በውሃ፣ በንፅህና እና በመጠለያ ሲሆን ሌሎቹ የድህነት መለኪያ መስፈርቶች ደግሞ ትምህርት፣ ከጤና ጋር በተያያዘ በቂ ዕውቀት፣ መረጃና ተሳትፎን የሚጨምር ነው ተብሏል። በጥናቱ እንደተገለጸው 88 በመቶ የሚሆኑት ዕድሜያቸው … [Read more...] about በኢትዮጵያ 36 ሚሊዮን የሚጠጉ ህጻናት በድህነት ደረጃ ላይ ናቸው
በአዲስ አበባ ለተከሰተው የነዳጅ አሻጥር መፍትሔ ሊበጅለት ነው
በአዲስ አበባ ከተማ የቤንዚን ነዳጅ እጥረት እንዲከሰት እና እንዲባባስ በሚያደርጉ ነዳጅ አቅራቢዎች እና አከፋፋዮች ላይ አስፈላጊውን ክትትል እያደረገ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። በአገር አቀፍ ደረጃ በቂ ነዳጅ እያለ ነገር ግን በአዲስ አበባ ከተማ የቤንዚን እጥረት እንዲከሰት እና እንዲባበስ በመደረጉ ያጋጠመውን ችግር ለመፍታት አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ያካተተ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክቡር ኢንጂነር ታከለ ኡማ የሚመራ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ ስራ መጀመሩ ይታወቃል። በከተማችን ነዳጅ ለማከፋፈል 120 ገደማ የሚሆኑ የነዳጅ ማደያዎች በሕግ አግባብ ፈቃድ መውሰዳቸው እየታወቀ 106ቱ ብቻ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል። ጥር 8 ቀን 2011 ዓ/ም በስራ ላይ ከሚገኙ 106 … [Read more...] about በአዲስ አበባ ለተከሰተው የነዳጅ አሻጥር መፍትሔ ሊበጅለት ነው
“የስብሃት ማፊያ ቡድን” – ህወሓት መፍረስ፤ EFFORT መወረስ አለበት
ህወሓት – ጨቋኝ ቡድን ወይስ ወራሪ ጠላት? 1) ጨቋኝ ቡድን እና ወራሪ ጠላት አንድ መንግሥት በሚመራው ህዝብ ላይ እንዲህ ያለ በጭካኔ የተሞላ ግፍና በደል የሚፈፅም የፖለቲካ ቡድን አምባገነን ወይም ጨቋኝ ብቻ ሊባል አይችልም። የሀገሪቱን ሉዓላዊነትና አንድነት በሚያፈርስ መልኩ ዘረፋና ሌብነት የሚፈፅም ቡድን ሙሰኛ ወይም በዝባዥ ብቻ ሊባል አይችልም። እንደ ህወሓት በሰው ልጅ ላይ ጨካኝ እና በሀገሩ ላይ ዘራፊ የሆነ መንግስት ፈልጎ ማግኘት የሚቻል አይመስለኝም። አብዛኞቹ አምባገነን መንግስታት በዜጎች ላይ ግፍና በደል የሚፈፅሙት የሀገርን አንድነትና ሉዓላዊነት ለማስከበር በሚል ሰበብ ነው። ስለዚህ በዜጎች ላይ ጨቋኝ እና ጨካኝ ቢሆኑም ለሚመሩት ሀገር አንድነትና ሉዓላዊነት በፅናት የሚታገሉ ናቸው። በሌላ በኩል ለሚያስተዳደሩት ሀገር አንድነትና ሉዓላዊነት ደንታ-ቢስ የሆነና በዜጎች … [Read more...] about “የስብሃት ማፊያ ቡድን” – ህወሓት መፍረስ፤ EFFORT መወረስ አለበት
የአኙዋክ ምድር በኢትዮጵያ የዕርቅ ማስጀመሪያ ቦታ ሊሆን ይገባል!
ዕለቱ ቅዳሜ ታኅሣሥ 3 ቀን 1996ዓም ነበር - ልክ የዛሬ 15 ዓመት። የአኙዋክ ወንዶች እንዲገደሉ ዕቅዱ የወጣው አስቀድሞ ነበር። በቅርቡ ህይወቱ ያለፈውና በወቅቱ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የነበረው ኦሞት ኡባንግ ኡሎም ቢሮ በ1996 ዓም የተገኘ በአማርኛ የተጻፈ ባለ 16 ገጽ ማስታወሻ እንደሚያመለክተው “መስከረም 13፤ 1996ዓም የዚያን ጊዜ ጠ/ሚ/ር በነበረው መለስ ዜናዊ ቢሮ ውስጥ በተካሄደው ስብሰባ ላይ መለስ ራሱ፣ ምክትል ጠ/ሚ/ር አዲሱ ለገሠ፣ የህወሓት ከፍተኛ ሹም ስብሃት ነጋ፣ የማስታወቂያ ሚኒስትር በረከት ስምዖን፣ የጋምቤላ ደኅንነት ዋና ኃላፊ ኦሞት ኡባንግ ኡሎም፣ ፌዴራሉ ደኅንነት ጽ/ቤት የመጣና ስሙ ያልታወቀ፣ የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር አባይ ፀሃዬ፣ ኤታማዦር ሹም ሳሞራ ዩኑስ፣ መከላከያ ሚኒስትር አባዱላ ገመዳ፣ የወታደራዊ ስለላ ሹም ብርጋዴር ጄኔራል … [Read more...] about የአኙዋክ ምድር በኢትዮጵያ የዕርቅ ማስጀመሪያ ቦታ ሊሆን ይገባል!
ከቅዳሜው የህወሓት ሰልፍ በፊት በትግራይ “ከዓቅም በታች የሰረቁ” ተፈረደባቸው
ቅዳሜ በህወሓት አስገዳጅነትና ተለማማጭነት አሁን በመላው ኢትዮጵያ የሚካሄደውን ለውጥ የመቃወም እንደምታ ያለው ሰልፍ ተጠርቷል። እስካሁን ድረስ በርካታ መረን የወጣ ሌብነት የፈጸሙ፣ እጅግ አሰቃቂ የሰብዓዊ መብቶችን የጣሱና ሌሎች ተፈላጊ ወንጀለኞችን በትግራይ ደብቆ የያዘው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) በኤፈርት አልባሽነት ቅዳሜ "ሰላማዊ" ያለውን ሰልፍ በመቀሌ፣ ትግራይ ጠርቷል። ሌብነትን እንቃወማለን ለማለትም በአንዳንዶች ዘንድ “ከዓቅም በታች የሰረቁ” የተባሉ አነስተኛና ጥቃቅን ሌቦች ላይ ፍርድ አስተላልፏል። የመቀሌ ከተማ የኮሙኒኬሽን ኃላፊ ዘመንፈስቅዱስ ፍሰሃን ጠቅሶ ኢዜአ እንደዘገበው የሰልፉ አንዱ ዓላማ “ህገመንግሥቱ ይከበር” የሚል ነው ብሏል። ይህ በህወሓት አነጋገር ከአንቀጽ 39 ጀምሮ በርካታ ነገሮችን ሊያስብል የሚችል አገላለጽ፤ ህወሓት ከሁለት ዐሥርተ … [Read more...] about ከቅዳሜው የህወሓት ሰልፍ በፊት በትግራይ “ከዓቅም በታች የሰረቁ” ተፈረደባቸው
ከኦነግ የተገነጠለው ኦዴግ ከኦዴፓ ጋር መቀላቀል ኢህአዴግን እና ግንቦት 7ን ወዴት ያመራቸዋል?
“አዲሲቷን ኢትዮጵያ በጋራ ለመመስረት ተነስተናል። የቀድሞው የትግል ስልት አያዋጣም” በማለት “የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር” (ኦዴግ) ODF የሚባል አዲስ ግንባር መጋቢት 22፤2005ዓም (ማርች 31/2013) ያቋቋሙት የቀድሞው የኦነግ ከፍተኛ አመራሮች የቀድሞውን ኦህዴድ የአሁኑን ኦዴፓን ተቀላቅለዋል። ከኦነግ ተገንጥሎ ኦዴግ የሆነው የሌንጮ ለታ ፓርቲ ኦዴፓን መቀላቀሉና በኢህአዴግና በግንቦት 7 ላይ የሚያስከትለው የፖለቲካ ተጽዕኖ ገና አልጠራም። ከዳውድ ኢብሣ ኦነግ ጋር እቀላቀላለሁ ያለው የመረራ ጉዲና ኦፌኮም መጨረሻው አልታወቀም። የዛሬ አምስት ዓመት አካባቢ ከብሪታንያ፣ ከስዊትዘርላንድ፣ ከካናዳ፣ ከአውስትራሊያ፣ ከጀርመንና ከተለያዩ አገራት የተሰባሰቡ ቁጥራቸው 400 የሚጠጋ ተሰብሳቢዎች ባካሄዱት ውይይት ላይ ስለ ኦዴግ ማብራሪያ የሰጡት ሌንጮ አስፈላጊ የተባሉ ጥያቄዎች … [Read more...] about ከኦነግ የተገነጠለው ኦዴግ ከኦዴፓ ጋር መቀላቀል ኢህአዴግን እና ግንቦት 7ን ወዴት ያመራቸዋል?
የህወሓት ግፍ በጥቂቱ የተገለጸበት የፍርድቤት ውሎ
በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት ውስጥ በአሸባሪነት እስካሁን ተመዝግቦ የሚገኘው ህወሓት (የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር) ላለፉት 27ዓመታት በግፍ በነጻ አውጪ ስም ኢትዮጵያን በሚገዛበት ጊዜ ለጥቅሙ ባሰማራቸው አረመኔዎች የተፈጸመው ግፍ ጥቂቱ ፍርድቤት ተነግሯል። ሪፖርተር ባወጣው የዜና ዘገባ መሠረት በሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ተጠርጥረው የተያዙት የህወሃት የደኅንነት አባላት በሕዝብ ላይ የፈጸሙትን ግፍ መርማሪ ቡድኑ ሲያቀርብ ጥቂቱን ግፍ በዚህ መልኩ ገልጾታል። “… በጨለማ ቤት ውስጥ ለረዥም ጊዜ በማሰርና በመደብደብ ማሰቃየት፣ እግርና እጅ በሰንሰለት አስሮና ጣሪያ ላይ ሰቅሎ መግረፍ፣ በኤሌክትሪክ ገመድ መግረፍ፣ በሙሉ አካላቸው ታስረው በደረሰባቸው ደብደባ አካላቸው ጎድሎ በዊልቸር፣ በዱላና በሰው ተደግፈው እስከሚሄዱ መደብደብ፣ ራቁታቸውን አስሮ ገንዳና ቆሻሻ ቦታ ውስጥ … [Read more...] about የህወሓት ግፍ በጥቂቱ የተገለጸበት የፍርድቤት ውሎ
“እንጨርሳቸው፤ አንድም አኙዋክ መትረፍ የለበትም” የሚለውን የህወሓት ትዕዛዝ ተፈጻሚ ያደረገው ኦሞት ኦባንግ ሞቷል
በወንበዴው የህወሓት ቡድን ትዕዛዝ 424 አኙዋኮችን የጨፈጨፈው ኦሞት ኡባንግ ኡሎም ያለፈው ሳምንት መጨረሻ አካባቢ መሞቱ ታውቋል። ከመለስ ዜናዊ ትዕዛዝ በመቀበል ለ424 የአኙዋክ ተወላጆች የግፍ ዕልቂት ተጠያቂ የነበረው ኦሞት ኦባንግ በስደት በሚገኝበት ፊሊፒንስ ሞቷል። የሞቱ ምክንያት ኤችአይቪ ኤድስ ሊሆን ይችላል የሚል ግምት አለ። ኦሞት ኦባንግ የዛሬ 15 ዓመት አካባቢ በታኅሳስ ወር ከህወሓት ሹሞች ቀጥተኛ ትዕዛዝ በመቀበል ጭፍጨፋውን በፈጸመበት ወቅት የክልሉ የፀጥታና ደኅንነት ኃላፊ ነበር። ለዚህም ኢሰብዓዊ ድርጊቱ ሽልማት ይሆን ዘንድ የወንበዴው ህወሓት መሪዎች የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አድርገው ሾመውታል። ጋምቤላን እንደፈለገ ሲፈነጭባት የኖረው ኦሞት ከታህሳስ 23 ቀን 2004 ዓም ጀምሮ ሞት እንደ ቡሽ ክዳን ያስፈነጠረው መለስ ዜናዊ በላከው አስገምጋሚዎች ለሳምንት … [Read more...] about “እንጨርሳቸው፤ አንድም አኙዋክ መትረፍ የለበትም” የሚለውን የህወሓት ትዕዛዝ ተፈጻሚ ያደረገው ኦሞት ኦባንግ ሞቷል










