• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከቅዳሜው የህወሓት ሰልፍ በፊት በትግራይ “ከዓቅም በታች የሰረቁ” ተፈረደባቸው

December 7, 2018 06:21 am by Editor 3 Comments

ቅዳሜ በህወሓት አስገዳጅነትና ተለማማጭነት አሁን በመላው ኢትዮጵያ የሚካሄደውን ለውጥ የመቃወም እንደምታ ያለው ሰልፍ ተጠርቷል። እስካሁን ድረስ በርካታ መረን የወጣ ሌብነት የፈጸሙ፣ እጅግ አሰቃቂ የሰብዓዊ መብቶችን የጣሱና ሌሎች ተፈላጊ ወንጀለኞችን በትግራይ ደብቆ የያዘው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) በኤፈርት አልባሽነት ቅዳሜ “ሰላማዊ” ያለውን ሰልፍ በመቀሌ፣ ትግራይ ጠርቷል። ሌብነትን እንቃወማለን ለማለትም በአንዳንዶች ዘንድ “ከዓቅም በታች የሰረቁ” የተባሉ አነስተኛና ጥቃቅን ሌቦች ላይ ፍርድ አስተላልፏል።

የመቀሌ ከተማ የኮሙኒኬሽን ኃላፊ ዘመንፈስቅዱስ ፍሰሃን ጠቅሶ ኢዜአ እንደዘገበው የሰልፉ አንዱ ዓላማ “ህገመንግሥቱ ይከበር” የሚል ነው ብሏል። ይህ በህወሓት አነጋገር ከአንቀጽ 39 ጀምሮ በርካታ ነገሮችን ሊያስብል የሚችል አገላለጽ፤ ህወሓት ከሁለት ዐሥርተ ዓመታት በላይ ሳያከብረው የኖረውን ህገመንግሥት አሁን ግምባር ቀደም የመታገያ መሣሪያ ማድረጉ አስቀድሞ ለራሱ የሠራው ሥራ እንዳለ አመላካች ነው።

ከዚህ ሌላ በሰልፉ ላይ “የትግራይን ህዝብ ለማምበርከክ የሚደረጉ ሴራዎች ተቀባይነት” የላቸውም፤ “በማንነት ጥያቄና በአዋሳኝ አካባቢዎች ምክንያት በማድረግ የክልሉን ህዝብ የሚነኩ ትንኮሳዎች” አንቀበልም፤ የውጭ ጣልቃ-ገብነትና የውስጥ ሤራዎች እንዲቆሙ እንጠይቃለን፤ ወዘተ የሚሉ መልዕክቶች በሰልፉ እንደሚተላለፉ ዘመንፈስቅዱስ አመላክተዋል።

ይህ አስቀድሞ ምን ያህል ሕዝብ እንደሚወጣበት፣ ምን ዓይነት መፈክር እንደሚፈከርበት ተጠናቆና ተዘጋጅቶ የተጠራ ሰልፍ፤ የትግራይ ሕዝብን በየትኛውም መልኩ እንደማይደግፍ አንዳንድ የትግራይ ተወላጆች ይናገራሉ። ሆኖም በዚህ በ“ባሎኒ” ስታዲየም የተጠራውን ሰልፍ ሕዝባዊ ቁመና ለማላበስ ህወሓት የተለያዩ የሚዲያ ተወካዮችን በክልሉ መስተዳድር ስም በክብር በደብዳቤ ጋብዟል። ምን ያህሉ እንደሚገኙ እስካሁን የታወቀ ነገር የለም።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ በዓለምአቀፍ የአሸባሪዎች የመረጃ ቋት ውስጥ በአሸባሪነት እስካሁን ተመዝግቦ የሚገኘው ህወሓት፤ የወንበዴው ቡድን አምበል የነበረውን የመለስ (ለገሰ) ዜናዊ ፎቶ ያለበትን ቲሸርት መቀሌ ላይ ሕዝቡን አስለብሶ ሐሙስ ዕለት የድጋፍ ሰልፍ አስወጥቷል። በመላው ኢትዮጵያ የሚገኘው ሕዝብ የመለስን ፎቶ ላለማየት ካለበት ቦታ ሁሉ አውርዶ አገሩን በተረከበበት ጊዜ (ከፓርላማም በዚህ ዓመት የመለስ ፎቶ ተወግዷል)፤ ህወሓት የማሌሊትን ጨርቅ በግድ አስለብሶ ሕዝቡ እንዲታይ አድርጓል።

በሌላ በኩል የሌባና የወንጀለኛ ተባባሪ ደባቂ በመሆን ሰሞኑን በተለያዩ ሁኔታዎች ስሙ ሲወቀስ የነበረው ህወሓት፤ በትግራይ 63 ግለሰቦችን በእስርና በገንዘብ ቀጥቻለሁ ብሏል። አሃዱ ሬዲዮ እንደዘገበው ከሆነ “የክልሉ የስነ-ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ባለፉት አምስት ወራት ውስጥ የህዝብና የመንግስት ሀብትን በመዝረፍና ፍትህን በማዛባት ጥፋተኛ ሆነው ተገኝተዋል የተባሉ 63 ግለሰቦች በእስርና በገንዘብ እንዲቀጡ ማድረጉን አስታወቋል። በግለሰቦቹ ተዘርፎ የቆየ 8 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብና ከአንድ ሺህ ካሬ ሜትር በላይ የከተማ መሬት ወደ መንግስት ካዝና እንዲመለስ፤ ጥፋተኛ ሆነው የተገኙ 52 ግለሰቦች ከ6 እስከ 8 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት፤ 11ዱ ደግሞ ከ9 እስከ 16 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ውሳኔ እንደተላለፈባቸው” ሬዲዮው ኮሚሽነሩን በመጥቀስ ዘግቧል።

ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ እንደሚሉት በኢትዮጵያ የመጣውን ለውጥ እየተቃወመ ያለው ህወሓት፤ አሁን ደግሞ ሌቦችንና በሰብዓዊ መብቶች ጥሰት የሚጠረጠሩ ግለሰቦችን ሸሽጎ ስለሚገኝ ለዚህ ማጣፊ እንዲሆን ያደረገው ነው ይላሉ። ሁኔታው ያልጣማቸውና ከዚህ በላይ በአገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ሌብነትና ወንጀል የፈጸሙትን የህወሓት ሰዎች አሳልፎ ከመስጠት ልቅ እነዚህን “ከዓቅም በታች የሰረቁ” ግለሰቦችን በመቅጣት ራሱን ከተጠያቂነት ለማስመለጥ የሚያደርገው ከንቱ ልፋት ነው በማለት አስተያየታቸውን ይሰጣሉ።

ከበረሃ ጀምሮ በውንብድና ተግባሩ በዓለምአቀፍ ደረጃ የሚታወቀው ህወሓት፤ ኢትዮጵያን በነጻ አውጪ ስም የግል ንብረቱ አድርጎ ሲበዘብዝና የፈለገውን ግፍ ሲፈጽም የቆየበት ጊዜ እያከተመ ሲመጣ በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች ብጥብጥ በማስነሳትና ስፖንሰር በማድረግ ዓላማውን ለማስፈጸም ሲጥር እንደነበር ይነገራል። በተለይ በሶማሊ ክልል ሤራው ከከሸፈ በኋላ በጋምቤላም በተመሳሳይ ሁኔታ አመራሮቹ ተነስተው ለውጥ በክልሎቹ ሥር እየያዘ ነው። በቀጣይነት ደግሞ ዋና ምሽጉ አድርጎ ሲንቀሳቀስበት የነበረው የአፋር ክልል በአሁኑ ጊዜ በለውጥ እንቅስቃሴ ላይ የሚገኝ ሲሆን ቤንሻንጉልም በዚያው መስመር ላይ ይገኛል። ይህ ሲጠናቀቅ ህወሓት በግፍ አፍኖ በያዘው የትግራይ ሕዝብ መተፋቱ እንደማይቀር ብዙዎች የሚስማሙበት ነው።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, meles, Middle Column, tigray, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    December 7, 2018 03:29 pm at 3:29 pm

    የትግራይ ህዝብ ጠላቱ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ነው። ሌላው ሁሉ ለፓለቲካ ፍጆታ የሚናፈሰና መሰረት በሌለው በጅሎች የፓለቲካ እይታ የታጀበ ነው። ገና ከበረሃ ጀምሮ በትግራይ ህዝብ ስም ሃበሳን ሲያመነጭ የኖረው ወያኔ ሃርነት ትግራይ ለ 27 ዓመት የከተማ አለቃ ከሆነም በህዋላ ለትግራይ ህዝብ ያደረገው ከዚህ ግባ የሚባል ነገር የለም። በበረሃ በትግራይ ህዝብ ስም ሲነግድና ሲያተርፉ የነበሩ በከተማም በትግራይ ህዝብ ስም ነጋዴና ቀማኛ በመሆን ለራሳቸውና ለዘመዶቻቸው በሃገርና በውጭ ያካበቱት ሃብት ምሥክር ነው።
    በቀበሌ ጥሩንባ ያለ ልቡ ለሰላማዊ ሰልፍ የትግራይ ህዝብ ወጣ የሚባለውም ትሩፋት የለሽ ውስልትና ነው። የወያኔ የማወናበጃ ዋና ተግባሩ የትግራይን ህዝብ ማስቀደምና ጥይት መተኮስ ነው። የትግራይ ህዝብ የታፈነ ህዝብ ነው። አፈናውም ነጻ አወጣንህ እያለ ቀንና ሌሊት በሚለፉት በወያኔ አመራሮችና ፍርፋሪ ለቃሚ ካድሬዎች ነው። የትግራይ ህዝብ ሃገሩን የሚወድ፤ ፈጣሪን የሚፈራ ህዝብ ነው። የህዝባችን እይታ ያጨለመው የወያኔ የዘር ፓለቲካ ነው። ዛሬ ሰርቀው፤ ሰቆቃ ፈጽመው፤ ጠ/ሚሩን ለመግደል ሙከራ ያደረጉ የመሸጉባት መቀሌ እነዚህን ሰዎች ለፍርድ አሳልፎ መስጠት እጅግ አሰፈላጊ ነው። ከዛ ውጭ በወያኔ ግፊት የሚደረጉ ፍሬ አልባ ሰላማዊ ሰልፎች ሁሉ ፉርሽና ተጨፈኑና ላሞኛችሁ እንደማለት ነው።

    Reply
  2. gi Haile says

    December 7, 2018 08:21 pm at 8:21 pm

    ኣሳነባሪው ነውን መያዝ ኣሳዎች መች አስቸግረው ያውቃሉ። የኣሳ ግማቲ ከጭንቅላቱ ስለሆነ ከበሰበሰ ክፉ የሕወአት የቀድሞ መሪዎች ምንም መልካም ነገር አይገኝም። ከወር በላይ የፈጀወሰ የግምገማ ስብሰባ በመቀሌ ጠቅላላ ይዘቱ ቢፈተሽ ግድያን ዘረፋን በምን መልክ እናት ድርግ ውጭ አይደለምና የያዛቸው የዘር ካንሰር እስኪጨርሳቸው ማየት ነው።

    Reply
  3. Tadesse says

    December 10, 2018 04:27 pm at 4:27 pm

    We are really alone fighting these shiftas.Even other people,Oromo/Amhara are shallow minds when it come to tjhis situation but the people of Tigray including me will better die than to live in this situation.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule