• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አንድ ሚሊዮን ብር የሚገመት ለጥቁር ገበያ ሽያጭ ሊቀርብ የነበረ ነዳጅ ተያዘ

January 22, 2019 03:58 am by Editor 1 Comment

ለጥቁር ገበያ ለሽያጭ ሊቀርብ የነበረ ነዳጅ እና ግምቱ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ልዩ ልዩ ቁሳቁስ ከኅብረተሰብ በደረሰ ጥቆማ መያዙን አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ።

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ “ትዕግስት ብሩክ ቶታል ማደያ” ውስጥ ጥር 12 ቀን 2011 ዓ/ም በ44 ጀሪካን 995 ሊትር ቤንዚን ከማደያው በመቅዳት ላይ እንዳሉ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል።

የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የተቀዳውን ከአስራአንድ ሺ ብር በላይ ዋጋ የሚያወጣ ቤንዚን እና ሌላ ሊቀዳበት የነበረ አርባ አራት ባዶ ጀሪካን የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 አ/አ 29642 ከሆነ አይሱዙ ተሽከርካሪ ጋር በቁጥጥር ሥር አውሏል።

ድርጊቱን ፈፅመዋል ተብለው የተጠረጠሩ 5 ግለሰቦችም ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን አስታውቋል።

የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የወንጀልና ትራፊክ አደጋ ምርመራ ዲቪዚዮን ኃላፊ ኮማንደር ጌታነህ በቀለ እንደገለፁት የማደያው ሠራተኞች ቤንዚን በጥቁር ገበያ ከሚሸጡ ህገ-ወጦች ጋር በመተባበር ድርጊቱን ፈፅመዋል።

ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ታህሳስ 8 ቀን 2011 ዓ/ም ልዩ ቦታው አማኑኤል ቤተክርስቲያን አካባቢ ኮድ 3-47453 አ/አ የሆነ አይሱዙ ተሽከርካሪ ከላይ ሲሚንቶ በማድረግ ከሥር ስድሳ ሦስት ጀሪካን ቤንዚን ጭኖ ሲንቀሳቀስ በድንገተኛ ፍተሻ መያዙን ኮማንደሩ አስረድተዋል።

በተያያዘ ዜና ጥር 13 ቀን 2011 ዓ/ም ምዕራብ ሆቴል አከባቢ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-80502 አ/አ የሆነ ተሽከርካሪ ግምቱ ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ በኮንትሮ ባንድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ ልዩ ልዩ ዕቃዎች ይዞ ሲንቀሳቀስ ተይዟል።

ፖሊስ መምሪያው ከህዝብ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ተሽከርካሪው ቢያዝም አሽከርካሪው ግን ለጊዜው እንደተሰወረ እና ለመያዝ ክትትል እየተደረገ መሆኑን ኮማንደር ጌታነህ ገልፃዋል።

ተሽከርካሪው ሲያዝ በርካታ ጣቃ ጨርቆች፣ 2ሺህ የሞባይል ቻርጀሮች፣ 3480 አይነቱ “ኑር ሴላ” የሆነ ሲጋራ እና አንድ ሺ የሪሲቨር ሪሞት ኮንትሮል ይዞ ለማምለጥ ሲሞክር እንደነበር ኃላፊው አስረድተዋል።

ምንጭ፦ ኢ.ፕ.ድ.

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. gi Haile says

    January 23, 2019 08:04 pm at 8:04 pm

    ከቀድሞ የምሮ የረገራችን ችግር ፈጣሪዎች በለስልጣንና ሐጉምሩክ ሰራተኞች ከለይ ጀምረው በኔትዎርክ ኮንትሮባንድ ሲያስገቡ ያሉ ሰለሆነ ማጠናከር የሚገባው የበላይ ለሥልጣንን ከአቀጣጣር ጀምሮ ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል። በተለይም ከድሮ ጀምሮ ጉምሩክና ከኳድ መኪና ሹፌሮች በሰሜን ክልል ተወላጆች የተያዘ ነበር ከአይለስላሴ ጊዜ ጀምሮ መፍትሔ ያጠው ኮንቶሮባንድ አደገኛ የወንጀል ሰራ የሚሰራበት ቦታ ነው የየክልል ጉሙሩክ ኬላዎች በካሜራና በልዪ የምርመራ ስልት ቁጥጥር ሊደረግበት ያለ ክፍል ቢኖር በአየር ትራንስገኸፖርት፣ በወደብ ና በክልል ጉምሩክ ጣቢያ ላይ ፈዴራልና የክልል መንግስት ተባብረው ሊሰሩና ይህን የመሰለ ወንጀልና ዪንግስት ገቢ በከንቱ በሌቦች እጅ መግባት የለበትም። ሌብነት የሰው ልጅ የመጨረሻው የሞራል ዝቅተኛው ሰፍራ ነው። በሰው ልጅ ሊጠላ የሚገባው አመል ነው። ኢትዮጵያና አፍሪካ ሰሌብነት ነፃ ይወጣሉ ሌብነት ወንጀል ነው።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule